ደስታየሁ አድማስ

ወ/ሮ ደስታየሁ አድማስ በድሮው ጎጃም አጠቃላይ ግዛት አገው ምድር አውራጃ፤በባንጃ ወረዳ፤ በባንጃ ለኮማ ምክትል ወረዳነት ከ1936-1987 ዓ.ም የቆየች ከ1987 አ.ም ወዲህ አዊ ብሄረሰብ ዞን አስተዳደር አሁኑ ፋግታ ለኮማ ወረዳ አስተዳደር ኮሪጎሃና ቀበሌ ልዩ ስሙ ቻባርቲ ከአባታቸው አቶ አድማስ ወርቄ እና ከእናታቸው እማሆይ ሻሺቱ በቀል ጥቅምት 2 ቀን 1952 ዓ.ም ተወለደች።
ወ/ሮ ደስታየሁ አድማስ ተወለደ አቅማ ሄዋን እስኪደረስ ድረስ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በጥሩ ሁኔታ አደገች።ከዚያህ በሆላ በቤተሰብ ፍላጎትና እምነት በተነሳ በአፍላ ወጣትነቷ ማለትም በተወለደች 9 አመቷ ትዳር ያዘች። ትዳር ከየዘች በኋላም በፊቱ አጣራር ጎጃም አጠቃላይ ግዛት አገው ምድር አውራጃ ፤በባንጃ ወረዳ፤በባንጃ ለኮማ ምክትል ወረደነት ከ1936-1987 ዓ.ም የቆየች ከ1987 ዓ.ም ወዲህ አዊ ብሄረሰብ ዞን ስር በአሁኑ ፋግታ ለኮማ ወረዳ አስተዳደር ኮሪጎሃና ቀበሌ ቸዋሲ ኪ/ምህረት ከትዳር በለቤታቸው አቶ በሪሁን ታምር ጋር ኑሮዋን መስርተው ሁለት ልጆችን
አፍርተው የሚኖሩ ታዋቂ
እና ዝናኛ አከበባውን ህብረተሰብ ወይም ማህበረሰብ የሚያከብሩ ታላቅ እናት ናቸው።




ወ/ሮ ____ በህይወት እያሉ የካናወኑት ተግባራት ውስጥ፦
~ ቸዋሲ ኪዳነ ምህረት ስትቋቋም 100 ብር ለመቋቋሚያ አበርክተዋል፣
~ ቸዋሲ ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ከሳር ወደ ቆርቆሮ ሲቀየር 200 ብር ለግሰዋል፣
~ ቸዋሲ ኪዳነ ምህረት ሶለር ሲገመጥ 150 ብር አበርክተዋል፣
~ ቸዋሲ ኪዳነ ምህረት የሚኬኤል ማህበር ከቀበሌ ማህበረሰብ ጋር በሰፊው ሲያጣጡና ሲጠጡ ቆይተዋል፣
~ የስላሴ ማህበር ከ680 ህዝብ ጋር ሲጠጡና ሲያጠጡ ቆይተዋል፣
~ የሰንበቴና የፅጌ ማህበር ከቸዋሲ ኪዳነ ምህረት ህዝብ ጋር ሲጠጡና ሲያጠጡ ቆይተዋል፣
~ ወ/ሮ ____ የቸዋሲ ኪዳነ ምህረት መንበር ሲገባ 150 ብር አበረክተዋል፣
~ ወ/ሮ ____ አራት ወንድ ልጆች እና ሁለት ሴት ልጆች የወለዱ ሲሆኑ የእነዚህም ሁሉ ልጆች ጦለት ቆርጠው ድረው ትዳር አስመስርተቸዋል።
~ ወ/ሮ ____ አንድም ወንድ ልጅ በዘመናዊ ት/ቤት አስገብተው በጥሩ ሁኔታ አስተምረው በዲግሪ መእረግ ደረጃ እንዲበቃና እንዲደረስ አድርገዋል፣
~ ወ/ሮ ____ ከበለቤታቸው ጋር በንስሃ አባታቸው አስራት ኩራት አውጥተው ንስሃ ገብተው ስጋውን ደሙን የተቀበሉ እናት እንደሆኑ የህይወት ታሪካቸው ይመሰክርላቸዋል።
~ ሟች ወ/ሮ ____ የ6 የወንድ ልጆች እና የ2 የሴት ልጆች እናት ሲሆኑ በድምሩ የ8 ልጆች እናት ናቸው። ሟች ____ በህይወት ሲኖሩ አንድም ሰው ጋራ ይክርታ የሌላቸው ፀባያቸው የአማረ እንደሆነ ሁሉም ህዝብ የሚወደቸው ደግ እናት ነቸው።
~ ሟች ወ/ሮ ____ በህይወት ሲኖሩ ትልቀቸውን ያከበሩ፣ ዘር ለሌላቸው ዘር ያበዳሩ፣ ለታቦት የዘከሩ፣ ለመንግስት የገበሩ ደግ እናት ናቸው።
ሟች ወ/ሮ ____ በደረባቸው ህመም ምክንያት ከኮሰበር ሪፈራል ሆስፒታል፣ በባህር ዳር ፈለገ ህይወት ጠቅላላ ሆስፒታል ህክምና ልጆቻቸው አስገብተው ሲረዱ ቆይተው ሊሻለቸው በለመቸላቸው ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም በተወለዱት 70 አመታቸው በቀኑ 6 ሰዓት ውድ ህይወታቸው አልፎ ዛሬ ደግሞ ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም ቸዋሲ ኪዳነ ምህረት ቀበሌ ቤተክርስቲያን የቀብር ስርኣታቸው ልክ ከቀኑ 6 ሰዓት በብዙ ሊቃውንት ስርዓተ ፍታት፣ በብዙ ፈረስተኞች እጀባ እና በብዙ ህዝብ በተሰበሰባበት ስርኣቱ ተፈፅሞላቸዋል። ነፍሳቸው ይመር!!
| ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |