የ፷ዎቹ መኮንኖች ግድያ
Appearance

በደርግ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ቀጥተኛ ትዕዛዝ በአጠቃላይ ፷ የቀድሞው የዘውድ ሥርዓት ባለሥልጣናት በአንድ ላይ ያለፍርድ፣ ቅዳሜ ኅዳር ፲፬ ቀን ፲፱፻፷፯ ዓ.ም. ተረሽነው ተገደሉ። እስከዚህ ድርጊት ድረስ ከየካቲት ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ጀምሮ ያለደም ማፍሰስ ሲካሄድ የቆየውና በመስከረም ወር የቀድሞውን የዘውድ ሥርዓት ያለአንዳችም ሽብር ከሥልጣን ያወረደው አብዮት ከዚህ ኢሰብዓዊ አድራጎት በኋላ እስከ ዕድሜው ፍጻሜ ድረስ በደም የተጨማለቀ አድርጎታል።
| ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |