ጉና ተራራ በደቡብ ጎንደር በነፋስ መውጫ አውራጃ የሚገኝ ሲሆን በከፍታው ከአፍሪካ 9ኛ፣ ከኢትዮጵያ ደግሞ 3ኛ ነው። ከፍታውም 4231 ሜትር ይደርሳል። ቀይ ቀበሮ በዚህ ተራራ የሚገኝ ሲሆን ከስሩም ጣና ሐይቅን የሚመግበው የርብ ወንዝ ይፈልቃል።