ፀጉር

ከውክፔዲያ
200 ጊዜ ተልቆ የተነሳ የሰው ልጅ ፀጉር

ፀጉርፕሮቲን የበለጸገ follicles ከተባለ የሰውነት ክፍል ማደግ የሚጀምር አካል ነው። ይህ አካል በተለይም ኬራቲን (keratin) ከተባለው የፕሮቲን አይነት የተገነባ ነው። በአብዛሃኛው ጊዜ ፀጉር የአጥቢ እንስሳት መለያ ቢሆንም በአንዳንድ ነፍሳት ላይ ይታያል፤ ይህ ግን በሳይንስ ፀጉር አይባልም።

ባሕል[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ጽጉር በእጅ ሲጐተት ከአይን እስከሚታይ ድረስ ያለመረዘሙ ለወንዶች የሚለው ደንብ፣ የተነሣ በፍትሐ ነገሥት ቀኖኖች ይገኛል (፶፩፣ 1800)፤ «ጠጉርህ በአፍኣ በውጭ አይታይ» (ኢያስተርኢ ሥዕርትከ በአፍኣ) ሲል፤ በ1958 ዓም በብርሃንና ሰላም በታተመው በድሮ ፎቶ ኦፍሴት አማርኛ ነጥቦች ዘንድ፣ ይህ ማለት በገዛ እጅህ ተጎትቶ የራስህ ጽጉር ወይንም ሪዝህ በአይንህ እንዳይታይ የሚል ደንብ ነበር። (አለበለዚያ ለናዝራዊ ወይም ለባሕታዊመኖኩሴ ግን የተፈጥሮ ጉንጉኖች ሥርዓት ከሙሴ አለ።) በእስልምና መጻሕፍት በተለይ ለጥቁሮች የተለየ ልምድ ኖሯል፣ በዚህም በኩል የወንድ ጸጉር ከጆሮ ይልቅ እንዳይዘረጋው የሚል ነው።

ተጨማሪ ይዩ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]