ዓመት በዓላት እና ታሪካዊ ማስታወሻዎች

ከውክፔዲያ
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

እንኳን ለ ፳፻፬ ዓመተ ምሕረት በሰላም አደረሳችሁ!!!Adey abeba.jpg

ማውጫ

[ለማስተካከል] ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች

[ለማስተካከል] መስከረም

መስከረም 1 ቀን: ዕንቁጣጣሽ፣ ብሄራዊ ቀን በካታሎኒያ እስፓንያ...


መስከረም 2 ቀን: ብሄራዊ ቀን በኬፕ ቨርድ...

Flag of Cape Verde.svg

መስከረም 3 ቀን

George Washington at the Philadelphia Convention.jpg

መስከረም 4 ቀን

T Roosevelt.jpg

መስከረም ፭ ቀን

Agatha Christie.png

መስከረም ፮ ቀን

Oliver Cromwell by Samuel Cooper.jpg

Camp David, Menachem Begin, Anwar Sadat, 1978.jpg

*፲፱፻፸፩ ዓ.ም. - የግብጽ ፕረዚዳንት አንዋር ሳዳት እና የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ሜናኽም ቤጊንአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተር ሸምጋይነት፣ ከ ፲፪ ቀናት የምሥጢር ድርድር በኋላ፤ በካምፕ ዴቪድካምፕ ዴቪድ ስምምነት ተፈራረሙ።

  • ፫፻፹፯ዓ/ም - የሮማ ንጉዛት ክርስቲያናዊ ቄሳር ቀዳማዊ ቴዎዶስዮስ ዘውዱን ለመንጠቅ የተነሳውን አረመኔያዊ የምዕራብ ሮማ መሪ አውግንዮስን በፍሪጊዱስ ውግያ ሲያሸንፍ የሮማ ክርስቲያናዊ ንጉዛት በመጽናቱ የክርስትና ሃይማኖት በአውሮፓ ቀደምትነትን እንዲይዝ አድርጎታል።
  • ፲፰፻፺፱ ዓ/ም - በሆንግ ኮንግ አካባቢ የተከሰተ አውሎ ንፋስ እና የባሕር ሞገድ (tsunami) ፲ ሺ የሚጠጉ ሰዎችን ሕይወት አጥፍቷል።
  • ፲፱፻፪ ዓ/ም - የጋናው የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር እና የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ክዋሜ ንክሩማ በዚህ ዕለት ተወለዱ።
  • ፳፻፪ ዓ/ም በምዕራብ ጐጃም የአንድነት ቅርንጫፍ ቢሮ አስተባባሪዎች ላይ ድብደባ ተፈጸመ
  • ፲፱፻፴፮ ዓ.ም. - የሙሶሊኒ አዲስ ፋሺስታዊ መንግሥት በአዶልፍ ሂትለር ግፊት እና ድጋፍ 'የጣልያን ሕብረተሰባዊ ሪፑብሊክ' በሚል ስም በሰሜን ጣልያን ጀመረ።
  • ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. - ቀድሞ "የፈረንሣይ ሱዳን" የተባለው ቅኝ ግዛት የማሊ ሪፑብሊክ ተብሎ ነጻነቱን አወጀ።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የሠራተኞች ማኅበር ፕሬዚደንት፤ ምክትል ፕሬዚደንት እና ዋና ጸሐፊ አዲስ ሥልጣን በያዘው የደርግ ወታደራዊ መንግሥት ትዕዛዝ ተይዘው ታሠሩ።


  • ፲፱፻፺፱ ዓ/ም የህውሐት ማእከላዊ ኮሚቴ አቶ መለስ ዜናዊ የድርጅቱ ሊቀ መንበር ሆነው እንዲያገለግሉ በድጋሚ መረጠ፡ ...
  • ፮፻፲፭ ዓ/ም - ነቢዩ መሐመድ ከመካ እስከ መዲና ያደረገውን የሱባዔ ጉዞ (ሂጅራ) ፈጸመ።
  • ፲፱፻፷፱ ዓ/ም - በአፍሪቃ አኅጉር ደቡባዊ አካል፣ በ ኢያን ስሚዝ የሚመራው የሮዴዚያ (የአሁኗ ዚምባብዌ) የነጭ አስተዳደር መንግሥቱን ለበዢው የጥቁር ሕዝብ በሁለት ዓመት ውስጥ ለማስረከብ ተስማማ።

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/መስከረም 15

  • ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - ‘ጁላ’ (MV Joola) የተባለች የሴኔጋል የንግድ መርከብ ከተፈቀደላት የሰው ጭነት በላይ ሦስት እጥፍ ጭና ስትጓዝ ከጋምቢያ ጠረፍ አካባቢ ላይ ሰምጣ ወደ ፩ሺ ፰፻፷፫ መንገደኞች ሕይወታቸውን አጡ።
  • ፲፱፻፱ ዓ/ም - በትልቁ የመስቀል በዓል ቀን መኳንንቱ ከነሠራዊቱ፤ ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስና እጨጌ ወልደ ጊዮርጊስ ከነካህናቱ በተሰበሰቡበት በ ፲ ነጥብ የተዘረዘረው የልጅ እያሱ ወንጀል ተነቦ እሳቸውን ሽረው ወይዘሮ ዘውዲቱን ንግሥት፣ ደጃዝማች ተፈሪራስ ብለው አልጋ ወራሽና የመንግሥቱ እንደራሴ ተደረጉ።
José Eduardo dos Santos 2.jpg

መስከረም ፳ ቀን

መስከረም ፳፩ቀን

በዚህ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ማርያምን በዓል በማሰብ ትዘክረዋለች።


  • ፲፱፻፶፬ ዓ.ም - የምስራቅ እና የምዕራብ ካሜሩን ክፍሎች ተዋህደው፣ የካሜሩን ፌዴራላዊ ሪፑብሊክን መሠረቱ።
  • ፲፱፻፶፬ ዓ.ም - በአሜሪካ የጥቁሮች ሰብዓዊ መብት ትግል ጄምስ መሬዲዝ የተባለውን ጥቁር ተማሪ ወደ ሚሲሲፒ ዩኒቨርሲቲ መግባት በተከሰተው ግጭት ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ሰባ አምሥት ሰዎች ደግሞ የአካል ጉዳት ደረሰባቸው።
  • ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - ለሟቹ የግብጽፕሬዚደንት ጋማል አብደል ናስር የቀብር ስርዓት የወጡ ወደ አምሥት ሚሊዮን የሚገመቱ አዘነተኞች በተነሳ ግርግር እና ግፊያ ብዙ ሰዎች ተጨፍልቀው ሞቱ።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በፊሊፒንስ ከተማ ማኒላ ላይ በተካሄደው የቡጢ ውድድር ሞሐመድ አሊ ባላጋራውን ጆ ፍሬዘርን ከአሥራ አራት ዙር ግብግብ በኋላ በነጥብ ብልጫ አሸነፈ።
John Logie Baird.png

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/መስከረም 25 መስከረም ፳፮ ቀን

  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የግብጽ ሠራዊት በእስራኤል ላይ የ’ራመዳን ጦርነት’ ወይም የ’ዮም ኪፑር’ ጦርነት በመባል የሚታወቀውን የስድስት ቀን ውጊያ ከፈቱ።

መስከረም ፳፯ ቀን

  • ፲፱፻፲፪ ዓ/ም - የሆላንድን ዓርማ ያዘለው ‘ኬ. ኤል. ኤም’ (KLM) የተባለው እና ከምሥረታው ጀምሮ እስካሁን ስሙንም ሆነ ዓርማውን ሳይቀይር በመቆየት አንደኝነትን ያስመዘገበው ዓየር መንገድ ተመሠረተ።
  • ፲፱፻፳፮ ዓ/ም - አምሥት ነባር የፈረንሳይ አየር መንገዶችን በማዋሐድ የአሁኑ ‘ኤየር ፍራንስ’ (Air France) ተመሠረተ።
  • ፲፱፻፺፱ ዓ/ም -ኤርትራዊው ዘፋኝ፣ ገጣሚ እና የሙዚቃ አቀናባሪ አብርሐም አፈወርቂ ቀይ ባህር ውስጥ ሰምጦ በተወለደ በ ፵ ዓመቱ ሞተ።
  • ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው ስብከተኛ እና የሰብዓዊ መብት ታጋይ ጄሲ ጃክሰን በዚህ ዕለት ተወለደ።
Jesse Jackson at Max Palevsky Cinema crop.jpg
  • ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - በፓኪስታን እና ሕንድ ድንበር አካባቢ የሚኖሩ ፹፮ንሺህ ያህል ሰዎች በተከሰተው ትልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ አደጋ ሕይወታቸውን አጡ።

መስከረም ፴

Tokyo olympics & eth flag.jpg
  • ፮፻፸፫ ዓ/ም - የቀሊፋ ቀዳማዊ ያዚድ ወታደሮች በካርባላ ጦርነት ላይ የነቢዩ ሞሐመድን የልጅ ልጅ የአሊ ልጅ ሁሴንን አንገቱን በመቁረጥ ሰውት። ሺአቶች ዕለቱን በሐዘን ያስቡታል፡፡
  • ፲፱፻፶ ዓ/ም - የጋናው የገንዘብ ሚኒስትር ኮምላ አግቤሊ ግብዴማ፣ በዘረኛነት ጥላቻ ምክንያት በዴላዌር ምግብ ቤት መስተንግዶ በመነፈጋቸው፣ የአሜሪካው ፕሬዚደንት ድዋይት አይዘንሃወር ይቅርታ ጠየቋቸው።
  • ፲፱፻፸፫ ዓ/ም - ሁለት ትላልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ነውጦች ኤል አስናም በምትባለዋ የሰሜናዊ አልጄሪያ ከተማ ላይ የ፳ ሺህ ሰዎችን ነፍስ ጥፋትና የብዙ ሺህ ሰዎችን የአካል ጉዳት አስከተሉ።

[ለማስተካከል] ጥቅምት

ጥቅምት ፩ ቀን

KasaTesema.jpg
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም የክራሩ ጌታ፤ የኮሪያው ዘማች፤ ካሳ ተሰማ በተወለደ በ፵፯ ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ጥቅምት ፪ ቀን

ጥቅምት ፫ ቀን


Hosni Mubarak - Official Photo.JPG
  • ፲፱፻፸፬ዓ/ም - የምስር ምክትል ፕሬዚደንት ሆስኒ ሙባራክ የቀድሞው ፕሬዚደንት አንዋር ሳዳት በተገደሉ በሳምንቱ የአገሪቱን ፕሬዚደንታዊ ሥልጣን ተረከቡ።
  • ፲፱፻፹፯ ዓ/ም - የፍልስጥኤም መሪ ያሲር አራፋት፤ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ይስሓቅ ራቢን እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ስምዖን ፔሬዝ የዓመቱን የኖቤል ሰላም ሽልማት በኅብረት ተቀበሉ።

ጥቅምት ፬ ቀን

MLK nobelpeaceprize.jpg

ጥቅምት ፭ ቀን

  • ፲፮፻፺፱ ዓ/ም - በዓፄ ተክለ ሃይማኖት (ስመ መንግሥት ልዑል ሰገድ) ትዕዛዝ፣ ሸሽተው ጣና ሐይቅ ላይ በጨቅላ መንዞ ደሴት የነበሩትን አባታቸውን ዳግማዊ ኢያሱ አድያም ሰገድን ጳውሎስ እና ደርመን የተባሉ ነፍሰ ገዳዮች ሕይወታቸውን ካጠፉ በኋላ አስከሬናቸውን በእሳት አቃጠሉት። ከቃጠሎ የተረፈውን ካህናቱ በታንኳ ወስደው ምጽራሓ ደሴት ላይ ቀበሩት።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የቀድሞው ንጉሠ ነገሥት የልጅ ልጅ መቶ-ዓለቃ ልዑል መኮንን መኮንን ትምህርት ላይ ከነበሩበት ከአሜሪካ ወደአገራቸው በአስቸኳይ እንዲመለሱ ደርግ ትዕዛዝ አስተላለፈ።

ጥቅምት ፮ ቀን


Anwar Sadat cropped.jpg
  • ፲፱፻፸፬ ዓ/ም - ስመ ጥሩው የእስራኤል ጄኔራል፤ እንዲሁም በአገሪቱ የመከላከያ ሚንስቴርነት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርነት ማዕረግ የበቁት ሞሼ ዳያን በተወለዱ በ፶፮ ዓመታቸው በሞት ተለዩ።

ጥቅምት ፯ ቀን

Einstein 1921 portrait2.jpg
CheHigh.jpg
  • ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የሶርያን ሪፑብሊክ ሕጋዊነት እንደሚያውቅና እንደሚያከብር ይፋ አደረገ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ.ም - አረባዊ የነዳጅ አምራች አገሮች፣ እስራኤልን ረድታችኋል በማለት የወነጀሏቸውን ምዕራባዊ አገሮችችና በጃፓን ላይ ለአንድ ዓመት ሙሉ የነዳጅ ክልከላ ስልት አካሄዱ።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኅብረተ-ሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት በመላ አገሪቱ የነበሩትን የማዘጋጃ ቤት ሸንጎዎች እንዲዘጉ አዘዘ።

ጥቅምት ፰ ቀን


Edison-at home in Ft. Myers Florida 1914 detail LC-LC-USZ62-131044 .tiff adjusted.jpg
  • ፲፱፻፸ ዓ.ም. - የምዕራብ ጀርመን ወታደራዊ ጸረ ሽብርታዊ ቡድን በሽብርተኞት ተጠልፎ ሞጋዲሹላይ ያረፈውን የሉፍትሃንሳ አውሮፕላን ካስገደዱት አራት ሽብርተኞች መኻል ሦስቱን በመግደል የተያዙትን ፹፮ ሰላማዊ ተሳፋሪዎች ነጻ አወጣ።

ጥቅምት ፱ ቀን

  • ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - የአሜሪካ መንግሥት ለፍንጫ ወንዝ ልማት የተመደበ ፸፭ ሚሊዮን ብር የብድር ውል ከኢትዮጵያ ንጉዛት ጋር ተፈራረመ።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኅብረተ-ሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት፣ የቀድሞ የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት ባለሥልጣናት የሚዳኝ ወታደራዊ የፍትሕ ሸንጎ መሠረተ።
Dejazmachkidane.jpg
  • ፲፱፻፸፱ ዓ/ም - የሞዛምቢክን ፕሬዚደንት ሳሞራ ማሼልን እና አብረዋቸው የሚጓዙ ፴፫ ሰዎችን የጫነው አየር ዠበብ በአገሪቱ ውስጥ ሌቦምቦ ተራራ ጋር ሲጋጭ ተሳፋሪዎቹ ሕይወታቸው አልፏል።
  • ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞው የኢራቅ ፕሬዚደንት ሳዳም ሁሴን በነፍሰ ገዳይነት እና በሰፊው በሰው ልጅ ላይ ወንጀል ሠርተዋል በመባል ፍርድ ቤት ሲቀርቡ፣ ከተከሰሱባቸው ወንጀሎች ሁሉ ነፃ መሆናቸውን መሰከሩ።
  • ፲፱፻፺፱ ዓ/ም - በከፍተኛ ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ የሚፈለጉ ኢትዮጵያውያንን በሞያሌ በኩል ሸኝተው ለማስኮብለል የሞከሩ የውጭ ዜጋ የሆኑ ሁለት የአውሮፓ ኮሚሽን ሠራተኞች በወንጀል ከተጠረጠሩት ኢትዮጵያውያን ጋር በዛሬው እለት እጅ ከፍንጅ ተያዙ ከተባለ በኋላ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ዋና መምሪያ ይህን ህገ ወጥ ተግባር የፈፀሙት ሁለቱ የውጪ ዜጎችም ከአገር እንዲወጡ መወሰኑን ገለፀ፡፡

ጥቅምት ፲

  • ፲፯፻፴፫ ዓ/ም - “የአውስትሪያ አልጋ የውርስ ጦርነት” ዐቢይ ምክንያት የሚባለው፣ ንግሥትማሪያ ተሬዛ አባቷ ንጉሥ ቻርልስ ስድስተኛ በዛሬው ዕለት አርፎ እሷ ዙፋኑን መውረሷ ነው።
  • ፲፰፻፵፯ ዓ.ም. - በ ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ሐረር ላይ ሰፍሮ ይኖር የነበረው፣ ፈረንሳዊው ግጥም ተቃኝ አርተር ራምቦ (Arthur Rimbaud)በዚህ ዕለት ተወለደ።
Jomo Kenyatta.jpg
  • ፲፰፻፹፬ ዓ.ም -በጎረቤት አገር በኬንያ አገራቸውን ከብሪታንያ ቅኝ ግዛትነት ነጻ ለማውጣት በመጋደል ቆይተው አገሪቱ ነጻ ስተውጣም የመጀመሪያው ፕሬዚደንት የነበሩት ጆሞ ኬንያታ ተወለዱ።
  • ፲፱፻፵፭ ዓ.ም - በብሪታንያ ቅኝ ግዛት፣ ኬንያ ውስጥ ለነጻነት ይካሄድ የነበረውን የማው ማው ትግልን ለማክሸፍ በሚል ምክንያት የግዛቷ ዋና አስተዳዳሪ የነበረው ኤቨሊን ቤሪንግ “አደገኛና አስቸኳይ ሁኔታ” አውጆ የሽብሩ መሪዎች የነበሩትን እነጆሞ ኬንያታን በእሥራት ቁጥጥር አዋለ።

ጥቅምት ፲፩

Hernando de Magallanes del museo Madrid.jpg
Bikila in Tokyo 1964.jpg
  • ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - የሮማ ኦሊምፒክ የማራቶን ድል አድራጊው አበበ ቢቂላቶክዮ ውድድር የራሱን የኦሊምፒክ ክብረ ወሰን በመስበር በ2 ሰዓት 12 ደቂቃ 11.2 ሰከንድ አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ድልን ተቀዳጀ። ከዚህ ድል ከሰላሳ ስድስት ቀናት በፊት ትርፍ አንጀቱን በቀዶ ሕክምና አስወግዶ ስለነበረ፣ ድሉን ለሁለተኛ ጊዜ ብቻ ሳይሆን ሳያገግም በአዲስ ክብረ ወሰን ማሸነፉ በማራቶን ውድድር እስካሁን ድረስ አቻ የለሽ ጀግና አድርጎ አስመስክሮለታል።

ጥቅምት ፲፪

  • ፲፯፻፺ ዓ/ም - በፓሪስ ከተማ፣ ሦስት ሺህ ሁለት መቶ ጫማ ሽቅበት ላይ አንድሬ-ዣክ ጋርኔራን የተባለ ሰው በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በመዝለያ ጥላ (parachute) ዘለለ።
Haile Melekot.JPG
Negus Sahle Selassie.jpg
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) ዋና ማዕከሉን ከ፬ኛ ክፍለ ጦር ወደ ታላቁ ቤተ መንግሥት አዛወረ።

ጥቅምት ፲፫

Afewerk tekle.jpg
  • ፲፱፻፬ ዓ/ም - በቱርክና በኢጣሊያ መካከል በነበረው ጦርነት የቱርኮችን የጦር ግንባር ከአየር ለመሰለል የኢጣልያ አውሮፕላንሊቢያ ተነሳ። ይሄም ድርጊት አውሮፕላን በጦርነት ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለበት ዕለት ነው።
  • ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ፔሌ በሚል ቅጽል ስሙ የሚታወቀው የብራዚል እግር ኳስ ተጫውች ኤዲሶን አራንቴስ ዶ ናሲሜንቶ ተወለደ። ፔሌ በዓለም የኦሊምፒክ ሸምቡድ (International Olympic Committee) “የ፳ኛው ክፍለ ዘመን አትሌት” ብሎታል።

ጥቅምት ፲፬

421px-Rosaparks.jpg
  • ፲፱፻፶፱ ዓ/ም - ቼልሲ የሚባለው የእንግሊዝ የእግር ኳስ ቡድን ባለቤት ሩሲያዊው ሀብታም ሮማን አብራሞቪች በዚህ ዕለት ተወለደ።

ጥቅምት ፲፭

  • ፲፰፻፶ ዓ/ም - ሼፊልድ በሚባለው የእንግሊዝ ከተማ፣ የሼፊልድ የእግር ኳስ ክለብ ሲመሠረት በዓለም የመጀመሪያው የእግር ኳስ ክለብ ነው።
  • ፲፱፻፸፮ ዓ/ም - በ ካሬቢያን ባሕር ላይ በምትገኘው የግሬናዳ ደሴት ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት በተካሄደበት ሣምንት ውስጥ የአሜሪካው ፕሬዚደንት ሮናልድ ሬጋን “የአሜሪካን ዜጋዎች ደኅንነት” ለመጠበቅ በሚል ምክንያት ደሴቷን በአገራቸው ሠራዊቶች አስወረሩ።

ጥቅምት ፲፮

Shah of iran.jpg

ጥቅምት ፲፯

Ras Mikel Wello.jpg

ጥቅምት ፲፰

ጥቅምት ፲፱

  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) ሥልጣን ሲጨብጥ ቀርበው እንዲመረመሩ ባዘዛቸው መሠረት ባለመገኘታቸው የቀድሞው ንጉሠ ነገሥት የልጅ-ልጅ የልዑል መኮንን መኮንንን እና የትግሬውን አገረ ገዥ የልዑል-ራስ መንገሻ ሥዩምን ንብረት ወረሰ። እንዲሁም ደርግ ባስተላለፈው አዋጅ መሠረት በ”ብሔራዊ የሥራ ዘመቻ” ላይ ሳይሳተፉ የሚቀሩ ተማሪዎችን በጽኑ እንደሚቀጣ በዚሁ ዕለት አስታወቀ።

ጥቅምት ፳

Rumble-in-the-jungle-Zaire.jpg
  • ፲፱፻፺፩ ዓ.ም. - “ሃሪኬን ሚች” የተባለው ታላቅ አውሎ ነፋስ ባስከተለው የጭቃ ጎርፍ ኒካራጓ ላይ በጥቂቱ ሁለት ሺህ ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ።

ጥቅምት ፳፩

Indira2.jpg
  • ፲፱፻፸፯ ዓ.ም. - የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኢንዲራ ጋንዲ በሁለት የሲክ የጥበቃ ወታደሮቻቸው እጅ ተገደሉ። ይሄንንም ሁኔታ ተከትሎ በኒው ዴሊ በፈነዳው የሕዝብ ሽብር ወደ ሁለት ሺህ የሚጠጉ የሲክ ተወላጆች ሕይወታቸውን አጡ።

ጥቅምት ፳፪

Menelik statue1.jpg

ጥቅምት ፳፫

Coronation of HS.jpg
  • ፳፻ ዓ.ም. - በሰሜን ሸዋ አስተዳደር፣ በሀገረ-ማርያም ከሰም ወረዳ፣ ኮረማሽ አጥቢያ የሚገኘው የየለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በዘመናዊ መልክ ከተገነባ በኋላ ተመርቆ አገልግሎት ላይ ዋለ።

ጥቅምት ፳፬

ጥቅምት ፳፭

Menelik II - 4.jpg
  • ፲፰፻፹፪ ዓ.ም - የሸዋንጉሥ ምኒልክ በ እንጦጦ “መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም” ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሊቀ ጳጳሱ በአቡነ ማቴዎስ እጅ ቅብዓ መንግሥት ተቀብተው፣ ዳግማዊ ምኒልክ ተብለው የንጉሠ ነገሥት ዘውድ ጫኑ።
  • ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. - የኢራን ሻህ ሬዛ ፓህላቪ በሕዝብ ፍንቀላ ከሥልጣን ከወረዱ በኋላ አብዮታዊ ተማሪዎች የአሜሪካን ኤምባሲ በኃይል ደምሥሠው ገብተው ዘጠና የአሜሪካ ዜጎችን በቁጥጥራቸው ስር አዋሉ።

ጥቅምት ፳፮

  • ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - በኢትዮጵያ እና በታላቋ ብሪታኒያ መኻል የስልክ ግንኙነት ተጀመረ። አገልግሎቱ በወቅቱ ከሰኞ እስከ ዓርብ ብቻ ከጧቱ ፭ ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ ፮ ሰዓት ከሩብ ድረስ የተወሰነ ሲሆን ከብሪታኒያ በደቂቃ አንድ ፓውንድ ስተርሊንግ ከሩብ (£1.25) ይፈጅ ነበር።
  • ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. - የቀድሞው የኢራቅ ፕሬዚደንት ሳዳም ሁሴን በአገራቸው ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተመሠረተባቸው ክስ በሰው ዘር ላይ አድርገዋል በተባሉባቸው ወንጀሎች ኃላፊነታቸው ተረጋግጦ የስቅላት ሞት ተፈረደባቸው።

ጥቅምት ፳፯

Nasser.jpg

ጥቅምት ፳፰

  • ፲፮፻፷፩ ዓ/ም - በዕለተ እሑድ ፀሐይ ደም መስላ እንደታየችና ሁለመናዋ በጉም እና ጭለማ እንደተከበበች (በግዕዙ፦”…ወተወለጠ ኵለንታሃ በኅብረ ጢስ ዘጸሊም” ይለዋል) የዘመኑ ‘ዜና-መዋዕል’ አስፍሮታል። ይህ የፀሐይ ግርደት በከፊል እስከ እንግሊዝ አገር ድረስም እንደታየ በፈረንጆቹ ተዘግቧል።

ጥቅምት ፳፱

  • ፲፰፻፹፪ ዓ.ም. - በአሜሪካ ሰሜን ምዕራብ የሚገኘውና ስሙ ከስፓኝኛ ቋንቋ ሞንታኛ (ተራራ) የመጣው ሞንታና የተባለው ክልል የአሜሪካ ሕብረትን በመቀላቀል አርባ አንደኛው ክፍለ ግዛት ሆነ።
John F. Kennedy, White House color photo portrait.jpg
  • ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. - በብሪታንያ የሞት ቅጣትን የሚሽር ሕግ በአገሪቷ ንግሥት ስምምነትና ፊርማ ተደነገገ።
  • ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአድአን አካባቢ በዘመናዊ ግብርና ለማልማት የሚያስችል፣ በ፵ ዓመት የሚከፈል የሦስት ተሩብ ሚሊዮን ብር (E$3.25 million) ብድር ውል ከአሜሪካ መንግሥት ጋር ተፈራረመ።

ጥቅምት ፴

Haile Melekot.JPG
  • ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. - የጀርመን ፖሊሶችና ወታደሮች በሙኒክ ከተማ የቢራ አዳራሽ በናዚዎች ቅስቀሳ የተጀመረውን ያልተሳካ መፈንቅለ መንግሥት ደመሰሱ።
  • ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. - በጀርመን እና በአውስትሪያ አገሮች ናዚዎች የይሁዳውያን መቅደሳትና መደብሮችን በዝብዘው በእሳት አጋዩ። ይሄም ታሪካዊ ምዕራፍ “Kristallnacht” የመስተዋት መስበሪያ ምሽት በመባል ይታወቃል።
  • ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. - በሰሜን ምሥራቅ አሜሪካ ግዛቶችና በካናዳ ለአሥራ ሦስት ሰዐት ተኩል ያህል ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ ስምንት መቶ ሺህ ሰዎች በኒው ዮርክ ውስጠ መሬት ባቡር ላይ ተደንቅረው አመሹ። ችግሩ በግምት የሃያ አምስት ሚሊዮን ሕዝቦችን ኑሮ አዛብቷል።

[ለማስተካከል] ኅዳር

ኅዳር ፩

  • ፲፱፻፹፰ ዓ.ም. - በናይጄሪያ ታዋቂው ደራሲና የተፈጥሮ ጉዳይ ተከራካሪ ኬን ሳሮ ዊዋ፣ ሰፊ የዓለም አቀፍ ተቃውሞ ቢኖርም በአገሪቱ መንግሥት ከ ሌላ ስምንት ሰዎች ጋር በሰቀላ የሞት ቅጣት ተቀጣ።

ኅዳር ፪

  • ፲፱፻፲፩ ዓ.ም. - ከአራት ዓመት ጦርነት በኋላ የአንደኛው የዓለም ጦርነት በአንድ በኩል ንምሳ በሌላ በኩል ተቃዋሚዎቿ አባር አገሮች በስምምነትና በፊርማ ውጊያው ከጧቱ አምስት ሰዐት ላይ እንዲያቆም ተስማሙ። ይሄ ድርጊት በየዓመቱ ከጧቱ አምስት ሰዐት ላይ በሁለት ደቂቃ ሕሊናዊ ጸሎት ይከበራል።
ArafatEconomicForum.jpg

ኅዳር ፫

  • ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. - በአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን በነበረ ቴዎድሮስ ኸርዝል በሚባል ጋዜጠኛ ለመጀመሪያ የተጠቆመውን ማለትም ማዳጋስካርን “የአይሁዶች አገር” ይደረግ የሚለውን ሐሣብ፤ በ ጀርመንናዚው የፕሮፓጋንዳ ሚኒስቴር ኸርማን ገሪንግ ዕቅድ አቀረበ።
  • ፲፱፻፸፭ ዓ.ም. - በፖሎኝ በገዢው የኮሙኒስት ፓርቲ “ህገ ወጥ” ተብሎ የታገደው የ “ሶሊዳሪቲ” ቡድን (Solidarity Party) መሪ የነበረው፣ በኋላ የአገሪቱ ፕሬዚደንት የሆነው ሌክ ቫሌሳ ከአሥራ አንድ ወራት እሥራት በኋላ ተፈታ።

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ኅዳር 4 ኅዳር ፭


Chuck Kennedy - The Official White House Photostream - P060409CK-0199 (pd).jpg

ኅዳር ፮


  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በድርቅ የተጎዳው የኦጋዴን አጥቢያ ጉዳት ከወሎው የረኃብ ዕልቂት የበለጠ ጉዳት ሊያደርስ እንደሚችል ተገለጸ።
Hu Jintao.jpg

ኅዳር ፰

  • ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - ፲፩ ነጥብ ፬ ‘ሜጋዋት’ የሚያመነጨው የጢስ እሳት መብራት ኃይል ማመንጫ በዚህ ዕለት ተመርቆ ሥራ ላይ ዋለ።

ኅዳር ፱

CristobalColon.jpg

ኅዳር ፲

Sahle Selassie Treaty.JPG
  • ፲፱፻፲ ዓ/ም - አገሯን በጠቅላይ ሚኒስቴርነት ከአሥራ አምስት ዓመት በላይ ያገለገለችው ኢንዲራ ጋንዲ አላሀባድ በሚባል ሥፍራ ተወለደች።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የቀድሞ ባለ-ሥልጣናትን በሙስና እና የአስተዳደር ጉድለት ወንጀል በሕግ ለመመርመር የተሠየሙትን ሁለት ልዩ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶች ሕጋዊ የሚያደርገው አዋጅ ቁጥር ፯ በኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) ይፋ ተደረገ።

ኅዳር ፲፩ ቀን

Paulos GnoGno.jpg
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በአስተዳደር ጥፋት እና በሙስና ወንጀል ተከሰው በልዩ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የቀረቡትን የቀድሞ ባለ-ሥልጣናት መመርመሪያ እንዲሆን የተዘጋጀው አዲስ ሕግ በነጋሪት ጋዜጣ አዋጅ ቁጥር ፰ ታውጆ ወጣ። ይህ ድንጋጌ ባ፲፱፻፵፱ ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ላይ ተጨማሪ ነው።

ኅዳር ፲፪

Boutros Boutros-Ghali in Davos.JPG
Tutanchamon (js) 3detalle.jpg
  • ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት በቅርብ ነፃነቷን ክተቀዳጀችው የናይጄሪያ መንግሥት ጋር የአምባሳዶር ሏጥ እንደሚያደርጉ ይፋ አደረገ።
  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በዳላስቴክሳስ ሠላሳ አምሥተኛው የአሜሪካ ፕሬዚደንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በጠመንጃ ጥይት ተገድለው ሞቱ። በሚጓዙበት ተሽከርካሪ ውስጥ አብረዋቸው የነበሩትም የቴክሳስ ገዥ ጆን ኮናሊ በጥይት ተመተው ቆስለው ነበር። በዚህም ታሪካዊ ድርጊት የተወነጀለው ሊ ሃርቪ ኦዝዋልድ ተይዞ በቁጥጥር ሥር ሆነ። የዚያኑ ዕለት ምክትል ፕሬዚደንቱ ሊንደን ቢ ጆንሰን ሠላሳ ስድስተኛው ፕሬዚደንት ሆነው የመሀላ ሥርዐታቸውን በመፈጸም ስልጣኑን ተቀበሉ።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የቀድሞው የማዕድን ሚኒስትር አቶ ተሾመ ገብረ ማርያም በኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) ታሰሩ።
  • ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - በናይጄሪያ በወቅቱ ሊካሄድ በታቀደው ከ”ወይዘሪት ዓለም” የቁንጅና ውድድር ጋር በተያያዘ ጉርምርምታ መነሻነት “ThisDay” በተባለ የናይጄሪያ ጋዜጣ ላይ የወጣው ‘ሐይማኖት ነክ’ አንቀጽ ባስከተለው ሽብር ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። ውድድሩም በዚሁ ሽብር ምክንያት ወደ ለንደን ተዛወረ።
  • ፲፱፻፺፯ ዓ/ም - በዩክራይን የተካሄደውን የፕሬዚደንታዊ ምርጫ ሕዝቡ ትልቅ ጭብርብርነት ተፈጽሟል በሚል መነሻነት፣ በብዙ አሥራት ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች፣ የዕጩዋቸውን፣ የቪክቶር ዩሽቼንኮን ስም እየጠሩ የኪዬቭን ከተማ አጥለቀለቋት። ይሄውም የተቃውሞ ሰልፍ “የብርቱካን አብዮት” (Orange Revolution) ተብሎ የተሰየመውን ቅስቀሳ የተጀመረበት ዕለት ነው።
Ellen Johnson-Sirleaf, April 2010.jpg

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ኅዳር 15

AlfredNobel adjusted.jpg

፲፰፻፷ ዓ.ም. የስዌድ ተወላጁ አልፍሬድ ኖቤልዲናሚት ፈጠራውን የባለቤትነቱን መብት አስመዘገበ።

፲፱፻፶፮ ዓ.ም. በዳላስቴክሳስ ላይ በሰው እጅ የተገደሉት ሠላሣ አምሥተኛው የአሜሪካ ፕሬዚደንት ጆን ኤፍ ኬኔዲአርሊንግተን ብሔራዊ መቃብር በታላቅ ሥነ ስርዐት ተቀበሩ። በዚሁም የቀብር ስርዐት ለመሳተፍ ከዓለም ዙሪያ ብዙ መሪዎች መጥተው ነበር። ከነዚህም መሃል የፈረንሳይ ፕሬዚደንት ሻርል ደ ጎል፤ የአየርላንድ ፕሬዚደንት ደ ቫሌራ፤ የምዕራብ ጀርመን ቻንስለር ኤርሃርድና የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ይገኙበት ነበር።

፲፱፻፸፯ ዓ.ም. በኢትዮጵያ ውስጥ ለተከሰተው ታላቁ ድርቅና ረሐብ እርዳታ እንዲሆን በብሪታንያ ሠላሣ ስድስት የሙዚቃ ባለሙያዎች “ባንድ ኤይድ” በሚል ስም ተሰባስበው፤ “የክርስቶስ ልደት መሆኑን ያውቁታል ወይ?” (Do They Know It's Christmas) የተባለውን ዘፈን ቀረጹ።

፲፱፻፸፱ ዓ.ም. በአሜሪካ የ”ኢራን ኮንትራ አፌር” የተባለው የፖለቲካ ቅሌት ፈነዳ። ፕሬዚደንቱ ሮናልድ ሬጋን እና አቃቤ ሕጉ በስልጣን የነበሩ ሽርከኞች በምስጢር ለኢራን የጦር መሣሪያ እየሸጡ የሚገኘውን ትርፍ ደግሞ ለኒካራጓ ሽብርተኞች በምስጢር እንዳስተላለፉ ይፋ አደረጉ። ሁለት ባለሥልጣናት ወዲያው እንደተሻሩም ፕሬዚደንቱ ገለጹ።

፲፱፻፹፭ ዓ.ም. የቼኮስሎቫኪያ ፌዴራላዊ ሸንጎ አገሪቱ ከሚቀጥለው የአውሮፓውያን ዘመን መግቢያ ጀምሮ ለሁለት እንድትከፈል ደነገገ። ይሄም የአሁኖቹን የቼክ ሪፑብሊክ እና ስሎቫኪያ ሉዐላዊ አገሮችን የፈጠረው ድርጊት ነው።

፲፯፻፹፪ ዓ.ም. የአሜሪካን ሕገ መንግሥት መቋቋም በማስታወስ እግዚአብሔርን ማመስገኛ ብሔራዊ በዓል በፕሬዚደንቱ ጆርጅ ዋሽንግተን አሳሳቢነት በኮንግረስ የጸደቀ ህግ ተደነገገ።

፲፱፻፴፬ ዓ.ም. የአሜሪካ ፕሬዚደንት ፍራንክሊን ዲ ሩዝቬልት በአውሮፓውያን አቆጣጠር የኅዳር ወር አራተኛው ሐሙስ እግዚአብሔርን ማመስገኛ ብሔራዊ በዓል እንዲሆን የሚያስገድደውን ህግ ፈርሙ።

፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ሃማጉይር በሚባል የሠሐራ በረሀ ሥፍራ ላይ፣ ፈረንሳይ ለመጀመሪያ ጊዜ የጠረፍ መንዂራኩር ተኮሰች።

Aérospatiale-BAC Concorde taking off evening.jpg

፲፱፻፺፮ ዓ.ም. ኮንኮርድ የተባለው ዓየር-ዠበብ ተሽከርካሪ ለመጨረሻ ጊዜ በረረ። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም የፋሺስት ኢጣልያን የመጨረሻውን ይዞታ ጎንደርን ለማስለቀቅ አባቶቻችን አርበኞች ከእንግሊዝ ሠራዊት ጋር በከተማዋ ዙሪያ ውጊያቸውን ጀመሩ። በዚሁ ዕለት ጄኔራል ናሲ ከነሠራዊቱ እጁን ሰጥቶ የአገራችን ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማፋሲለደስ ግንብ ላይ ተውለበለበ። በታሪክ መዝገብ የድል ቀን ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፬፻፴፫ዓ/ም ቢባልም ኢትዮጵያ ከፋሺስቶች የተላቀቀችበት ዕለት ግን ኅዳር ፲፰ ቀን ፲፱፻፴፬ ዓ/ም ነው።

፲፱፻፴፭ ዓ.ም. በከፊል በናዚ ጀርመን ቁጥጥር ስር፤ በከፊል ደግሞ በጀርመን ደጋፊው የቪሺ አስተዳደር ስር የነበረችው የፈረንሳይ የባሕር ኃይል ቱሎን ወደብ ላይ የተሰበሰቡትን መርከቦቿን፣ በናዚዎች ቁጥጥር ስር እንዳይውሉ አሰመጧቸው።

፲፱፻፶፯ ዓ.ም. የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጃዋሃርላል ኔህሩ አሜሪካ እና የሶቪዬት ሕብረት የኑክሊዬር መሣሪያዎችን መፈተሻቸውን እንዲያቆሙና እንዲያውም ያላቸውን የኑክሊዬር መሣሪያዎች እንዲያጠፉ አቤቱታቸውን አቀረቡ።

፲፱፻፷፫ ዓ.ም. የካቶሊክ ጳጳስ ጳውሎስ ስድስተኛ ለጉብኝት ፊሊፒን አገር ሲደርሱ በማኒላ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ የቄስ ልብስ የለበሰና ጩቤ የያዘ የቦሊቪያ ተወላጅ፣ ጳጳሱን በመውጋት አቆሰላቸው።

፲፱፻፹፫ ዓ.ም. በብሪታንያወግ አጥባቂ (Conservative party) ፓርቲ መሪዋንና የአገሪቷን ጠቅላይ ሚኒስቴር ማርጋሬት ታቸርን ከሥልጣን ካወረደ በኋላ ተተኪ እንዲሆኑ ጆን ሜጀርን የቡድኑ መሪ አድርጎ መረጣቸው። ፲፭፻፲፫ ዓ.ም. በፈርዲናንድ ማጄላን መሪነት የተቀናጁ ሦሥት የፖርቱጋል መርከቦች በደቡብ አሜሪካ ደቡባዊ ጫፍ የባሕር መስመር አልፈው ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ወደ ሰላማዊ ውቅያኖስ በመሸጋገር የመጀመሪያዎቹ አውሮፓውያን ሆኑ።

፲፰፻፴፮ ዓ.ም. በሐዋይ ደሴቶች የነጻነት ዕለት ነው። የብሪታንያ እና የፈረንሳይ መንግሥታት የሐዋይን ደሴቶች ንጉዛት (ንጉሣዊ + ግዛት)ሉዐላዊነት አወቁ፣ አከበሩ።

  • ፲፰፻፵፭ ዓ/ም - የደጅ አዝማች ካሣ (በኋላ ዓፄ ቴዎድሮስ)ሠራዊትና የጎጃሙ የደጅ አዝማች ጎሹ ተከታዮች ጉራምባ ላይ ተዋግተው ድሉ የደጅ አዝማች ካሣ ሆነ። ደጅ አዝማች ጎሹም በነፍጥ ተመተው ሞቱ።

፲፱፻፭ ዓ.ም. አልባኒያኦቶማን ግዛትነት ነጻነቷን አወጀች።

፲፱፻፴፮ ዓ.ም. የአሜሪካው ፕሬዚደንት ፍራንክሊን ሩዝቬልት፣ የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስቴር ዊንስተን ቸርቺል እና የሶቪዬት ሕብረት መሪ ጆሴፍ ስታሊን ኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ላይ ተገናኝተው ከናዚ ጀርመን ጋር ለሚያካሂዱት ጦርነት የሕብረት ስልት አውጥተው፣ ተስማምተው ተለያዩ።

፲፱፻፶፩ ዓ.ም. ቅኝ ግዛቶች የነበሩት ቻድ፣ የኮንጎ ሪፑብሊክ እና ጋቦንፈረንሳይ ቤተሰብ ስር እራሳቸውን ማስተዳደር ጀመሩ።

፲፱፻፶፫ ዓ.ም. ሞሪታንያፈረንሳይ ቅኝ ግዛትነት ነጻነቷን ተቀዳጀች።

፲፱፻፷፰ ዓ.ም. የፖርቱጋል ቅኝ ግዛት የነበረችው ምሥራቅ ጢሞር፣ ገዥዋ ስትተዋት የራሷን ነጻነት አወጀች። ከዘጠኝ ቀናት በኋላ ግን በኢንዶኔዚያ ሠራዊቶች ተወራ የኢንዶኔዚያ ሃያ ሰባተኛ አውራጃ ሆነች።

፲፱፻፹፫ ዓ.ም. በብሪታንያ “ኮንሰርቫቲቭ” የቀኝ ፖለቲካዊ ቡድን መሪ የነበረችው ማርጋሬት ታቸር ከመሪነቷ ካስወገዷት በኋላ የጠቅላይ ሚኒስቴርነቱን ስልጣን ለአገሪቷ ንግሥት ዳግማዊት ኤልሳቤጥ አስረከበች። ከአሥራ አምሥት ደቂቃ በኋላ ንግሥቲቱ አዲሱን የ”ኮንሰርቫቲቭ” ቡድን መሪ ጆን ሜጀርን አቅርባ፣ አዲስ አስተዳደር በጠቅላይ ሚኒስቴርነት እንዲመራ ሾመችው። ፲፯፻፸፬ ዓ.ም. በሊቨርፑልብሪታንያ ከተማ የተመዘገበ የአፍሪቃ ሰዎችን በግዳጅ ለአገልግሎት የሚሸጥ ድርጅት ንብረት የነበረችው “ዞንግ” የምትባለው መርከብ ከጫነቻቸው ሰዎች መቶ ሠላሳ ሦሥቱን አፍሪቃውያኖች መርከበኞቹ በሕይወት እያሉ ወደ ባሕር ጥለው ገደሏቸው። በአሥራ ስምንተኛው ክፍለ ዘመን ለባርነት የሚጫኑ የአፍሪቃ ዜጎች በአውሮፓ ሕግ ፊት እንደ ዕቃ ንብረት እንጂ እንደ ሰው ስለማይቆጠሩ፣ ይሄንን ታላቅ ወንጀል የፈጸሙት ሰዎች አልተከሰሱም። የመርከቧ ባለቤቶች ግን “ለጠፋው ንብረት’’ የዋስትና ውል የሰጣቸውን ድርጅት በፍርድ ቤት የኪሳራቸውን ዋጋ እንዲከፍላቸው ክስ አቀረቡ።

፲፰፻፳፫ ዓ.ም. በፖሎኝሩሲያን በላይነት እና አስተዳደር በመቃወም የ”ትጥቅ ትግል” ተጀመረ።

፲፱፻፵ ዓ.ም. የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፍልስጥኤምን በሐይማኖት መሠረት ለሁለት ከፍሎ አንደኛው የይሁዳዊ መንግሥት፤ ሁለተኛውን ክፍል ደግሞ የአረብ መንግሥት እንዲመሠረት የሚያስችለውን “ውሳኔ ፻፹፩” አጸደቀ። ይሄው ውሳኔ በድምጽ ሠላሣ ሦስት አገሮች ሲደግፉት፤ አሥራ ሦሥት አገሮች ተቃውመው አሥር አገሮች ደግሞ የድጋፍም የቅራኔም ድምጽ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ኢትዮጵያ እና ብሪታንያ ከነኝህ ከአሥር አገሮች መሀል ይገኛሉ።< ፲፱፻፵፮ ዓ.ም. በኡጋንዳቡጋንዳ ንጉሥ ዳግማዊ ኤድዋርድ ሙቴሳ በአገሪቱ የብሪታንያ አስተዳደሪ ‘ሰር አንድሩው ኮሄን’ ተሽረው በስደት ወደለንደን ሄዱ።

፲፱፻፶፫ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴጋናላይቤሪያቶጎብራዚልናይጄሪያ እና ካሜሩን የሚያካሂዱትን ጉብኝት ለመፈጸም ከአዲስ አበባተነሱ። ዳሩ ግን ዕቅዳቸውን ሳያጠናቅቁ በኢትዮጵያ የታኅሣሥ ግርግር መነሳት ምክንያት ጉዟቸውን አቋርጠው ይመለሳሉ።

U-Thant-10617.jpg

፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ዩ ታንትሦስተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሆነው ተመረጡ። በኮንጎ በአየር አደጋ የሞቱትን ሁለተኛውን የድርጅቱን ዋና ጸሐፊ ዳግ ሃመርሾልድን ይተካሉ።

፲፱፻፶፱ ዓ.ም. የባርባዶስ ደሴት ከብሪታንያ ነጻነቷን ተቀዳጀች።

፲፱፻፷ ዓ.ም. የየመን ሕዝባዊ ሪፑብሊክብሪታንያ ነጻነቷን ተቀዳጀች።

፲፱፻፷ ዓ.ም. በፓኪስታን በኋላ የአገሪቱ መሪ የሆኑት እና በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ወርደው በስቅለት ሞት የተቀጡት ዙልፊቃር አሊ ቡቶፓኪስታን ሕዝባዊ ፓርቲን መሠረቱ።

፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የነዳጅ ክምችቱን ለማፈንዳት የተደረገው ሙከራ ከሽፏል

፲፱፻፺፰ ዓ.ም. በካምፓላ ኡጋንዳ የተወለዱት ጆን ታከር ሙጋቢ ሴንታሙ ዘጠና ሰባተኛው የዮርክ ሊቀ ጳጳስ ሆኑ። በዚህ ቤተ ክርስቲያን ይሄንን ታላቅ ሥልጣን የተቀበሉት የመጀመሪያው ጥቁር ጳጳስ ናቸው። ፲፱፻፵፰ ዓ.ም. በአላባማ ግዛት ውስጥ በሞንትገመሪ ከተማ፣ ልብስ ሰፊዋ ሮዛ ፓርክስ ወጥቶ እብስ ላይ መቀመጫዋን፣ (በወቅቱ ዘረኛ የከተማዋ ሕግ መሠረት)፣ ለነጭ ሰው አልለቅም በማለቷ የ”ሞንትገመሪ ወጥቶ እብስ አድማ” ተከሰተ።

፲፱፻፶፩ ዓ.ም. የፈረንሳይ ቅኝ ግዛት የነበረችው የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ በዛሬው ዕለት ነጻነቷን ተቀዳጀች።

፲፱፻፹፫ ዓ.ም. በእንግሊዝ ባህር ስር በብሪታንያ እና በፈረንሳይ አገሮች መካከል የውስጠ መሬት የባቡር መሥመር የተመሠረተበት ቡርቦራ ከባሕሩ በታች አርባ ሜትር ጥልቀት ላይ ተገናኘ።

፲፱፻፺፬ ዓ.ም. የኢትዮጵያ አየር መንገድን የመሠረተው የአሜሪካትራንስ ወርልድ አየር መንገድ (Trans World Airlines) ከሰባ ስድስት ዓመታት አገልግሎት በኋላ በአሜሪካ አየር መንገድ (American Airlines) ተገዛ።

ኅዳር 24


Seal of Illinois.svg

፲፰፻፲፩ ዓ.ም. በመካከለኛው አሜሪካ የምትገኘው የኢሊኖይ ግዛት በሃያ አንድኛ ደረጃ ከአሜሪካ ሕብረት ጋር ተዋሃደች።

፲፱፻፷ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪቃ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶክቶር ክርስቲያን ባርናርድ የመጀመሪያው የሰው ልብ በ ’ቀዶ ጥገና’ ጥበብ ከሟቹ ‘ዴኒስ ዳርቫል’ ወደተቀባዩ የልብ በሽተኛ ‘ሌዊስ ዋሽካንስኪ’ አጠናቀቁ።

፲፱፻፷፱ ዓ.ም. በጃማይካ የ’ሬጌ’ ሙዚቃ ባላባት ቦብ ማርሌይ ላይ የገደላ ሙከራ ተደረገ። በሁለት ጥይቶች ቢመታም ማርሌይ ከሁለት ቀን በኋላ መድረክ ላይ ወጣ።

፲፱፻፸፬ ዓ.ም. ሕንድ አገር ውስጥ በቦፓል ከተማ ፥ የአሜሪካዩኒየን ካርባይድ ( Union Carbide) የኬሚካል ኩባንያ ውስጥ በተከሰተው አደጋ መርዛዊ ኬሚካል አየሩን በክሎት ሦስት ሺህ ስምንት መቶ ሰዎች ሲሞቱ እስከ ስድስት መቶ ሺህ ሰዎች በአደጋው ምክንያት ጤናቸው እንደተበላሸ ይገመታል። ፲፭፻፷ ዓ/ም - የዓፄ ልብነድንግል ሚስት እቴጌ ሰብለ ወንጌል በዚህ ዕለት አመድ በር በምትባል ሥፍራ አረፉ።

፲፮፻፲፪ ዓ.ም. ሠላሣ ስምንት ከብሪታንያ የመጡ አቅኝዎች ቨርጂኒያ ላይ አርፈው ለ እግዚአብሔር ምስጋናቸውን አቀረቡ። ይሄም ድርጊት በአሜሪካ የመጀመሪያው የምሥጋና ሰርዐት ዕለት ነበር ይባላል።

The-Observer-first-issue-001.jpg

፲፯፻፹፬ ዓ.ም. በዓለም የመጀመሪያው የ’ዕሑድ ጋዜጣ’ የብሪታንያው ‘ኦብዘርቨር’ ‘The Observer’ የተባለው ጋዜጣ የመጀመሪያው ዕትም ወጣ።

፲፱፻፴፰ ዓ.ም. በአሜሪካ የሕዝብ እንደራሴዎች ‘United States Senate’ አባላት በስድሳ አምሥት ለ ሰባት ድምጽ አሜሪካ ጥቅምት ፲፬ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. የተመሠረተው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓባል እንድትሆን አጸደቁ።

፲፱፻፶፩ ዓ.ም. የቀድሞዋ ዳሆሚ የዛሬዪቷ ቤኒንፈረንሳይ ቁጥጥር ውጭ ዕራሷን በራሷ የመግዛት ስርዐት ጀመረች።

፲፱፻፶፬ ዓ.ም. የብሪታንያ መንግሥት ለሴቶች ዜጋዎቹ የ’ጽንሰት መከላከያ’ መድሐኒት በብሔራዊ የጤና ጥበቃ አገልግሎት በነጻ መቀበል እንዲችሉ አደርገ።

፲፱፻፸ ዓ.ም. የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ፕሬዚደንት ጃን ቤደል ቦካሳ ዕራሳቸውን በራሳቸው ቀዳማዊ ቦካሳ በሚል ስም በማንገሥ የአገሪቱም ስም ተቀይሮ ‘የመካከለኛው አፍሪካ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት’ በሚል ስም ተሰየመች።

፲፱፻፹፬ ዓ.ም. የፓን አሜሪካ አየር መንገድ ከ ስድሳ አራት ዓመታት አገልግሎት በኋላ አከተመ።

፲፱፻፹፭ ዓ.ም. በሶማሊያ አገር ውስጥ በተከሰተው የ’ዕርስ በርስ ጦርነት’ የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጆርጅ ኸርበርት ዎከር ቡሽ የ’ሰብዓዊ ርሕራሔ’ ምክንያት በሚል መነሻ ሃያ ስምንት ሺህ የአሜሪካ ወታደሮችን ወደ ሶማሊያ ላኩ።

Haddis alemayehu.jpg

፲፯፻፹፫ ዓ.ም. የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትኒው ዮርክ ከተማ ወደ ፊላዴልፊያ ከተማ ተዛወረ።

፲፰፻፺ ዓ.ም. በዓለም የታክሲዎችን አገልግሎት በ ሕጋዊ ረገድ በማስተናገድ ሎንዶን ከተማ የመጀመሪያዋ ሆነች።

፲፱፻፶ ዓ.ም. አሜሪካ ወደጠረፍ መንኲራኩር ለመተኮስ የመጀመሪያ ሙከራዋ በኬፕ ካናቨራል ከሸፈ።

፲፱፻፺፩ ዓ.ም. በቬኔዙዌላ አገር ወታደራዊው መኮንን ሁጎ ሻቬዝ ፍሪያስ በፕሬዚደንትነት ተመረጠ። ፲፱፻፴፬ ዓ.ም. የጃፓን ንጉሠ ነገሥት የባሕር ኃይልአሜሪካንን የሰላማዊ ውቅያኖስ የባሕር ኃይል እና አብሮ የተሰለፈውን የጦር ኃይል በ ሃዋይ ደሴቶች ላይ ባለችው ፐርል ሃርበር ‘Pearl Harbour’ በተሰኘችው ወደብ ላይ እንዳሉ ከፍተኛ አደጋ ጥላባቸው አሜሪካን የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ውስጥ እንድትገባ የገፋፋትን ታሪካዊ ሁኔታ ከሰተች።

፲፱፻፸፪ ዓ.ም. በሮዴዥያ የሽግግር መንግሥትን እንዲያስተዳድሩ የተመረጡት የዊንስተን ቸርችል አማች የነበሩት እንግሊዛዊው ‘ሎርድ ሶምስ’ (Lord Soames) እጩነታቸው ይፋ ተደረገ።

፲፱፻፹፮ ዓ.ም. አገራቸውን አይቮሪ ኮስትን ከፈረንሳይ ነጻነቷን ከተቀዳጀችበት ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ በፕሬዚደንትነት የመሩት ፊሊክስ ሁፌ ቧኜ በተወለዱ በ ሰማንያ ስምንት ዓመታቸው አረፉ።

Artwork Galileo-Io-Jupiter.JPG

፲፱፻፹፰ ዓ.ም. የአሜሪካ የጠረፍ መንኲራኩር ‘ጋሊሌዎ’ ከምድር በተተኮሰች በስድስት ዓመቷ ጁፒተር ዘንድ ደረሰች። ፲፱፻፲፰ ዓ/ም ጥቁር አሜሪካዊው ዘፋኝ፤ ዳንሰኛ እና የፊልም ተዋናይ ሳሚ ዴቪስ ጁንየርበዚህ ዕለት ተወለደ።

፲፱፻፴፬ ዓ/ም የጃፓን ዓየር ኃይል በሃዋይፐርል ሀርበርን ወደብ ባጠቃ በማግሥቱ የአሜሪካ የሕዝብ ምክር ቤት አባላት በጃፓን ላይ የጦርነት አዋጅ አወጁ።

፲፱፻፸፩ ዓ/ም በአሁኑ ጊዜ በየመን ለአል ሳቅር ቡድን የሚጫወተው ኢትዮጵያዊው የእግር ኳስ ተጫዋች አንዋር ሲራጅየልደቱ ቀን ነው።

፲፱፻፸፫ ዓ/ም በኒው ዮርክ ከተማ የቀድሞው የቢትልስ መሥራችና ዓባል ጆን ሌነን መኖሪያ ቤቱ ፊት ለፊት ላይ ‘ማርክ ዴቪድ ቻፕማን’ በተባለ ሰው በሽጉጥ ተገደለ። ፲፰፻፵፰ ዓ/ም የሸዋው ንጉሥ እና የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አባት ንጉሥ ኃይለ መለኮት በኃይል ሊያስገብሯቸው ከመጡት ከዓፄ ቴዎድሮስ ጋር ለጦርነት ሲዘጋጁ በድንገት ታመው አረፉ።

፲፰፻፸፭ ዓ/ም በሉዊዚያና ግዛት ‘ ፒ. ቢ. ኤስ. ፒንችባክ’ የመጀመሪያው ጥቁር አሜሪካዊ ገዥ ሆነ ።

፲፰፻፺፰ ዓ/ም በፈረንሳይ መንግሥትን እና ቤተ ክርስቲያንን የሚለየው ህግ ጸደቀ።

፲፱፻፶፬ ዓ/ም የቀድሞዋ ታንጋኒካብሪታንያ ነጻነቷን ተቀዳጀች። ከነጻነት በኋላ በ፲፱፻፶፯ ዓ/ም ታንጋኒካዛንዚባር ጋር ተዋሕዳ የዛሬይቱን የታንዛኒያ ሪፑብሊክ መሠረቱ።

፲፱፻፹፫ ዓ/ም በፖሎኝ አገር ሌክ ቫሌሳ የመጀመሪያው በሕዝብ የተመረጠ ፕሬዚደንት ሆነ ።

፳፻፩ ዓ/ም በአሜሪካኢሊኖይ ገዥ ሮድ ብላጎዬቪች በብዙ ወንጀሎች ተከሶ በፌዴራል ህግ አስከባሪዎች ተያዘ። ፈጽሟል ከተባሉት ወንጀሎች አንዱ በፕሬዚደንትነት የተመረጡትን የባራክ ኦባማን የእንደራሴዎች ምክር ቤት (United States Senate) አባልነት በገንዘብ ሊሸጥ ሞክሯል በመባል ነው ።

[ለማስተካከል] ታኅሣሥ

ታኅሣሥ ፩ ቀን

  • ፲፰፻፷፩ ዓ/ም - በዓለም የመጀመሪያው የመንገድ ተሽከርካሪዎች መቆጣጠሪያ መብራት በእንግሊዝ ዋና ከተማ በለንደን ላይ የፓርላማ ሕንጻ (የዌስትሚንስተር ቤተ መንግሥት) ‘Palace of Westminster’ ፊት ለፊት ተተክሎ አገልግሎት ላይ ዋለ።
  • ፲፱፻፸፬ ዓ/ም - የብሪታንያቢ.ቢ.ሲ.አሜሪካ አሥራ አምሥት ግዛቶች ውስጥ ‘ሰዶማውያን’ን የሚያጠቃ ያልታወቀ አዲስ በሽታ እንደገባ እና በእነኚሁ ግዛቶች ውስጥ ሰባ አምሥት ሰዎች፥ በእንግሊዝ አገር ደግሞ አንድ ሰው በዚሁ በሽታ መሞታቸውን ዘገበ። ይሄ በሽታ በኋላ ኤይድስ የተባለው በሽታ ሲሆን ሠላሣ ዓመታት እንኳን ባልሞላ ጊዜ ውስት በዓለም ላይ ወደ ሃያ አራት ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ሕይወት ወስዷል።
  • ፲፱፻፹፩ ዓ/ም -በቀድሞው የሶቪዬት ሕብረት ግዛት ውስጥ በአርሜኒያ ክልል ውስጥ በተከሰተው የምድር እንቅጥቅጥ አርባ አምሥት ሺህ ሰዎች ሲሞቱ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ መኖሪያ ቤታቸውን አጥተዋል። ስፒታክ የምትባል የሃያ አምሥት ሺህ ነዋሪዎች ከተማ በዚሁ እንቅጥቅጥ ፈጽማ ወድማለች።

ታኅሣሥ ፪ ቀን

A solzhenitsin1.jpg
  • ፲፱፻፲፩ ዓ/ም - የሩሲያው ተወላጅና የሥነ ጽሑፍ ሰው አሌክሳንደር ሶልዤኒትሲን በዛሬው ዕለት በኪስሎቮድስክ ተወለደ። ሶልዤኒትሲን በስታሊን ዘመን አድሀሪ በመባል ተወንጅሎ በሳይቤሪያ ግዛት ውስጥ በእሥራትና በግዞት በነበረበት ወቅት የጻፈው “የጉላግ አርቺፒላጎ” በተባለው ድርሰቱ በዓለም ታዋቂነትን ያተረፈ ጸሐፊ ነበር።
CheHigh.jpg

ታኅሣሥ ፫ ቀን

Menelik II - 4.jpg

ይቺ ዕለት በኢትዮጵያ ታሪክ ሁነኛ ስፍራ አላት። ታላቁ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክና የጦሩ ፊታውራሪ፣ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ ያረፉበት ዕለት ናት፡፡ ዕለቱ ተመሳሳይ ይሁን እንጂ ሁለቱ ያረፉት በተለያዩ ዓመታት ነው፡፡ ‹‹አባ ዳኘው›› የተባሉት፣ ዳግማዊ ምኒልክ ፳ኛው ምዕት ዓመት በባተ በስድስተኛው ዓመት ላይ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. ሲያርፉ ‹‹አባ መላ›› የተሰኙት ፊታወራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ደግሞ በ፲፱፻፲፱ ዓ.ም. አርፈዋል። ዓመታቱ ይለያዩ እንጂ ሁለቱም ያረፉት ዓርብ ታኅሣሥ ፫ ቀን ነበር፡፡

H E Fitawrari Habte Giyorgis Dinegde.jpg
  • ፲፱፻፰ ዓ/ም - የቻይና ሪፑብሊክ ፕሬዚደንት አገሪቱን ወደንጉዛት ሥርዐት መመለሳቸውንና እራሳቸውንም ንጉሠ ነገሥት ማድረጋቸውን አወጁ።

ታኅሣሥ ፬ ቀን

Mengistu and germame Neway.jpg
  • ፲፱፻፹፫ ዓ/ም - በሲሲሊ ደሴት ላይ የተከሰተው ትልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ የአሥራ ስምንት ሰዎችን ሕይወት አጠፋ።

ታኅሣሥ ፭ ቀን

  • ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - በወንድማማቾች መንግሥቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ የተሰነጸጸው የታኅሣሥ ግርግር መፈንቅለ መንግሥት ዓላማውን ይፋ አደረገ። አብሮም የለውጥ ፈላጊ ናቸው የሚባሉትን ልዑል ራስ እምሩ ኃይለ ሥላሴን በጠቅላይ ሚኒስትርነት መሾማቸውንና አልጋ ወራሹን አስፋ ወሰንን (“አስገድደው”) በማስማማትም መንግሥት በቆረጠላቸው ደመወዝ እየተዳደሩ ለሕገ መንግሥት የሚገዙ ንጉሥ ሆነው እንደሚያገለግሉ እራሳቸው ለሕዝቡ በራዲዮ እንዲያስተላልፉ አደረጉ።
Dick Tiger.jpeg
  • ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - ዲክ ታይገር (ሪቻርድ ኢሄቱ) የሚባለው ናይጄሪያዊ ቦክሰኛ በተወለደ በ ፵፪ ዓመቱ በጉበት ነቀርሳ ምክንያት አረፈ። ዲክ ታይገር የባያፍራን የመገንጠል ሙከራ ደጋፊ ነው በሚል ወደአገሩ እንዳይመለስ ተከልክሎ በስደት አሜሪካ ይኖር ነበር።

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 6 ታኅሣሥ ፯ ቀን

  • ፲፱፻፷፪ ዓ/ም የብሪታንያ የሕዝብ ተወካዮች ሸንጎ የነፍሰ ገዳዮችን የሞት ቅጣት በህግ ሰረዘ።
  • ፲፱፻፶፫ ዓ/ም በወንድማማቾች መንግሥቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ የተሰነጸጸው የታኅሣሥ ግርግር መፈንቅለ መንግሥት ኃይል እየተዳከመ በአንጻሩ ደግሞ ተቃዋሚዎቻቸው እያደር እየጎለመሱ መሄዳቸውን የተገነዘቡት ሽብርተኞች በቁጥጥራቸው ላይ የነበሩትን ሃያ መሳፍንት፣ መኳንንት፣ ሚኒስትሮችንና መኮንኖችን ወደ አረንጓዴ ሳሎን ያዛውሩና አልጋወራሹንና አዲሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ለብቻቸው እንዲጠበቁ ያደርጋሉ። ጄነራል ጽጌ ዲቡ ወዲያው ከተቃራኒ ወገን በተተኮሰ ጥይት ሲገደሉ፣ እነ ጄነራል መንግሥቱ የያዟቸውን እስረኞት ረሽነው ለማምለጥ ወስነው ሜጄር ጄኔራል ሙሉጌታ ቡሊ፤ ራስስዩም መንገሻ፤ ራስ አበበ አረጋይ፤ አቶ መኮንን ሀብተወልድአባ ሐና ጅማ፤ በጠቅላላው አሥራ አምስት ሰዎች ተረሽነው ሞቱ። የክብር ዘበኛ መኮንን የነበሩት ሻምበል ደረጀ ኃይለ ማርያም ሽብርተኞቹን በመቃወም የቤተ መንግሥቱን አጥር በታንክ ደምስሰው ሲገቡ ከሽብርተኞት ወገን በተተኮሰ ጥይት ተገደሉ። ሻምበል ደረጀ የስመ ጥሩው አርበኛ የኃይለ ማርያም ማሞ ልጅ እና የንጉሠ ነገሥቱ የልጅ ልጅ የልዕልት ሶፊያ ደስታ ባል ነበሩ።
  • ፳፻፫ ዓ/ም የኢትዮጵያና የቅዱስ ጊዮርጊስ ቡድኖች እግር ኳስ ተጫዋችና አሰልጣኝ የነበረው በኩሩና ኮከቡ መንግሥቱ ወርቁ፣ በ፸ ዓመቱ አረፈ። መንግሥቱ ወርቁ በስድስት የአፍሪካ ዋንጫዎች የፍጻሜ ግጥሚያዎች የተሳተፈ ሲሆን፣ በ፫ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ግብፅን ፬ ለ ፪ አሸንፋ ዋንጫ እንድታገኝ ሁለቱን ግቦች ያስቆጠረና በዚሁ በ፫ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ፫ ግብ በማስቆጠሩም የኮከብ ግብ አግቢነት ክብር አግኝቷል፡፡
Mr. Kofi Annan.jpg

ታኅሣሥ ፱ ቀን

Jules rimet.jpg

ተሰረቀ። ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 10 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 11 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 12 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 13 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 14 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 15 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 16 ታኅሣሥ ፲፯

  • ፲፱፻፹ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ባዘጋጀችው የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ የእግር ኳስ ዋንጫ (ሴካፋ) ዚምባብዌን በፍጹም ቅጣት ምት በማሸነፍ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን ከፍ ያደረገችበት ነበር፡፡ ዋንጫውን ለብሔራዊ ቡድኑ አምበል ገብረ መድኅን ኃይሌ የሰጡት የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢሕዲሪ) ፕሬዚዳንት፣ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ሲሆኑ፣ የተሰማቸውን ደስታ የገለጹት ፻ ሺሕ ተመልካች የሚይዝ ስታዲየም ለመሥራት ቃል በመግባት ነበር፡፡
  • ፳፻ ዓ/ም - በኬንያ የፕሬዚደንታዊ ምርጫ ምዋይ ኪባኪ አሸናፊ ናቸው ተብሎ ሲታወጅ በመላ አገሪቱ የተከተለው የተቃውሞ ረብሻ በአገሪቱ ለተከሰቱት ፖለቲካዊ፤ ምጣኔ-ኃብት እና ሰብዓዊ ነውጦች ዋና መንስዔ ሆኗል።
Derg emblem.png

ታኅሣሥ ፲፱

  • ፳፻፩ ዓ/ም - በሶማሊያ የሥልጣን ትግል ውጊያ የአገሪቱ ጊዜያዊ ፌዴራላዊ መንግሥት ሠራዊት እና አጋሮቻቸው የኢትዮጵያ ወራሪ ኃይል የሞቃዲሹን ከተማ በቁጥጥራቸው ሥር አዋሉ።

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 20 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 21 ታኅሣሥ ፳፪

  • ፲፱፻፹፭ ዓ/ም - የቀድሞዋ ቼኮዝሎቫኪያ በሰላማዊ ስምምነት ለሁለት ተከፍላ የቼክ ሪፑብሊክ እና ስሎቫኪያ በተባሉ ሉዐላዊ አገራት ተተካች። መገናኛ ብዙሀን ይሄንን ከፈላ ‘የሐር ፍች’ (Velvet Divorce) የሚል ሥያሜ ሰጥተውታል።

ታኅሣሥ ፳፫

  • ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ባንኮችንና የኢንሹራንቸ ኩባንያዎችን የብሔራዊ ንብረት አድርጎ ወረሰ።
Kofi Annan.jpg

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 24 ታኅሣሥ ፳፭ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፭ተኛው እና የመፀው ወቅት መጨረሻውና ፺ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፪፻፶፩ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፶ ቀናት ይቀራሉ። ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 26 ታኅሣሥ ፳፯ ቀን

Roentgen2.jpg
  • ፲፰፻፹፰ ዓ/ም - ዊልሄልም ሮንትገን የተባለ ጀርመናዊ፣ ኤክስሬይ ብሎ የሠየመውን ጨረር እንዳገኘ በአውስትሪያ ጋዜጣ ላይ ተዘገበ።
  • ፲፱፻፸፯ ዓ/ም - የ፳ኤል መንግሥት ‘ኦፐሬሽን ሙሴ’ በሚል ሥያሜ ኢትዮጵያውያን ፈላሻዎችን ከኅዳር ፲፪ ቀን ፲፱፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በድብቅ ወደ ፳ኤል ካጓጓዘ በኋላ የዚህ ምሥጢራዊ የአየር ውፅዓተ-ነገድ ወሬ በመሰማቱ በዛሬው ዕለት የማቆሚያ ትዕዛዝ ተላለፈ። በዚህ የስድስት ሳምንት ውፅዓት ፰ሺ ፈላሻዎች ሲሰደዱ ከ፮ ዓመት በኋላ በተደገመው ‘ኦፐሬሽን ሰሎሞን’ ደግሞ ፲፭ሺ አይሁዳዊ ኢትዮጵያውያን ወደ ፳ኤል ተሰደዋል።

ታኅሣሥ ፳፰

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች በዘመነ ዮሐንስኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ያከብራሉ። ልደትን የምታከብሩ ሁሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም ያደረሳችሁ

Saint George FC.jpg

ታኅሣሥ ፳፱

  • ፲፰፻፸፱ ዓ/ም የሸዋንጉሥ ምኒልክ ሠራዊትና የሐረሩ አሚር ዐብዱላሂ ሠራዊት በሜታ ወረዳ፣ ምሥራቅ ሐረርጌ ውስጥ በምትገኘው ጨለንቆ ላይ ገጥመው ከ፴ ደቂቃ ውጊያ በኋላ የዐሚሩ ሠራዊትተሸንፎ ወደሐረር ሸሸ። ወዲያው ሐረር በሸዋው ንጉሥ እጅ ገባች።
  • ፲፱፻፷፭ ዓ/ም የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፤ አረባዊ ነዳጅ አምራች አገሮች በወቅቱ የነዳጅ ምርታቸውን የፖለቲካ መሣሪያ በማድረጋቸው በአፍሪቃውያን አገሮች ላይ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ ለማጥናት አዲስ አበባላይ ተሰበሰቡ።

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 30

[ለማስተካከል] ጥር

ጥር ፩ ቀን

Nixon 30-0316a.jpg
Sekou Toure usgov-83-08641.jpg
  • ፲፱፻፲፬ ዓ/ም አገራቸውን ጊኒን ወደነጻነት የመሩትና የመጀመሪያው ፕሬዚደንት፣ አሕመድ ሴኩ ቱሬ በዛሬው ዕለት ተወለዱ።
  • ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ‘አፕል’ (Apple Computer Inc.) የተባለው የአሜሪካ የመቀምር ድርጅት ‘አይ ቲዩንስ’ (iTunes) የተባለውን የሙዚቃ ተሰኪ ስብስብ አካል (software) ሳን ፍራንሲስኮ ላይ አስተዋወቀ።
  • ፲፱፻፺፱ ዓ/ም ‘አፕል’ (Apple Computer Inc.) “አይ ፎን” (iPhone) የተባለውን ተንቀሳቃሽ ስልክ አስተዋወቀ።

ጥር ፪

  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የ ፬ኛ ክፍለ ጦር አባላት ነገሌ ቦረና ላይ አምጸው አለቆች መኮንኖቻቸውን በቁጥጥራቸው ስር አዋሉ።
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የሚገኘውን ሕዝብ ለመርዳትና ለማስተማር፣ የመጀመሪያዎቹ "የእድገት በኅብረት የእውቀትና የሥራ ዘመቻ" ወጣቶች ከአዲስ አበባ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ዘመቱ።

ጥር ፫

ጥር ፬ ቀን

  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በዛንዚባር ደሴት በጊዜው በሱልጣን ይመራ የነበረውን አረባዊ መንግሥት በጆን አኬሎ የሚመራ ሽብርተኛ ቡድን ፈንቅሎ የዛንዚባር ሪፑብሊክን መሠረተ።
  • ፳፻፪ ዓ/ም - በሀይቲ ደሴት ላይ ትልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ተነስቶ ፪ መቶ ፴ ሺህ ያህል ሰዎችን አጠፋ።

ጥር ፭

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ጥር 6 ጥር ፯ ቀን

ስላሴ1.JPG

ጥር ፰ ቀን፣

Hammarskjold-selassie-i.jpg

ጥር ፱ ቀን

Pompidou.jpg

ጥር ፲ ቀን፣

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች በዚህ፣ የትልቁ የጥምቀት በዓል ሥነ ሥርዓት መጀመሪያ ዕለት የአጥቢያቸውን ታቦተ ሕግ በማጀብ ወደከተራው ተጉዘው እዚያው ያድራሉ።

A380 Reveal 1.jpg
  • ፲፱፻፺፯ ዓ/ም እስከ ፭ መቶ ፳፭ መንገዶኞችን የሚያስተናግደው፣ ወደረ ቢሱ ኤየርባስ ኤ፫፻፹ (Airbus A380) የተሰኘው አየር ዠበብ በቱሉስ የፈረንሳይ ከተማ ለዓለም ተገለጸ።

ጥር ፲፩ ቀን፣

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንኢየሱስ ክርስቶስ ዓ/ም በመጥምቁ ዮሐንስእጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ የጥምቀት በዓል ነው።

Indira2.jpg
  • ፲፱፻፶፰ ዓ/ም ኢንዲራ ጋንዲሕንድየመጀመሪያዋ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተመረጡ። አባታቸው ጃዋህራል ኔህሩ የአገሪቱ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ነበሩ።
  • ፳፻፪ ዓ/ም - በምስራቅ ጎጃም ዞን በሊበን ወረዳ ልዩ ስሙ ድጓም የደረብ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ አንዲት በግ የሚዳቋና የበግ ግልገሎች ተገላገለች፡፡

ጥር ፲፪ ቀን፣

Jfk inauguration.jpg
US President Barack Obama taking his Oath of Office - 2009Jan20.jpg
  • ፳፻፩ ዓ/ም ባራክ ኦባማ የመጀመሪያው የጥቁር ክልስ አሜሪካዊና ፵፬ተኛው የአሜሪካ ፕሬዚደንት በመሆን የቃለ መሀላ ሥነሥርዓታቸውን አከናወኑ።

ጥር ፲፫ ቀን፣

Yohannesson.jpg
  • ፲፰፻፷፬ ዓ.ም.፣ ደጃዝማች ካሳ ምርጫ (አባ በዝብዝ) በአክሱም ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ስመ መንግሥታቸው "ዮሐንስ ራብዓዊ" (ዮሐንስ ፬ኛ) ተብሎ፣ በጳጳሱ በብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ እጅ ተቀብተው በሥርዓተ መንግሥት ንጉሠ ጽዮን፣ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተብለው ነገሡ። በታሪክ እንደተመዘገበው በዚሁ ንግሥ ምክንያት ሦስት ቀን በዓል ሆኖ፣ ለግብር ፬ ሺህ ሰንጋ ታርዶ፣ ፶ ጉንዶ ማር የፈጀ፣ ፻፶ ሺህ ገንቦ ጠጅ ቀርቦ፣ በደስታ ሲበላ ሲጠጣ ሰንብቷል።
CAF HISTORIC final 097.jpg
  • ፲፱፻፶፬ ዓ.ም. ኢትዮጵያ ሦስተኛውን የአፍሪቃ እግር ኳስ ውድድር የግብፅን ቡድን አራት ለ ሁለት አሸንፋ ዋንጫውን ተሸለመች። ለኢትዮጵያ ቀዳሚውን ግብ ያስቆጠረው የቴሌው ግርማ ዘለቀ ሲኾን፣ የጊዮርጊሱ መንግሥቱ ወርቁ በ፹፬ኛውና በ፻፲፯ኛው ደቂቃ ሁለተኛና አራተኛውን፣ ኢታሎ ቫሳሎ በ፻፩ኛው ደቂቃ ሦስተኛውን ለማስገባት ችለዋል። ያልተደገመውንና ሕዝቡም እየናፈቀ ያለው የአፍሪቃ ዋንጫ ለኢትዮጵያ ያስገኙት ፩. ጊላ ሚካኤል ተስፋ ማርያም ፪. ክፍሎም አርአያ ፫. አስመላሽ በርሔ ፬. በርሔ ጎይቶም ፭. አዋድ መሐመድ ፮. ተስፋዬ ገብረ መድኅን ፯. ግርማ ዘለቀ/ተክሌ ኪዳኔ ፰. መንግሥቱ ወርቁ ፱. ሉቻኖ ቫሳሎ (አምበል) ፲. ኢታሎ ቫሳሎ ፲፩. ጌታቸው ወልዴ ሲሆኑ ተጠባባቂዎች ደግሞ ጌታቸው መኩሪያ፣ እስማኤል ጊሪሌ፣ ብርሃኔ አስፋው፣ ኃይሌ ተስፋ ጋብር፣ ነፀረ ወልደሥላሴ ነበሩ። አሰልጣኞች ይድነቃቸው ተሰማ፣ ፀሐየ ባሕረና አዳሙ ዓለሙ፣ ወጌሻው ጥላሁን እሸቴ ነበሩ፡፡

ጥር ፲፬ ቀን፣

  • ፲፰፻፲፮ ዓ/ም - በቀድሞዋ 'ጎልድ ኮስት' (አሁን ጋና) የአሻንቲ ብሔረሰብ ሠራዊት የእንግሊዝን ሠራዊት በውጊያ አሸንፈው በአፍሪቃአኅጉር፣ የነጭ ቅኝ ገዥ ሠራዊትን በማሸነፍ የመጀመሪያው ብሔረሰብ ሆኑ።።
Queen Victoria by Bassano.jpg
  • ፲፱፻፷፪ ዓ/ም የቦይንግ 'ጃምቦ ጄት' በመባል የሚታወቀው ቢ ፯፻፵፯ (Boeing 747) አየር ዠበብ ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳፋሪ መንገደኞችን ጭኖ ከኒው ዮርክ ኬኔዲ አየር ጣቢያ ተነስቶ ሎንዶን ሂዝሮው አየር ጣቢያ አረፈ።

ጥር ፲፭ ቀን

  • ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - የቀድሞው የኡጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ በሲንጋፖር ላይ በሚካሄደው የጋራ ሀብት አገሮች ጉባዔ ላይ እንዳሉ በጄኔራል ኢዲ አሚን በተመራ ወታደራው መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ወረዱ።

ጥር ፲፰ ቀን

ጥር ፲፱

Dogali .jpg
  • ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ሌሊቱን በደም ቋጠሮ ምት ታመው በአስቸኳይ ወደእንግሊዝ አገር የእንግሊዝ የጦር አየር ዠበብ ለሕክምና እንዲወስዳቸው ተለመነ። የጦር አየር ዠበብ በማግሥቱ ይዟቸው ወደሎንዶን በረረ።
  • ፲፱፻፹፫ ዓ/ም - በሶማሊያ ሞሀመድ ሲያድ ባሬ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣናቸው ወረዱ።
  • ፲፱፻፸፪ ዓ/ም - በቀድሞዋ ሮዴዚያ (የአሁኗ ዚምባብዌ) የነጻነት ትግል መሪ ሮበርት ሙጋቤ ከአምስት ዓመት ስደት በኋላ አገራቸው ተመልሰው ሲገቡ እጅግ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።
  • ፲፱፻፹፰ ዓ/ም - በኒጄር ለመጀመሪያ ጊዜ በሕዝብ የተመረጡትን ፕሬዚደንት ማማን ኡስማን፣ በኮሎኔል ኢብራሂም ባሬ ማኢናሳራ የተመራ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን አወረዳቸው።
  • ፲፱፻፵ ዓ/ም - ሕንዳዊው የሰላማዊ እንቅስቃሴ መሪ ማሀትማ ጋንዲ (Mohandas Karamchand Gandhi} በነፍሰ ገዳይ እጅ ተገደሉ።
  • ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - ቻሌንጀር የተባለችው የአሜሪካ የጠረፍ መንኮራኲር ሰባት ጠፈረኞችን ጭኖ እንደተተኮሰ አየር ላይ ፈንድቶ ሲከሰከስ ሰባቱም አሜሪካውያን ሞተዋል።
  • ፲፱፻፸፭ ዓ/ም - የብሪታኒያ ሞተር አሽከርካሪዎችንና የጋቢና ተሳፋሪዎችን ከዚህ ዕለት ጀምሮ የወንበር ቀበቶ እንዲያስሩ የሚያስገድድ ሕግ ተተገበረ።
  • ፲፱፻፺፮ ዓ/ም መካ ላይ በሕዝብ ግፊትና ትርምስ ምክንያት ፪፻፩ ሀጂዎች ሲሞቱ፣ ፪፻፵፬ ተሳላሚዎች ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
  • ፳፻፩ ዓ/ም - በኬንያ፣ ሞሎ በሚባል ስፍራ የፈሰሰ ነዳጅ ተቀጣጠሎ ፻፲፫ ሰዎች ሲሞቱ ከ ፪፻ በላይ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል።

ጥር ፳፫

  • ፲፱፻፸፭ ዓ/ም - የብሪታኒያ ሞተር አሽከርካሪዎችንና የጋቢና ተሳፋሪዎችን ከዚህ ዕለት ጀምሮ የወንበር ቀበቶ እንዲያስሩ የሚያስገድድ ሕግ ተተገበረ።
  • ፲፱፻፺፮ ዓ/ም መካ ላይ በሕዝብ ግፊትና ትርምስ ምክንያት ፪፻፩ ሀጂዎች ሲሞቱ፣ ፪፻፵፬ ተሳላሚዎች ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
  • ፳፻፩ ዓ/ም - በኬንያ፣ ሞሎ በሚባል ስፍራ የፈሰሰ ነዳጅ ተቀጣጠሎ ፻፲፫ ሰዎች ሲሞቱ ከ ፪፻ በላይ ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት ደርሷል።

ጥር ፳፬

  • ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - ኮለምቢያ የተሰኘችው የአሜሪካ የጠፈር መንኲራኩር ከተልዕኮዋ ተመልሳ የምድር የአየር ክልል ውስጥ ስትገባ በደረሰባት የፍጻሜ አደጋ ሰባቱም አብራሪዎቿ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
  • ፲፰፻፺፫ ዓ/ም ከረጅም ዘመናት የብሪታንያ ንግሥትነትና የሕንደኬ ንግሥተ ነገሥትነት በኋላ ያረፉት ቪክቶሪያ በዚህ ዕለት ተቀበሩ።
  • ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - በኡጋንዳ ኢዲ አሚን በተፈነቀሉት ሚልተን ኦቦቴ ምትክ የአገሪቱ መሪ ሆኑ።
  • ፲፱፻፹፪ ዓ/ም የአፓርታይዳዊዋ ደቡብ አፍሪቃ ፕሬዚደንት ደ ክለርክ ለሠላሳ ዓመታት በሕግ ተከልክሎ የነበረውን የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቡድን (African National Congress) ሕጋዊ መሆኑንና በወቅቱ በእሥራት ላይ የነበሩትን ኔልሰን ማንዴላ እንደሚፈቱ አስታወቁ።


ጥር ፳፮፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፵፮ ኛው ዕለት ሲሆን፤ የበጋ ወቅት ፴፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፪፻፳ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፲፱ ቀናት ይቀራሉ።

  • ፲፱፻፶፯ ዓ.ም. የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ሕንፃ ተመረቀ። በሕንፃው መግቢያ ላይ የተለጠፈው ሰሌዳ እንዲህ ይላል፤

    ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ለመናገሻው ከተማ ለአዲስ አበባ ሕዝባቸው፣ ለማኅበራዊ ኑሮው፣ ለኤኮኖሜውና ለባህሉ ዕድገት አማካይ የአገልግሎት ቤት ይሆን ዘንድ ፈቅደው ያሠሩትን ይህን ሕንፃ፣ በሠላሳ አራተኛው ዘመነ መንግሥታቸው መርቀው ከፈቱ።

ጥር ፳፰

  • ፲፱፻፶ ዓ/ም - በግብጽ፣ ጋማል አብደል ናስር የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ሆነው ታጩ።
  • ፲፱፻፶ ዓ/ም - የአሜሪካ ኅብረት አየር ኃይል በሳቫና (ጂዮርጂያ) ጠረፍ አካባቢ አንድ የሃይድሮጅን ቦምብ ጠፍቶበት እስካሁን አልተገኘም።

ጥር ፳፱

  • ፲፮፻፹፪ ዓ/ም - በአሜሪካ ግዛቶች የመጀመሪያው የወረቀት ገንዘብ በማሳቹሴትስ ተሠራጨ።
  • ፲፰፻፸፯ ዓ/ም - ካይሚ የተባለ የጣልያን የባህር ኃይል መኮንን ምጽዋ ወደብን ይዞ የአገሩን ሰንደቅ ዓላማ ካውለበለበ በኋላ፣ የግብጽ እና የብሪታኒያ መንግሥቶች ወደቡን እንድይዘው ፈቅደውልኛል ብሎ አወጀ።

ጥር ፴

  • ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - በፍልውሃ አቅራቢያ በዘመናዊ ዕቅድ አዲስ የተሠራው ኢዮቤልዩ (የአሁኑ ብሔራዊ) ቤተ መንግሥት ተመረቀ
  • ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የአፍሪቃ ኢኮኖሚ ኮሚሲዮን ዋና መሥሪያ ቤትና በአዲስ አበባ ከተማ ለሚደረገው ልዩ ልዩ የአፍሪቃ መንግሥታት ጉባኤዎች መሰብሰቢያ፣ በኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት ፊት ለፊት የተሠራውን የአፍሪካ አዳራሽ፣ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተመርቆ ተከፈተ።

[ለማስተካከል] የካቲት

የካቲት ፩ ቀን

  • ፫፻፹፮ ዓ/ም - በክርስትና ሃይማኖት የተከሰቱትን ተቃራኒ ትምህርቶች በጉባኤ ለመወሰን የቁስጥንጥንያው ንጉሥ ቀዳማዊ ቴዎዶስዮስ ባስተላለፈው ጥሪ መሠርተ ፩፻፶ ሊቃውንት፣ ኤጲስ ቆጶሳት በቁስጥንጥንያ ጉባኤ ተሳትፈው መቅዶንዮስን፤ አፖሊናሪዮስን እና ሌሎችን መናፍቃንን አወገዙ።

የካቲት ፪ ቀን

የካቲት ፫

  • ፲፰፻፵፯ ዓ/ም - ደጃዝማች ካሳ (ዓፄ ቴዎድሮስ)ና ደጃዝማች ውቤ ቧሂት ላይ ድንኳን ተክለው ተገናኙ። ደጃዝማች ካሳም የእንግሊዙን ሊቀ መኳስ ዮሐንስን (John Bell)በመንጥር አይተህ ንገረኝ አሉት። የሸማ ድንኳን ባየ ጊዜ ነገራቸው። ደጃዝማች ካሳም «አያሳድረኝ አላሳድረውም» ብለው ተናገሩ። ያንግዜውንም ተነሣ አሉ። ባሰለፉትም ጊዜ እንዴህ ብለው በፍከራ ትንቢት ተናገሩ። «እንኳን ይህን ቁርጥማታም ወሎን፣ መትቼ የሻዋውን ንጉሥ እይዘዋለሁ። ስሜን ስሜን እንግርሀለሁ ያልሁህ ወታደር ስሜም ቴዎድሮስ ነው» አሉ። አስቀድሞ ገና በንጉሥ አምላክ በል። ስሜን ስሜን እነግርሀለሁ ብለው ነበርና። ያንግዜውን እንዴህ አሉ። «ወታደር አይዞህ አትፍራ። የውቤ ነፍጥ የውቤ ነፍጥ ቢልህ የተለጎመው ጨርቅና ባሩድ ነው። አይነካህም» አሉት። እኔ የክርስቶስ በርያ ሁሉንም አሳይሀለሁ ወታደር ባሉ ግዜ ሰልፍ ገጠመ። ደጃች ውቤም ተያዙ።

የካቲት ፬

Empress Zewditu.jpg
Tayitu.JPG

የካቲት ፭

Téwodros II - 2.jpg
  • ፲፱፻፶፫ ዓ/ም የቀድሞዋ ኮንጎ ሊዮፖልድቪል (የአሁኗ የኮንጎ ሪፑብሊክ) የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ፓትሪስ ሉሙምባ መገደላቸው ይፋ ተደረገ።

የካቲት ፯

  • ፲፰፻፶፩ ዓ/ም - በሰሜን ምዕራብ የአሜሪካ ኅብረት የምትገኘው የኦሪጎን ግዛት ፴፫ ኛዋ የኅብረቱ አባል ሆነች
  • ፲፱፻፬ ዓ/ም - በደቡብ ምዕራብ የአሜሪካ ኅብረት የምትገኘው የአሪዞና ግዛት ፵፰ ኛዋ የኅብረቱ አባል ሆነች
  • ፲፱፻፲፮ ዓ/ም - ‘የዓለም አቀፍ የንግድ ሒሣብ መሣሪያዎች ድርጅት’ አይ.ቢ.ኤም(IBM) ተመሠረተ።
  • ፲፱፻፴፰ ዓ/ም በዓለም የመጀመሪያው ሁለ-ገብ መቀምር (Electronic Numerical Integrator And Computer) ወይም ኮምፕዩተር ይፋ ተደረገ።
Empress Menen Asfaw with Crown.jpg

የካቲት ፱

Alula Engida2.JPG

የካቲት ፲

  • ፲፯፻፴፮ ዓ/ም - አጼ ኢያሱ ብርሃን ሰገድ ከጳጳሱ አባ ዮሐንስ እና ከ እጨጌ ኤውስጣቴዎስ ጋር ሆነው አንድ የሶርያ ተወላጅ ነጋዴ በሐሰት ጳጳሱ እኔ ነኝ እያለ ብዙ ሰዎችን በማሳሳቱ አስረው ወደአገሩ አባረሩት።
Mekonnen endalkachew-1.JPG
  • ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥትን መስከረም ፪ ቀን የገለበጠውን፣ የኅብረተ ሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር (ደርግ) ለመገርሰስ፣ በቀድሞ አጠራሩ ተጋድሎ ሓርነት ሕዝብ ትግራይ (ተሓሕት"፣ በኋላም ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ተመሠረተ፤ በምዕራባዊ ትግራይ ደደቢት በተባለ ሥፍራም የትጥቅ ትግሉን ጀመረ።

የካቲት ፲፪

የካቲት 12 አደባባይ.JPG
  • ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - ለኢጣሊያ ንጉሣዊ ቤተሰብ አንድ ልዑል በመወለዱ ምክንያት በጄነራል ግራዚያኒ ትዕዛዝ በቀድሞው የገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቅጽር ግቢ ከተሰበሰቡት የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፤ ለፋሺስቶቹ ያደሩ ከሀዲ ባንዳዎችና መኳንንት፤ የፋሺስት ባለ ሥልጣናት ወታደሮች በተሰበሰቡበት መኻል፣ አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም የእጅ ቦምብ ወርውረው አደጋ ሲጥሉ ግራዚያኒን ጨምሮ ብዙ ሰዎች ተጎድተዋል። ይኸንን ድርጊት በመበቀል ሰበብ እዚያው ግቢ ውስጥ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ተጨፈጨፉ፤ ቀጥሎም የተማሩ ወጣቶች፣ የጦር መኮንኖችና ካህናት፣ የደብረ ሊባኖስ መነኮሳት በሙሉ እየተለቀሙ ተጨፈጨፉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በቤት ውስጥ እያስገቡ ከውጭ ቆልፈው ቤንዚን እያርከፈከፉ አቃጠሉአቸው። በአካፋ፣ በዶማ፣ በመጥረቢያ በተገኙበት ኢትዮጵያውያንን እየቆራረጡ የደም ጎርፍ አወረዱ። ፋሽስቶች የአዲስ አበባንና የአካባቢውን ሕዝብ በጅምላ ጨፈጨፉት። በሶስት ቀናት ፴ሺህ ሕዝብ መስዋዕትነት ተቀበለ።
  • ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኢቲ-ኤ-ኤፍ ደብልዩ (ET-AFW) ዲሲ ፫ (Douglas C-47B-10-DK፤ በደቡብ-ምዕራብ ኤርትራ በምትገኘው ባረንቱ ላይ በቦምብ ፍንዳታ ተከስክሶ ሲወድቅ አምስቱም ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል። አየር ዠበቡም ከጥቅም ውጭ ሆኗል።
  • ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - የአዲሲቷን ቻይና የሰብዓዊ እና ኤኮኖሚካዊ ገጽታዎች በማነጽ አገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ አሁን የያዘችውን የኤኮኖሚያዊ ኃያልነት ሥፍራ እንድትይዝ ያስቻሏት መሪዋ ዶንግ ዥያው ፒንግ በተወለዱ በ ፺፪ ዓመታቸው አረፉ።

የካቲት ፲፫

  • ፲፯፻፰ ዓ/ም - ንጉሥ አጼ ዮስጦስ አርፈው በልደታ ተቀበሩ። በህመም ምክንያት ሞቱ ቢባልም፣ በነፍሰ ገዳይ እጅ ታንቀው እንደሞቱ በሰፊው ይታመናል።
  • ፲፱፻፴ ዓ/ም - በአጋምሳ ላይ ኢትዮጵያውያን አርበኞች ከፋሺስት ኢጣሊያ ጋር ውጊያ ገጠሙ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ በፈነዳው አብዮት፣ የወጥቶ-እብስ ሠራተኞት የሦስት ቀን አድማቸውን ጀመሩ። በ[አዲስ አበባ]] በየቀበሌው እና በየመንገዱ የሚካሄደው ሽብር ቀጥሎ ዋለ።

የካቲት ፲፬

  • ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በአሜሪካ ለጥቁር አሜሪካውያን ሰብአዊ መብት በመታግል የሚታወቀው ማልከም X በኒው ዮርክ ከተማ ላይ በጥይት ተደብድቦ ሞተ።

የካቲት ፲፭

  • ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ግብጽ እና ሶርያ የአረብ ሪፑብሊ ኅብረትን (United Arab Republic) መሠረቱ። ይሄ የሁለቱ አገሮች ኅብረት ከሦስት ዓመታት በኋላ ቢፈርስም የግብጽ መጠሪያ ስሟ ሆኖ ለብዙ ዓመታት ቆይቷል።.
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያአብዮት ፍንዳታ የተፋፋመውን ሽብር ለመቆጣጠር በተወሰደው እርምጃ፣ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ወታደሮችን በአዲስ አበባ ከተማ ቀበሌዎችና ‘ቁልፍ’ ቦታዎች ለጥበቃ አሰማራ።
Jonas Savimbi.jpg
  • ፲፱፻፺፬ ዓ/ም አንጎላዊው የፖለቲካ እና የነጻነት ትግል መሪ የመበሩት ጆናስ ሳቪምቢ በወታደራዊ የደፈጣ ስልት ተገደሉ።

የካቲት ፲፮

RasDesta.jpg
  • ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በግራዚያኒ የሚመራ የፋሺስት ኢጣልያ ሠራዊት በዝዋይ አካባቢ የጦር አዝማቾቹን የራስ ደስታ ዳምጠውን እና የደጃዝማች በየነ መርዕድን አርበኞት ድል አደረጉ። ሁለቱም ኢትዮጵያውያን አዝማቾች ሕይወታቸውን በዚህ ዕለት ሰዉ። ኢጣሊያውያኑ ራስ ደስታን ከያዟቸው በኋላ በጥይት ደበደቧቸው፡፡
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ኢትዮጵያ ላይ በፈነዳው አብዮት አስገዳጅነት የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የሕዝቡን ሸክም ለማቃለል የነዳጅ ዋጋ ቅነሳን የሚያካትት ኤኮኖሚያዊ እርምጃዎችን እንደሚወስድ ይፋ አደረገ።

የካቲት ፲፯

  • ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ቴኔኮ የተባለ የአሜሪካ ኩባንያ በኦጋዴን ግምቱ ፸፮ ቢሊዮን ሜትር ኩብ የሆነ ሰፊ የተፈጥሮ ነዳጅ (ጋዝ) እንዳገኘ አስታወቀ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ላይ በፈነዳው አብዮት በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ በልዕልት ፀሐይ ሆስፒታል አካባቢ ተኩስ ተከፈተ። በዚሁ ዕለት የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ለወታደሮች የደሞዝ ጭመራ ለማድረግ መወሰኑን አስታወቀ።

የካቲት ፲፰

  • ፲፱፻፸፱ ዓ/ም - የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ሴቶችን የቅስና ሥልጣን ለመቀበል የሚያስችለውን ውሳኔ ከፍ ባለ የድምጽ ብዛት አጸደቀ።

የካቲት ፲፱

የካቲት ፳

  • ፲፱፻፲፬ ዓ/ም - የብሪታኒያ ንጉዛት መንግሥት በራሱ ፈቃድ በግብጽ ላይ የነበረውን ሉዐላዊነት አቁሞ ነጻነትን ለግብጻውያን አሳልፎ ሲሰጥ የውጭ ጉዳይን፤ ግንኙነትን፤ የጦር ሠራዊትንና የግብጽ ሱዳንን አስተዳደር የሚመለከቱ ጉዳዮችን ግን በራሱ አስተዳደር ሥር አስቀረ።
  • ፲፱፻፳፯ ዓ/ም - ለዱፖንት ኩባንያ ይሠራ የነበረው ዋላስ ካሮዘርስ ናይሎን (Nylon) ፈጠረ።

የካቲት ፳፩

  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ለሰባት ዓመታት ከተቋረጡ በኋላ አሜሪካ እና ግብጽ የዲፕሎማቲክ ግንኙነታቸውን እንደገና ጀመሩ።

የካቲት ፳፪

  • ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የብሪታንያ ቅኝ ግዛት የነበረችው ኡጋንዳ እራሷን በራሷ እንድታስተዳድር ተፈቀደላት። ወዲያውም የመጀመሪአዋን የሕዝብ ምርጫ አካሄደች።

የካቲት ፳፫

  • ፲፰፻፶፱ ዓ/ም - ነብራስካአሜሪካ ኅብረት ፴፯ ኛዋ አባል ሆነች። ላንካስተር የሚባለው ከተማዋ በአዲስ ስም ሊንከን ተብሎ ዋና ከተማዋ ሆነ።
  • ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - በብሪታኒያ እና በፈረንሳይ ትብብር የተሰራው ‘ኮንኮርድ’ አየር ዠበብ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፈረንሳይ ከተማ ቱሉዝ ተነስቶ ለ ሃያ ሰባት ደቂቃ የበረራ ሙከራ አደረገ።
  • ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - አሁን ዚምባብዌ የምትባለው የቀድሞዋ ሮዴዢያ ነጭ ዜጎች በመሪያቸው ኢያን ስሚዝ ሥልጣን አገሪቱን ከብሪታኒያ ዘውድ ጋር የነበራትን ሰንሰለት በጥሰው በሸፍጥ ሪፑብሊክ አደረጓት።

የካቲት ፳፬

የካቲት ፳፭

  • ፲፱፻፸፪ ዓ/ም - በአዲሲቷ ዚምባብዌ በተካሄደው የሕዝብ ምርጫ፣ ሮበርት ሙጋቤ በከፍተኛ የድምጽ ብልጫ የአገሪቱ የመጀመሪያው ጥቁር ጠቅልይ ሚኒስትር ሆኑ።

የካቲት ፳፮

የካቲት ፳፯

  • ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - ጎልድ ኮስት ትባል የነበረችው የብሪታንያ ቅኝ ግዛት ጋና ተብላ ነጻ ሆነች
Muhammad Ali NYWTS.jpg
  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - ቦቅሰኛው ካስየስ ክሌይ በእስልምና ሃይማኖት መሪው ኤልያስ ሙሐመድ አዲስ ስም ተሰጥቶት ሙሐመድ አሊ ተብሎ ተሠየመ።

የካቲት ፳፰

  • ፲፰፻፺፩ ዓ/ም - የባየር መድኀኒት ኩባንያ አስፒሪን የተባለውን መድኀኒት በንግድ-ስም አስመዘገበ።
Golda Meir 03265u.jpg

የካቲት ፳፱

  • ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - ‘ቴሌፎን’ ተብሎ የተሠየመው ፈጠራ የአዕምሯዊ ንብረትነቱ (patent) በአሌክሳንደር ግራሃም ቤል ስም ተመዘገበ።
  • ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በወለጋ ጠቅላይ ግዛት የቅርፀ ምድር ጥናት ለማካሄድ የሚያስችል የቴክኒክ ስምምነት በኢትዮጵያ እና በጃፓን መሀል ተፈረመ።
  • ፲፰፻፹፰ ዓ/ም - ኢጣልያም በአድዋ ጦርነት ድል ከተመታች በኋላ በዚሁ ምክንያት ጠቅላይ ሚኒስትሯ ፍራንቼስኮ ክሪስፒ ሥልጣኑን ለቀቀ።

[ለማስተካከል] መጋቢት

መጋቢት ፩

  • ፲፰፻፹፩ ዓ/ም - ዮሐንስ ፬ኛ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ በትልቅ ጦርነት ከደርቡሾች ጋር ሲዋጉ መተማ ላይ በእነሱ ውጅ ወደቁ። ሱዳኖቹ አንገታቸውን ቆርጠው እንጨት ላይ ሰክተው ገበያ ለገበያ ለሕዝባቸው አሳዩት።
  • ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - አዲስ አበባ፣ በጄኔራል ዊንጌት ትምህርት ቤት የኦሮሞ ተወላጅ ተማሪዎች ባካሄዱት አመጽ ትምህርት ቤቱ ለጊዜው ተዘግቶ ዋለ።

መጋቢት ፪

  • ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ።
  • ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር (Civil Aviation Administration) ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል።

መጋቢት ፫

መጋቢት ፬

  • ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የተመደቡ (ሦስት የሩሲያ ጋዜጠኞችና ሦስት የቼኮዝሎቫኪያ ዲፕሎማቶች)፤ ለተማሪዎች እንቅስቃሴ የገንዘብ እርዳታ አድርገዋል በሚል ወንጀል ከአገር እንዲባረሩ ተደረገ።

መጋቢት ፭

  • ፲፱፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (UNDP) በእርሻ ልማት መስክ ለአዋሽ ሸለቆ ማልሚያ ሁለት ስምምነቶችን ፈረሙ። በተጨማሪ የዓለም ባንክ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (IDA) በኢትዮጵያ ለከብት እርባታ የሚውል የአምሥት ሚሊዮን ዶላር ዋስትና እንደሚሰጥ አስታወቀ።

መጋቢት ፰

  • ፲፱፻፹ ዓ/ም - የኤርትራ ነጻነት ግንባር ሠራዊት በአፋበት ግንባር በተሰማራው የ’ናደው እዝ’ ጦር ላይ ከጎንና ከኋላም አስርጎ ሲያጠቃ በኮሎኔል ጌታነህ ኃይሌ የሚመራው የናደው እዝ በከፍተኛ ሽብር ሊሸነፍ ቻለ።
Chuck Kennedy - The Official White House Photostream - P060409CK-0199 (pd).jpg

መጋቢት ፱

  • ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - በምሥራቃዊ ጀርመን ለመጀመርያ ጊዜ የነጻ ምርጫ ተካሄደ።

መጋቢት ፲

መጋቢት ፲፩

  • ፲፭፻፳፪ ዓ/ም - ከአህመድ ግራኝ ጋር ሽምብራኩሬ በተባለ ቦታ ላይ በተደረገ ጦርነት ራስ ኅዱግ፣ ራስ ማኅፀንቶ፣ ገብረ መድኅን እና ብዙ የኢትዮጵያ ሠራዊት አለቁ።
  • ፳፻፪ ዓ/ም - የአፍሪቃ ኅብረት የሠላምና ጸጥታ ምክር ቤት በማዳጋስካር ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል በለወጡ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የተጣለው ማዕቀብ ተግባራዊ እንዲሆን ወሰነ፡፡

መጋቢት ፲፪

  • ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በአፓርታይዳዊ ደቡብ አፍሪቃ፣ በታሪክ ዘገባ ‘የሻርፕቪል ፍጅት’ (Sharpeville Massacre) በሚባለው ክስተት ፖሊሶች በጥቁር ሕዝብ ላይ ተኩስ ሲከፍቱ ፷፱ ጥቁሮች ሲገደሉ ፻፹ ሰዎች በጥይት የቁስል አደጋ ደርሶባቸዋል።
  • ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የአለማኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአዶልፍ ሂትለር የሚመራው የሚንስትሮች ሸንጎ በራሱ ሥልጣን ሕግ መደንገግ የሚያስችለውን ሕግ (ሕጋዊ አምባ ገነንነት) ደነገገ።
  • ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - በአይሮፍሎት በረራ ቁጥር ፭፻፺፫ ላይ ተሳፍረው የነበሩ ፸፭ ሰዎች፤ የአብራሪው የ ፲፭ ዓመት ልጅ አየር ዠበቡን በ’ስህተት’ ከአውቶ-ፓይለት በመሰረዙ ሳይቤርያ ውስጥ ተከስክሰው አለቁ።

መጋቢት ፲፭

መጋቢት ፲፮

  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያአብዮት ንቅንቅ፣ በኮሎኔል የዓለም ዘውዴ የተመራ የአየር ወለድ ሠራዊት በደብረ ዘይት የአየር ኃይል ረብሸኞችን በመምታት በቁጥጥር ስር አዋለ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የባለ ሥልጣናትን አቋም እና ወንጀል የሚያጠና አጣሪ ሸንጎ እንደመሠረቱ አስታወቁ።

መጋቢት ፲፯

  • ፲፱፻፸፮ ዓ/ም - ጊኒን ለነጻነት ያበቋት መሪዋ አህመድ ሴኩ ቱሬ በተወለዱ በ ፷፪ ዓመታቸው አረፉ።

መጋቢት ፲፰

  • ፲፰፻፸ ዓ/ም - ዓፄ ዮሐንስ እና የሸዋንጉሥ ምኒልክ ወሎቦሩ ሜዳ ላይ ተገናኝተው ንጉሥ ምኒልክ የንጉሠ ነገሥቱን የበላይነት መቀበላቸውን እና ዓፄ ዮሐንስ ደግሞ የምኒልክን በሸዋ ላይ ንጉሥነታቸውን በመቀበል በመሐላ ታረቁ። ንጉሠ ነገሥቱ ለንጉሥ ምኒልክም ዘውድ ጫኑላቸው።
  • ፲፱፻፴ ዓ/ም - በፋሺስት ኢጣሊያና በአርበኞች መካከል በፉግታ ውጊያ ተካሄደ።

መጋቢት ፲፱

  • ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - የንግድ እና ኢንዱስትሪ ማዕከል እንዲሁም የቱርክ ርዕሰ ከተማ የሆነችው ‘አንጎራ’ ስሟ ተለውጦ አንካራ ስትባል፤ የአገሪቱ አንደኛ ከተማ እና በሮማይስጡ ቄሳር ቁስጥንጢኖስ የተመሠረተችው ቁስጥንጢንያ ወይም ኮንስታንቲኖፕል (Constantinople) ስሟን ቀይራ ኢስታንቡል ተባለች።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አብዮት ሲፈነዳ ከተሰነዘሩት ዐበያት ሕዝባዊ እሮሮዎች አንዱ በመሳፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ ሚኒስትሮችና ባለሥልጣናት ግፈኝነት እና ሙስና ስለነበር ይሄንኑ ጉዳይ እንዲያጠና የተመሠረተው ኮሚሲዮን አባላት ተሠየሙ።
  • ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - በደቡብ አፍሪቃ ሪፑብሊክ ፤ በጆሃንስበርግ ከተማ፣ በዙሉዎችና ‘የአፍሪቃ ብሔራዊ ሸንጎ’ (African National Congress) ደጋፊዎች መኻል በተከሰተው ሽብር አሥራ ስምንት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።

መጋቢት ፳

መጋቢት ፳፩

  • ፲፱፻፺፪ ዓ/ም በኢትዮጵያ በሆቴሎች እና በቱሪዝም የሥራ ዘርፍ ፋና ወጊ በመሆን ሀገራቸውን ለበርካታ ዓመታት ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ በቀለ ሞላ በተወለዱ በ፹፯ ዓመታቸው ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

መጋቢት ፳፫

  • ፲፮፻፩ ዓ/ም – አጼ ሱስንዮስ የደብረ ዘይት ዕለት በአክሱም ጽዮን (ርዕሰ አድባራት ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ፅዮን) ቤተ ክርስቲያን፣ በስመ መንግሥት ሥልጣን ሰገድ ተሰይመው ነገሡ።

መጋቢት ፳፬

  • ፲፱፻፺፯ ዓ/ም - የካቶሊኩ ሊቀ ጳጳስ ዳግማዊ አቡነ ዮሐንስ-ጳውሎስ በ፹፬ ዓመት ዕድሜያቸው አለፉ።
  • ፳፻፫ ዓ/ም - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።

መጋቢት ፳፭

ሴቫስቶፖልመድፍ.jpg

መጋቢት ፳፮

  • ፲፰፻፺፯ ዓ/ም - ‘የካንግራ ሸለቆ’ በሚባለው የሕንድ ግዛት ውስጥ የተከሰተው እሳተ ገሞራ የ ፳ ሺ ሰዎችን ሕይወት ሲያጠፋ የአካባቢውን ከተማዎችና ሠፈሮች አውድሟል።
Martin Luther King Jr NYWTS.jpg
  • ፲፱፻፷ ዓ/ም - በአሜሪካ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጄምስ ኧርል ሬይ በተባል ነፍሰ ገዳይ እጅ በሜምፊስ ከተማ ተገደለ። የኪንግ ሞት ዜና ሲሰማ በ መቶ የአሜሪካ ከተሞች ከፍ ያለ የሕዝብ ሽብር ተከተለ።
  • ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኒው ዮርክ መንታ ሰማይ-ጠቀስ ፎቆች (‘የዓለም የንግድ ማዕከል’ World Trade Center ) ሕንፃ ግንባታ ተጠናቀቀ። እነዚህ መንታ ፎቆች መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም በአመጽ የአየር ዠበብ ግጭት ወድመዋል።

መጋቢት ፳፯

  • ፲፭፻፶፩ ዓ/ም - የስቅለት ዓርብ ዕለት በአዋሽ አካባቢ ከአዳሉ አሚር ኑር ጋር በተደረገ ጦርነት ላይ ዓፄ ገላውዴዎስ እና የደብረ ሊባኖስ እጨጌ ዮሐንስ ተገደሉ። በሐረሩ ዘእና መዋዕል ዘገባ አሚር ኑር የንጉሠ ነገሥቱን ጭንቅላት ወደይፋቱ ሡልጣን ሳዳዲን ልኮ ዘመቻውን ቀጠለ። ወንድማቸው ዓፄ ሚናስ በስመ መንግሥት አድማስ ሰገድ ተብለው በኢትዮጵያ አልጋ ተክተዋቸው ነገሡ።
  • ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - የብሪታንያ ቅኝ ገዚዎች በሕንድ ሕዝብ ላይ ጭነውት የነበረውን የ’ጨው ቀረጥ’ ሕዝቡ በማህተማ ጋንዲ መሪነት በሠላማዊ ሰልፎች መቃወሙን ቢያሳይም ትግሉ አልተሳካለትም ነበር። ነገር ግን ጋንዲ ወደ ጨው-ባሕር ወርደው ከባሕር ውሐ ጨው በነጻ ማውጣት በመቻላቸው ቅኝ ገዥዎቹ እስከዚያ ጊዜ ድረስ በሕዝቡ ላይ አውጀውት የነበረውን የጨው ፍብረካ ባለቤትነት የግዳጅ ቀንበር ሰብሮታል።
  • ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - የርዋንዳ እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንቶች አብረው የተሳፈሩበት አየር ዠበብ በርዋንዳዋ ርዕሰ ከተማ ኪጋሊ አካባቢ ላይ በደረሰበት አደጋ ሁለቱም ፕሬዚናንቶች ሞተዋል።

መጋቢት ፳፱

  • ፲፰፻፹፰ ዓ/ም - የጥንቷ ሮማ ቄሳር ቀዳማዊ ቴዎዶሲዩስ በአዋጅ ከከለከለው ከ ሺ ፭ መቶ ዓመታት በኋላ ዘመናዊው የኦሊምፒክ ውድድር በአቴና ከተማ ተጀመረ።
Flag of WHO.svg
  • ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - በርዋንዳ በጎሳ ልዩነት ላይ የተመሠረተው የእርስ በእርስ ፍጅት፣ የሁቱ ጎሠኞች እስከ ፰ መቶ ሺ የሚሆኑ የቱትሲ ብሔር ተወላጆችን ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ታይቶም ተሰምቶም በማያውቅ ሁኔታ ፈጇቸው። የውጭ መንግሥታትን በጉዳዩ ጣልቃ እንዳይገቡ በተጤነ ዕቅድ፣ የርዋንዳ ሠራዊት በዚሁ ዕለት አሥር የቤልጂግ ጸጥታ አስከባሪ ወታደሮችን ገድለዋል።

መጋቢት ፴

  • ፲፱፻፵፭ ዓ/ም - በኬንያ ‘የአፍሪቃ ኅብረት እንቅስቃሴ’ መሪ የነበሩት ጆሞ ኬንያታ ድርጅቱ በቅኝ ገዝዎቻቸው ላይ የ’ማው ማው’ ሽብርን አካሂዷል በሚል በተሰነዘርበት ክስ ኃላፊነት አለብዎ ተብለው ለሰባት ዓመት የጽኑ እሥራት ቅጣት ተፈረደባቸው።
JohannesPaul2-portrait.jpg

[ለማስተካከል] ሚያዝያ

ሚያዝያ ፩

  • ፲፱፻፶፩ ዓ/ም - የአሜሪካ የጠፈር በረራና ምርመራ ባለሥልጣን (NASA the National Aeronautics and Space Administration) ’መርኩሪ’ በሚባለው የአገሪቱ የመጀመሪያ የሰው አሳፋሪ መንኮራኩር መርሐ-ግብር የሚሳተፉትን ጠፈርተኞች ለዓለም አስተዋወቀ። እነርሱም፦ ስኮት ካርፔንተር፣ ጎርደን ኩፐር፣ ጆን ግሌን፣ ቨርጅል ግሪሰም፣ ዎልተር ስኪራ፣ አላን ሼፈርድ እና ዶናልድ ስሌይተን ነበሩ።
  • ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ሁለት የብሪታንያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፤ ብራያን ሃሪሶን (Brian Harrison) እና ጄምስ ስሌተር (James Slater) ለጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ። ከንጉሠ ነገሥቱም ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
  • ፲፱፻፷ ዓ/ም - የጥቁር አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት መሪ የዶክቶር ማርቲን ሉተር ኪንግ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በተወለዱበት ከተማ በአትላንታ ተከናወነ። የጆርጂያ ክፍለ-ሀገር ገዥ ሌስተር ማደክስ ዶክቶር ኪንግ የ’ሀገር ጠላት’ ነበሩ በሚል አቋም እቀብሩ ላይ አልሳተፍም ብለው መቅረታቸው ሳይበቃ ለሟቹም ክብር የክፍለ ሀገሩን መንግሥታዊ ቢሮዎች እንደማይዘጉ አስታወቁ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በጠቅላይ ሚኒስትር እንዳልካቸው መኮንን የሚመራው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ሕገ መንግሥታዊ የዘውድ ሥርዓትን ለመመሥረት የታዘዘውን አጥኒ ሸንጎ በማንኛውም ጉዳይ እንደሚተባበረውና እንደሚረዳው አረጋገጠ። አያይዞም መሬትን በተመለከተ በአገሪቱ ውስጥ ማንም ሰው ለማልማት ከሚችለው በላይ መሬት መያዝ እንዳይችልና ለወደፊት ከአርሶ አደሮች በስተቀር የእርሻ መሬት ለማንም እንደማይሰጥ ለማድረግ የሚያስችል ሕግ እንደሚወጣ አስታወቀ።
  • ፲፱፻፺፩ ዓ/ም - የኒጄር ፕሬዚደንት ኢብራሂም ባሬ ማይናሳራ በአገሪቱ በተካሄደው ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ተገደሉ።

ሚያዝያ ፪

  • ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - ‘ቢትልስ’ (Beatles) የሚባለው የሙዚቃ ቡድን አባላት እርስ በእርስ ባለመስማማታቸው እንደተበተኑ የቡድኑ አባል የነበረው ፖል መካርትኒ ይፋ አደረገ።
  • ፲፱፻፷ ዓ/ም - የአሜሪካ ፕሬዚደንት ሊንደን ጆንሰን ጥቁር አሜሪካውያን ላይ የነበረውን የመኖሪያ ቤት ጭቆና ሕገ-ወጥ የሚያደርግ የሰብዓዊ መብት ሕግ አጽድቀው ፈረሙ።
  • ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - በታንዛኒያ መንግሥት ድጋፍ የተንቀሳቀሱ የኡጋንዳ ታጋዮች የአገሪቱን በትረ-ሥልጣን ከአምባ ገነኑ ኢዲ አሚን እጅ ፈልቅቀው ጨበጡ። አሚን ሸሽቶ ወደሊቢያ ኮበለለ።
  • ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የሶቪዬት ሕብረት የመጀመሪያውን ጠፈርተኛ፣ የ፳፯ ዓመት የአየር ኃይል አባል ዩሪ ጋጋሪንን በመኖራኩር ተኮሰች። ጋጋሪን በጠፈር በረራ ምድርን ለአንድ ሰዓት ከአርባ ደቂቃ ያህል ከዞረ በኋላ ወደመሬት ተመልሷል።
  • ፲፱፻፸፫ ዓ/ም - የአሜሪካ የበረራ እና የጠፈር አስተዳደር ድርጅት (NASA) ‘ስፔስ ሻትል’ በመባል የሚታወቀውን አየር ዠበብ/የጠፈር መንኮራኩር ለመጀመሪያ ጊዜ ወደጠፈር ተኮሰ። ይኽ የመጀመሪያው አየር ዠበበ/መንኮራኩር ‘ኮለምቢያ’ (Columbia) የተባለው ሲሆን ሃያ ሰባት ጊዜ ወደጠፈር ተተኩሶ ከተመለሰ በኋላ ጥር ፳፬ ቀን ፲፱፻፺፭ ዓ/ም ተመልሶ ወደምድር ሲገባ ተቃጥሎ ተሰባበረ።
  • ፭፻፭ ዓ.ም.፣ ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ተወለደ።
  • ፲፭፻፳፬ ዓ/ም - አይፈርስ አምባ በተባለ ስፍራ ከግራኝ መሀመድ ጋር በተደረገ ጦርነት ራስ እስላም ሰገድ፣ ተክለ ኢየሱስ እና ብዙ መኳንንት ሞቱ።
  • ፲፱፻፵፫ ዓ.ም. ፦ ፪ ሺህ ፻፷፰ ወታደር ያሰለፈው የኢትዮጵያ የክቡር ዘበኛ ሠራዊት፣ ቃኘው የሻለቃ ጦር ወደ ኮርያ ዘመተ። ከዘማቾቹ ማህል አንዱ የነበረው ‘የክራሩ ጌታ’ የ፶ ዐለቃ ካሣ ተሰማ "እልም አለ ባቡሩ" በሚለው ዘፈኑ ይሄንን ዕለት አወድሶታል።
  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - አንጋፋው የፊልም ተዋናይ ሲድኒ ፗቲዬር ‘ሊሊስ ኦፍ ዘ ፊልድ’ (Lilies of the Field) በተባለው ፊልሙ የ’ኦስካር’ ሽልማት ሲቀበል የመጀመሪያው ጥቁር አሜሪካዊ ነው።

ሚያዝያ ፮

The death of Tewodros.jpg
  • ፲፰፻፷ ዓ/ም - የፋሲካ ማግሥት ዕለት መቅደላ አምባ ላይ የዓፄ ቴዎድሮስ ሠራዊት እና በሎርድ ኔፒዬር የተመራው የእንግሊዝ ሠራዊት ጦርነት ገጥመው፣ ድሉ የእንግሊዞች ሆነ። ንጉሠ ነገሥቱ ዓፄ ቴዎድሮስ በእንግሊዞች እጅ ከመውደቅ እራሳቸውን ማጥፋትን መርጠው ሽጉጣቸውን ጠጥተው ሞቱ። ቀብራቸው በመቅደላ መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ተከናወነ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አብዮት ከተጀመረ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴየልጅ ልጃቸው ልዑል ዘርዓ ያዕቆብ በወቅቱ በሕክምነ ላይ ለነበሩት መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ተጠባባቂ አልጋ ወራሽ እንደሆኑ በይፋ አስታወቁ። ይሄም ማብራሪያ የንጉሠ ነገሥቱ የሁለተኛ ወንድ ልጅ የነበሩት የሟቹ የልዑል መኮንን ወንዶች ልጆች በዕድሜ የዘርዓ ያዕቆብ ታላላቆች ቢሆኑም ለዘውዱ ውርስ ቅደም ተከተል ግን ከአስፋ ወሰን ወንድ ልጅ ተከታይ እንደሆኑ አረጋግጧል።
  • ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - የኡጋንዳው አምባ ገነን ኢዲ አሚን በታንዛኒያ ሠራዊት እርዳታ ከተገለበጠ በኋላ ዩሱፍ ሉሌ የአገሪቱ አዲስ ፕሬዚደንት በመኾን ቃለ መሀላቸውን ፈጸሙ።
  • ፲፰፻፶፯ ዓ/ም - አሥራ ስድስተኛው የአሜሪካው ፕሬዚደንት አብርሀም ሊንከን የመድረክ ትርዒት በሚያዩበት የፎርድ ቴአትር ውስጥ ነፍሰ ገዳዩ ጆን ዊልክስ ቡዝ በጥይት መታቸው። ሕይወታቸው በማግሥቱ አለፈች።
  • ፲፱፻፶ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአፍሪቃ ተማሪዎች የነጻ ትምህርት ዕድል እንደምትሰጥ በጋና ከተማ አክራ ጉባኤ ላይ የተገኙት ክቡር አቶ አበበ ረታ አስታወቁ፡፡

ሚያዝያ ፰

  • ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ለሚቀጥለው ዓመት የወጪ እቅድ (Budget) ፮ መቶ ፴፫ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር እንደሚሆን ይፋ አደረገ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ትግል ድሬ ዳዋ ላይ ፖሊሶች በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ ተኩስ ከፍተው ስድስት ሰዎችን አቆሰሉ። በምጽዋ እና አስመራ የባሕር ወደብ እና የምድር ባቡር ሠራተኞች አድማቸውን ጀመሩ።
  • ፲፱፻፵፮ ዓ/ም - በግብጽ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ኮሎኔል ጋማል አብደል ናስር ሥልጣን ጨበጡ።
  • ፲፱፻፸፪ ዓ/ም - የቀድሞዋ ደቡብ ሮዴዚያ በአዲሱ ስሟ የዚምባብዌ ሪፑብሊክ ተብላ ተመሠረተች። የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ቀናን ባናና ሆኑ።
  • ፲፮፻፹፰ ዓ/ም - የሆሣዕና በዓል ማግሥት የኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ በነበረችው በጎንደር ከተማ በአንዲት ሴት-አዳሪ ቤት የተነሳ እሳት በ’ግራ ቤት’ አካባቢ ያሉትን ቤቶች በሙሉ ከመፍጀቱም ባሻገር፤ የቅዱስ ጊዮርጊስ፣ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት እና የኢየሱስ አብያተ ክርስቲያናትም ተቃጥለዋል።
  • ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጃማይካን ለመጎብኘት ኪንግስተን ሲገቡ ከመቶ ሺ የማያንሱ ሰዎች የደመቀ አቀባበል አደረጉላቸው። ይሄን ዕለት የ’ራስ ተፈሪያን’ ተከታዮች በየዓመቱ የዚያን የጉብኝት ማስታወሻ አድርገው ያከብሩታል።
  • ፲፱፻፸፪ ዓ/ም - በላይቤሪያ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የጨበጠው የሃምሣ ዓለቃ ዶ ተከታዮች፣ የቀድሞውን ፕሬዚደንት የዊሊያም ቶልበርትን ታላቅ ወንድም ጨምሮ ብዙ የቀድሞ ባለሥልጣናትንና ሚኒስቴሮች ረሸኗቸው።
  • ፳፻፫ ዓ/ም - በመላው ዓለም የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች በዛሬው ዕለት የኢየሱስ ክርስቶስን ስቅለተ ዓርብ በማስታወስ ይዘክራሉ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት በአብዮቱ ፍንዳታ እይተካሄዱ ያሉትን አድማዎችና ሰላማዊ ሰልፎችን ለመግታት የሚወስዳቸውን እርምጃዎች አስታወቀ። የፖስታ ሠራተኞች የአራት ቀን አድማቸውን ጀመሩ።
  • ፲፱፻፹፭ ዓ/ም - በኤርትራ በተካሄደው የሕዝብ ድምጽ ቁጥር አብዛኛው ሕዝብ ከኢትዮጵያ ተገንጥሎ በሉዓላዊነት ራሱን ማስተዳደር መምረጡ ታወጀ።
  • ፲፱፻፺፱ ዓ/ም - የሩሲያ ኅብረት መንግሥት (Russian Federation) የመጀመሪያው ፕሬዚደንት የነበሩት ቦሪስ የልስቲን በተወለዱ በሰባ ስድስት ዓመታቸው አረፉ
  • ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ በሀገራቸውና በጎረቤት አገር ሶማሊያ ጋር ያለውን ጸብ በሰላም ለመፍታት ተልከው ሞቃዲሹ ገቡ።
  • ፲፱፻፺፯ ዓ/ም - ጀርመናዊው ካርዲናል ዮሴፍ ራትዚንገር የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ፪፻፷፭ኛው ጳጳስ ሆነው፣ በቤኔዲክቶስ ፲፮ኛ የጵጵስና ስም ተቀቡ።
  • ፲፱፻፹፯ ዓ/ም - በአሜሪካኦክላሆማ ከተማ ውስጥ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ላይ የተለቀቀ፣ በፈንጂ የተሞላ ተሽከርካሪ ሲፈነዳ በጥቂቱ ሰማንያ ሰዎች ሞተዋል። ከመቶ የማያንሱ ሰዎችም የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በምሥራቅ አፍሪቃ የሚገኙት ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው አንድ አገር መሠረቱ። ይሄም የተዋሕዶ አገር ከሁለቱም ስም በተውጣጣው አዲሱ ስም ታንዛኒያ ተብሎ ተሰየመ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ከደርግ በተላለፈ ትእዛዝ መሠረት፣ የፖሊስ አለቆች፤ የቀድሞ ሚኒስትሮችና ባለ ሥልጣናት ታሠሩ።
  • ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በሶቪዬት ሕብረት ውስጥ የቸርኖቢል የኑክሊዬር መብራት ኃይል ማምረቻ ክፉ አደጋ ተከሰተ። የዚህን አደጋ ክስተት የስካንዲናቪያ አገሮች ይፋ እስካደረጉት ድረስ የሶቪዬት ሕብረት ባለ ሥልጣናት ደፋፍነውት ነበር።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ፍንዳታ የምድር ጦር ሠራዊት አባላት ሦስት ጄኔራሎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በብሪታኒያ በሚገኘው የሊቢያ ቋሚ ልዑካን መሥሪያ ቤት ደጅ ላይ አንዲት እንግላዚዊት የፖሊስ ባልደረባ በመገደሏ ምክንያት የብሪታኒያ መንግሥት ከሊቢያ ጋር የዲፕሎማቲክ ግንኙነቱን ከማቋረጡም ባሻገር፣ በዛሬው ዕለት የሊቢያን ልዑካን ካገር አስወጡ።
  • ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - የኢጣልያ የፋሺስት መሪ የነበረው ቤኒቶ ሙሶሊኒ ከነውሽማው ክላራ ፔታቺ ጋር በቀበሌ ታጣቂዎች ተይዞ በኮሎኔል ካሌሪዶ ከተረሸነ በኋላ አደባባይ ላይ ቁልቁል ተሰቀለ።
  • ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - የሆለታ ጦር ትምሕርት ቤት ብዙ የውጭ እንግዶች በተገኙበት የሃያ አምስተኛ የልደት በዓሉ ተከበረ።
  • ፲፱፻፶፱ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው ቡጢኛ ሙሐመድ አሊ ወደአገሪቱ ጦር ሠራዊት ገብቶ በቪየትናምጦርነት ላይ የማገልገል ግዴታውን እንዲወጣ ቢጠየቅም አሻፈረኝ አለ። የዚያኑ ዕለት የዓለም ቻምፒዮናነቱን ማዕረግ በኒው ዮርክ የአትሌቲክ ባለ ሥልጣን ተገፈፈ።
  • ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በስዊድንፊንላንድ እና ኖርዌይ የሚገኙ የኑክሊዬር ምርመራ ማዕከላት ያልተለመደ የጨረር ጉዳት በከላ በምድር ጠፈር ላይ እንዳገኙ ባስታወቁ በሁለተኛው ቀን የሶቪዬት ኅብረት ባለ ሥልጣናት ቸርኖቢል የሚባለው የኑክሊዬር የመብራት ኃይል ማምረቻ አደጋ እንደደረሰበት ይፋ አደረጉ።
  • ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - አዶልፍ ሂትለር እና የብዙ ዘመን ውሽማው ኤቫ ብሮን በበርሊን ምሽግ ውስጥ ተጋቡ። ሂትለር አድሚራል ካርል ዶኒትዝን የሥልጣን ተተኪው እንደሆነ አስታወቀ።
  • ፲፱፻፹፫ ዓ/ም - ‘ቺታጎንግ’ በተባለ የደቡብ-ምሥራቅ የባንግላዴሽ ግዛት ላይ የተነሳ አውሎ-ነፋስ መቶ ሰላሳ ስምንት ሺ ሰዎችን ሲገድል እስከ አሥር ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች የመኖሪያ ቤታቸው ወድሞባቸዋል።

ሚያዝያ ፳፪'

  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ እንቅስቃሴ የ፪ተኛ ክፍለ ጦር ሰራዊት የአስመራ ከተማን በቁጥጥሩ ስር አዋለ። የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የፖስታ እና ቴሌኮሙኒኬሽን ሚኒስትሩ ሌተና ጄኔራል አሰፋ አየነ በአብዮታዊ ወታደሮች በዚህ ዕለት እስር ላይ ሲውሉ፤ የመከላከያ ሚኒስቴር ደግሞ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበርን ሕገ-ወጥ አድማ ማካሄዱን ካላቆመ እንደሚዘጋ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።
  • ፲፯፻፺፭ ዓ/ም - የአሜሪካ ኅብረት መንግሥት የኦርሊአንስ ግዛት የተባለውን ክፍል ከፈረንሳይ ላይ በ አሥራ አምስት ሚሊዮን ዶላር ገዛ።
  • ፲፰፻፬ ዓ/ም ከዘጠኝ ዓመት በፊት ከፈረንሳይ የተገዛው የኦርሊአንስ ግዛት ሉዊዚያና ተብሎ የአሜሪካ አሥራ ስምንተኛው የኅብረት አባል ሆነ።

ሚያዝያ ፳፬

  • ፲፱፻፵፬ ዓ/ም - ‘ደ ሀቪላንድ-ኮሜት’ የተባለው የዓለም የመጀመሪያው የተሳፋሪ ጄት አየር-ዠበብ የመጀመሪያ በረራውን ከሎንዶን እስከ ጆሃንስበርግ ድረስ አከናወነ።

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ሚያዝያ 25

  • ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - በብሪታንያ ንጉዛት ማርጋሬት ታቸር የመጀመሪያዋ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኑ።

ሚያዝያ ፳፯

በአገራችን ታሪክ ሁለት የሐዘንና የደስታ ቀኖችን ትዘክራለች። ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም የፋሽሽት ኢጣልያ ጄነራል ባዶሊዮ በጊዚያዊ ድል አድራጊነት አዲስ አበባን ከቁጥጥሩ ሥር ያደረገበትና ነጻነታችንን ያጣንበት ዕለት ሲሆን ልክ በአምስት ዓመቱ በ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም ደግሞ ንጉሠ ነገሥቱ በአርበኞች አባት እናቶቻችን ትግል፣ በእንግሊዝ እና ግብረአበሮቿ ዕርዳታ በድል አድራጊነት አዲስ አበባ የገቡበት ዕለት ነው።

  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም የአውሮፓ ሸንጎ (The Council of Europe) ይሄንን ዕለት “የአውሮፓ ቀን” ብሎ ሰይሞታል
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በብሔራዊ የድል በዐል ላይ ባደረጉት ንግግር፣ በአገሪቱ የተለኮሰውን የአብዮት እሳት በተመለከተ ከውጭ የሚራገብ ነቀርሳ እንደሆነና ኢትዮጵያውያን በሙሉ በሕብረት እንዲቃወሙት ጥሪያቸውን አሰሙ።

ሚያዝያ ፳፰

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ሚያዝያ 29

  • ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ።

...


[ለማስተካከል] ነሐሴ

፲፱፻፫ ዓ/ም አንድ ሚሊዮንኛው የአዕምሯዊ ንብረት (patent) በዩናይትድ ስቴትስ የአዕምሯዊ ንብረት ጽ/ቤት ተመዘገበ። ይኼም የፍራንሲስ ሆልተን ውስጣዊ ቱቦ አልባ ጎማ ነው።

፲፱፻፷፮ ዓ/ም የአሜሪካ ፕሬዚደንት ሪቻርድ ኒክሰን የ“ወተርጌት ቅሌት” (watergate scandal) ተብሎ በሚታወቀው ጉዳይ ምክንያት የፕሬዚደንት ስልጣናቸውን በማግሥቱ እንደሚለቁ ይፋ አደረጉ።

፲፱፻፹፪ ዓ/ም ኢራቅ ጎረቤቷን ኩዌትን በመውረር የኢራቅ አካል አደርገች። ይኼም ድርጊት የመጀመሪያውን የባህረ ሰላጤ ጦርነት የጫረው ድርጊት ነው ፲፩፻፷፭ ዓ/ም - ሁለት ምዕተ ዓመት የፈጀው የፒሳ ግንብ ሥራ ተጀመረ።

፲፱፻፳፰ ዓ/ም -ጄሲ ኦዌን የተባለው ጥቁር አሜሪካዊበርሊንናዚ ጀርመን ከተማ በሚካሄደው አሥራ አንደኛው ኦሊምፒክ ውድድር ላይ አራተኛ የወርቅ ኒሻን አሸነፈ።

፲፱፻፴፯ ዓ/ም -ናጋሳኪ የተባለችው የጃፓን ከተማ ላይ የአሜሪካ የቦንብ አውሮፕላን የጫነውን አቶሚክ ቦንብ ሲጥል ሰላሳ ዘጠኝ ሺህ ሰዎች ወዲያው ሲሞቱ ከተማዋ ወድማለች።

፱፻፷፮ ዓ/ም - የአሜሪካ ፕሬዚደንት ሪቻርድ ኒክሰንወተርጌት ቅሌት በተሰኘው ጉዳይ ምክንያት ስልጣናቸውን ሲለቁ፣ ምክትል ፕሬዚደንቱ ጄራልድ ፎርድሥልጣኑን ተረክበው ፴፰ኛው ፕሬዚደንት ሆኑ። ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ነሐሴ 3

  • ፲፭፻፲፩ ዓ/ም ፈርዲናንድ ማጄላን ከአምስት የእስፓኝ መርከቦች ጋር ዓለምን በባሕር ለመዞር ሴቪል ከሚባል ሥፍራ ጉዟቸውን ጀመሩ። ማጄላን በመሃል ላይ ፊሊፒን ደሴቶች ላይ ሲሞት ጉዞውን ምክትሉ ሴባስቲያን እልካኖ ጨረሰ።
  • ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - የፓሪስ ከተማ የሙቀት ሞገድ እስከ አርባ አራት ዲግሪ ሴልሲዩስ ደርሶ ባስከተለው ሰበብ ወደ መቶ አርባ አራት ያህል ሰዎች ሞቱ።

ነሐሴ ፮ የዓለም ዓቀፍ የግራኞች ቀን በመባል ከዓለም ጠቅላላ ሕዝብ ቁጥር ከሰባት እስከ አስር በመቶ ይሆናሉ ተብለው የሚገመቱት ግራኞች የሚገጥሟቸውን ዕለታዊ ችግሮችን ለማስታወስ በ፲፱፻፷፰ ዓ/ም ተጀምሮ በየዓመቱ ይከበራል።

  • ፲፱፻፪ ዓ/ም - በክራይሚያ ጦርነት “የኩራዟ ዕመቤት” በሚል ቅጽል ስም የታወቀችው እንግሊዛዊቷ የመጀመሪያ ዘመናዊት አስታማሚ ፍሎሬንስ ናይቲንጌይል አረፈች።
  • ፲፱፻፲ ዓ/ም - በሙኒክ የባቫሪያ የሞተር ፋብሪካ (Bayerische Motoren Werke AG (BMW)) ተመሠረተ።

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ነሐሴ 8

  • ፲፱፻፴፱ ዓ/ም - ለ፫ መቶ ፴፬ ዓመታት በብሪታኒያንጉዛት ሥር በቅኝ ግዛትነት የኖረችው ሕንድ በዚህ ዕለት ነጻነቷን ተቀዳጀች። እስላማዊው የሰሜን-ምዕራብ አካልም በዚሁ ዕለት ተገንጥሎ ፓኪስታን በሚል ስም አዲስ አገር ተፈጠረ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት የሥልጣን ሽግግር፤ ደርግ የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት የጡረታ ሚኒስቴር በቁጥጥሩ ሥር አደረገ።
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር ደርግ የንጉሠ ነገሥቱን ችሎት እና የዘውድ ምክር ቤት በመሻር ሕገ-ወጥ ከማድረጉም ባሻገር በዚሁ ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ታጣቂ ወታደሮችን እና ታንክ ጭምር በማሠማራት የመሣሪያ ኃይሉን አሳየ። በተያያዘ ሁኔታ ኤርትራውያንን የሚወክሉ የፓርላማ አባላት ሥራቸውን እንደሚለቁ አስታወቁ።
  • ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያብሪታኒያ ዋና መላክተኛ (Ambassador) ዳግላስ ራይት (Douglas A. H. Wright) በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ።
  • ፲፱፻፱ ዓ/ም - በግሪክ ሁለተኛ ከተማ በተሰሎንቄ (Thessaloniki) የተከሰተ የእሳት አደጋ የከተማዋን ቤቶች በቁጥር ከሦስት እጅ አንድ በማውደሙ እስከ ፸ሺ ነዋሪዎችን ውጭ አዳሪ ቤት አልባ አድርጓቸዋል።
  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ(International Olympic Committee - IOC) ዘረኛውን የደቡብ አፍሪቃ መንግሥት ‘አፓርታይድ’ በሚል መርሆ የሚያካሂደውን የግፍ አስተዳደር እንዲያወግዝ ያቀረበለትን ጥሪ ባለመቀበሉ በዚህ ዓመት ቶክዮ ከተማ ላይ በተዘጋጀው ፲፰ኛው የኦሊምፒክ ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ አገደው።
  • ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - በደብረ ዳሞ ገዳም ብዙ ታሪካዊ ፤ ሃይማኖታዊ እና ምሥጢራዊ የመጽሐፍ ቅርሶችን ያካተተው ቤተ መጻሕፍትና ሃይማኖታዊ 'ንዋየ ቅድሳት' የተከተቱበት ግምጃ ቤት ባልታወቀ ምክንያት በእሳት አደጋ ቃጠሎ ወደሙ

ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ነሐሴ 14 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ነሐሴ 15 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች በዛሬው ዕለት በየዓመቱ ነሐሴ ፩ ቀን የሚጀመረውን ጾመ ፍልሰታ የሚፈቱበት ቀን ነው።

  • ፲፰፻፶፮ ዓ/ም - በጦርነት የተማረኩ ሰዎችን መብት ስለማስጠበቅና ስለማክበር የተዘጋጀው የጋራ ድንጋጌ (የጀኒቫ ኮንቬንሽን) በአሥራ ሁለት መሥራች አገሮች ተፈረመ። የቀይ መስቀል ማኅበርም አብሮ ተመሠረተ።
  • ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ሸንጎ (International Olympic Committee) ሮዴዚያን (አሁን ዚምባብዌ) በዘረኛነቷ ምክንያት አባልነቷን ሠረዘ።

ነሐሴ 17 ቀን: ነጻነት ቀን በሮማንያኡምህላንጋ (የሸምበቆ) በዓል በስዋዚላንድ...

Lunar orbiter 1 (large).jpg

ነሐሴ 18 ቀን: የባንዲራ ቀን በላይቤሪያ፤ ብሔራዊ በዓል በዩክራይንሲዬራ ሌዎን...

Situationskärtchen von Kanton, Makao, Hongkong.jpg

ነሐሴ 19 ቀን: ብሔራዊ በዓል በዩሩጓይና በፊልፒንስ...

Voyager spacecraft.jpg

ነሐሴ 20 ቀን: ዓመት በአል በናሚቢያ፤ የሱልጣን ልደት በዓል በዛንዚባር...

Namibia coa.PNG

ነሐሴ 21 ቀን: ነጻነት በዓል በሞልዶቫ ...

Gaspard deColigny.jpg

ነሐሴ 22 ቀን: ነጻነት በዓል በሆንግኮንግ...

Mlkdreamspeech.jpg

ነሐሴ 23 ቀን: አብዮት በዓል በስሎቫክያ...

Battle-of-Long-Island-Map-sml.jpg

ነሐሴ 24 ቀን: የድል ቀን በቱርክ (የ 1922 ዱምሉፒናር ድል ለማስታወስ)፤ የቅዱስ ሮዛ በዓል በፔሩ...

Thurgood-marshall-2.jpg

ነሐሴ 25 ቀን: የነጻነት በዓል በማለይዝያትሪኒዳድኪርግዝስታን...

Kwangmyongsong.jpg

ነሐሴ 26 ቀን: የሕገመንግስት ቀን በስሎቫኪያ...

Flag of Uzbekistan.png

ነሐሴ 27 ቀን: ብሔራዊ በዓል በቬትናም...

Cetshwayo-c1875.jpg

ነሐሴ 28 ቀን: ነጻነት በዓል በቃጣር...

Coat of arms of Qatar.svg

ነሐሴ 29 ቀን: የአባቶች ቀን በአውስትራሊያኒው ዚላንድ...

AR Little Rock Nine.jpg

ነሐሴ 30 ቀን: አስተማሮች ቀን በሕንደኬ (የራዳክሪሽናን ልደት)...

GreatFireOfLondon1666 VictorianEngravingAfterVisscher300dpi.jpg

ጳጉሜ 1 ቀን: ነጻነት ቀን በስዋዚላንድ፣ አንድነት ቀን በቡልጋሪያ...

Swaziland flag 300.png

ጳጉሜ 2 ቀን: ነጻነት ቀን በብራዚል፣ የድል ቀን በሞዛምቢክ...

Archbishop-Tutu-medium.jpg

ጳጉሜ 3 ቀን: ብሄራዊ በአል በአንዶራ...

General of the Army Dwight D. Eisenhower 1947.jpg

ጳጉሜ 4 ቀን: ሬፑብሊክ ቀን በስሜን ኮርያ፣ ነጻነት ቀን በታጂኪስታን፣ ብሄራዊ ቀን በቡልጋርያ...

Elcano.jpg

ጳጉሜ 5 ቀን: ብሄራዊ ቀን በጂብራልታር...

Österreich-Ungarns Ende.png

ጳጉሜ 6 ቀን

TheToughest.jpg

የኔ መሣርያዎች

Variants
Actions
የማውጫ ቁልፎች
ጠቃሚ መሣሪያዎች