የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር
Appearance
| መረጃ | አካል |
|---|---|
| ርዕስ | የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር |
| መዝሙር | የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር |
| ሙዚቃ_አዘጋጅ | ሰሎሞን ሉሉ ምትኩ፤ አቶ ዳንኤል ዮሐንስ፤ ኬቮርክ ናልባንዲያን |
| የግጥም_ጸሓፊ | ደረጀ መላኩ መንገሻ፤ በአሰፋ ገብረማርያም፤ በቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ |
| ሀገር | ኢትዮጵያ |
| የተወሰነበት_ቀን | 1984, 1968, 1919 |
| የግጥም_ቋንቋ | አማርኛ |
| መግለጫ | ይህ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር በዘመነ ኢህአዴግ,በዘመነ ደርግ እና በንጉሱ ዘመን |
የዜግነት ክብር በኢትዮጵያችን ፀንቶ ታየ ህዝባዊነት ዳር እስከዳር በርቶ ለሰላም ለፍትህ ለህዝቦች ነፃነት በእኩልነት በፍቅር ቆመናል ባንድነት መሰረተ ፅኑ ሰብዕናን ያልሻርን ህዝቦች ነን ለስራ በስራ የኖርን ድንቅ የባህል መድረክ ያኩሪ ቅርስ ባለቤት የተፈጥሮ ፀጋ የጀግና ህዝብ እናት እንጠብቅሻለን አለብን አደራ ኢትዮጵያችን ኑሪ እኛም ባንቺ እንኩራ።
- ግጥም፦-ደረጀ መላኩ መንገሻ፤
- ዜማ፦- ሰሎሞን ሉሉ ምትኩ
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ -ኢትዮጵያ ቅደሚ በኅብረተሰባዊነት - አብቢ ለምልሚ! ቃል ኪዳን ገብተዋል - ጀግኖች ልጆችሽ ወንዞች ተራሮችሽ - ድንግል መሬትሽ ለኢትዮጵያ አንድነት - ለነፃነትሽ መስዋዕት ሊሆኑ - ለክብር ለዝናሽ! ተራመጂ ወደፊት - በጥበብ ጎዳና ታጠቂ ለሥራ - ላገር ብልጽግና! የጀግኖች እናት ነሽ - በልጆችሽ ኩሪ ጠላቶችሽ ይጥፉ - ለዘላለም ኑሪ።
- ግጥም፦-በአሰፋ ገብረማርያም
- ዜማ፦-አቶ ዳንኤል ዮሐንስ
(ማርሽ ተፈሪ)
ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ በአምላክሽ ኃይል በንጉስሽ ተባብረዋልና አርበኞችሽ አይነካም ከቶ ነፃነትሽ ብርቱ ናቸውና ተራሮችሽ አትፈሪም ከጠላቶችሽ። ድል አድራጊው ንጉሣችን ይኑርልን ለክብራችን።
በ1919 ዓ.ም፤ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት (አጼ ቀደማዊ ኃይለ ሥላሴ)
- ግጥም፦-በቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ
- ዜማ፦-ኬቮርክ ናልባንዲያን ፦ ደረጃ በጋሻዉ