Jump to content

ደማስቆ

ከውክፔዲያ

ደማስቆ (ወይም ፡ ደማስቆስዓረብኛ ፦ دمشق) የሶርያዋና ፡ ከተማ ፡ ነው ።

የሚኖርበት ፡ የህዝብ ፡ ቁጥር ፡ የአካባቢውን ፡ ኗሪ ፡ ሲጨምር 2,381,800 ሆኖ ፡ ሲገመት ፡ የራሱ ፡ የከተማው ፡ ኗሪ ፡ ቁጥር ፡ ደግሞ 1,861,900 ሆኖ ፡ ይገመታል ። ከተማው 33°30′ ሰሜን ኬክሮስ እና 36°19′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ፡ ተቀምጦ ፡ ይገኛል።

በአንዳንድ ፡ ሊቃውንት ፡ ዘንድ ፣ ደማስቆ ፡ ከሁሉ ፡ ይልቅ ፡ ረጅሙ ፡ እድሜ ፡ ያለው ፡ ከተማ ፡ ነው ። በመጽሐፍ ፡ ቅዱስ ፡ ዘንድ ፡ በአብርሃም ፡ ዘመን ፡ ይገኝ ፡ ነበር ። በፍላቪዩስ ፡ ዮሴፉስ ፡ ዘንድ ፡ በአራም ፡ ልጅ ፡ በዑፅ ተሠራ ። ሚካኤል ፡ ሶርያዊው (12ኛው ፡ ክፍለ ፡ ዘመን) እና ፡ ባር ፡ ሄብራዩስ (አቡል-ፋራጅ) (13ኛው ክፍለ ዘመን) እንዳሉ ፡ ግን ፡ ዮሴፉስ ፡ ተሳተና «ሞርፎስ» ወይም «ሙሪፖስ» በተባለ ፡ ኬጢያዊ ፡ ሰው ፡ ተሠርቶ ፡ ነበር ።

ደማስቆ ፡ በኤብላ ፡ በተገኙት ፡ የኤብላ ፡ ጽላቶች (2100 ዓክልበ. ግድም) «ደማሽኪ» ተብሎ ፡ ይጠቀሳል ። የሁክሶስ ፡ ሕዝብ ፡ በ17ኛ ፡ ክፍለ ፡ ዘመን ፡ ዓክልበ. ግብጽን ፡ በገዙበት ፡ ወቅት ፣ ደማስቆ ፡ በአሙሩ ፡ ግዛት ፡ ውስጥ ፡ ነበር ። በአማርና ፡ ደብዳቤዎች (1350 ዓክልበ. ገዳማ) ዲማስቁ ፡ ተብሎ ፡ በንጉሱ ፡ ቢርያዋዛ ፡ እንደ ፡ ተገዛ ፡ ይጻፋል ። ከ1100 እስከ 740 ዓክልበ. ድረስ ፡ የአራም ፡ ከተማ-አገር ፡ ነበር ። በዚያን ፡ ጊዜ ፡ የአሦር ፡ ንጉስ 3 ቴልጌልቴልፌልሶር ፡ ያዘው ።