መስከረም ፴
ከውክፔዲያ
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የመጀመሪያ ወር መደምደሚያ እና የዓመቱ ፴ኛው ዕለት ሲሆን፣ የመፀው ወቅት ፭ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ሉቃስ ፫፻፴፮ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ዮሐንስ ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፫፻፴፭ ዕለታት ይቀራሉ።
ማውጫ |
[ለማስተካከል] ታሪካዊ ማስታወሻዎች
- ፮፻፸፫ ዓ/ም የቀሊፋ ቀዳማዊ ያዚድ ወታደሮች በካርባላ ጦርነት ላይ የነቢዩ ሞሐመድን የልጅ ልጅ የአሊ ልጅ ሁሴንን አንገቱን በመቁረጥ ሰውት። ሺአቶች ዕለቱን በሐዘን ያስቡታል፡፡
- ፲፰፻፷ ዓ/ም - ዓፄ ቴዎድሮስ ርዕሰ ከተማቸው ያደረጓትን ደብረ ታቦር ካቃጠሉ በኋላ አውሮፓውያን ሠራተኞቻቸውን እና ሠራዊታቸውን አስከትለው ጉዟቸውን ወደ መቅደላ ምሽግ ጀመሩ።
- ፲፱፻፶ ዓ/ም የጋናው የገንዘብ ሚኒስትር ኮምላ አግቤሊ ግብዴማ፣ በዘረኛነት ጥላቻ ምክንያት በዴላዌር ምግብ ቤት መስተንግዶ በመነፈጋቸው፣ የአሜሪካው ፕሬዚደንት ድዋይት አይዘንሃወር ይቅርታ ጠየቋቸው።
- ፲፱፻፸፫ ዓ/ም ሁለት ትላልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ነውጦች ኤል አስናም በምትባለዋ የሰሜናዊ አልጄሪያ ከተማ ላይ የ፳ ሺህ ሰዎችን ነፍስ ጥፋትና የብዙ ሺህ ሰዎችን የአካል ጉዳት አስከተሉ።
[ለማስተካከል] ልደት
[ለማስተካከል] ዕለተ ሞት
- ፲፱፻፺፰ አገራቸውን ዩጋንዳ፣ መጀመሪያ ወደነጻነትና በጄኔራል ኢዲ አሚን መፈንቅለ መንግሥት እስከወደቁ ጊዜ ድረስ በቀዳማዊ ጠቅላይ ሚንስትርነት፤ ከአሚን ውድቀት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ በመፈንቅለ መንግሥት እስከተሰደዱ ድረስ ያገለገሉት አፖሎ ሚልተን ኦቦቴ ጆሃንስበርግ ላይ አረፉ::
[ለማስተካከል] ዋቢ ምንጮች
- (እንግሊዝኛ) http://news.bbc.co.uk/onthisday/hi/dates/stories/october/10/
- (እንግሊዝኛ)Markham, Clements R., A History of the Abyssinian Expedition, London Macmillan and Co. (1869)
- (እንግሊዝኛ) http://www.answers.com/topic/milton-obote
| የኢትዮጵያ ወራት | |
|---|---|
| መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ | |