Jump to content

የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር

ከውክፔዲያ
የብሔራዊ መዝሙር መረጃ
መረጃአካል
ርዕስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር
መዝሙር የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር
ሙዚቃ_አዘጋጅ ሰሎሞን ሉሉ ምትኩ፤ አቶ ዳንኤል ዮሐንስ፤ ኬቮርክ ናልባንዲያን
የግጥም_ጸሓፊ ደረጀ መላኩ መንገሻ፤ በአሰፋ ገብረማርያም፤ በቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ
ሀገር ኢትዮጵያ
የተወሰነበት_ቀን 1984, 1968, 1919
የግጥም_ቋንቋ አማርኛ
መግለጫ ይህ የኢትዮጵያ ብሔራዊ መዝሙር በዘመነ ኢህአዴግ,በዘመነ ደርግ እና በንጉሱ ዘመን

በዘመነ ኢህአዴግ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

(ወደፊት ገስግሺ ውድ እናት ኢትዮጵያ)

የዜግነት ክብር በኢትዮጵያችን ፀንቶ
ታየ ህዝባዊነት ዳር እስከዳር በርቶ
ለሰላም ለፍትህ ለህዝቦች ነፃነት
በእኩልነት በፍቅር ቆመናል ባንድነት
መሰረተ ፅኑ ሰብዕናን ያልሻርን
ህዝቦች ነን ለስራ በስራ የኖርን
ድንቅ የባህል መድረክ ያኩሪ ቅርስ ባለቤት
የተፈጥሮ ፀጋ የጀግና ህዝብ እናት
እንጠብቅሻለን አለብን አደራ
ኢትዮጵያችን ኑሪ እኛም ባንቺ እንኩራ።

1984 ዓ.ም፣ ዘመነ ኢህአዴግ

በዘመነ ደርግ

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ -ኢትዮጵያ ቅደሚ
በኅብረተሰባዊነት - አብቢ ለምልሚ!
ቃል ኪዳን ገብተዋል - ጀግኖች ልጆችሽ
ወንዞች ተራሮችሽ - ድንግል መሬትሽ
ለኢትዮጵያ አንድነት - ለነፃነትሽ
መስዋዕት ሊሆኑ - ለክብር ለዝናሽ!
ተራመጂ ወደፊት - በጥበብ ጎዳና
ታጠቂ ለሥራ - ላገር ብልጽግና!
የጀግኖች እናት ነሽ -  በልጆችሽ ኩሪ
ጠላቶችሽ ይጥፉ - ለዘላለም ኑሪ።

1968 ዓ.ም፣ ዘመነ ደርግ

በንጉሱ ዘመን

[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

(ማርሽ ተፈሪ)

ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ
በአምላክሽ ኃይል በንጉስሽ
ተባብረዋልና አርበኞችሽ
አይነካም ከቶ ነፃነትሽ
ብርቱ ናቸውና ተራሮችሽ
አትፈሪም ከጠላቶችሽ።
ድል አድራጊው ንጉሣችን 
ይኑርልን ለክብራችን።

1919 ዓ.ም፤ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት (አጼ ቀደማዊ ኃይለ ሥላሴ)