ዓመት በዓላት እና ታሪካዊ ማስታወሻዎች
እንኳን ለ ፳፻፬ ዓመተ ምሕረት በሰላም አደረሳችሁ!!!
ማውጫ |
[ለማስተካከል] ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች
[ለማስተካከል] መስከረም
መስከረም 1 ቀን: ዕንቁጣጣሽ፣ ብሄራዊ ቀን በካታሎኒያ እስፓንያ...
- 1507 - የፖሎኝ ሠራዊት በኦርሻ ውግያ በሩስያ ላይ አሸነፈ።
- 1806 - የአሜሪካ መርከቦች በኤሪ ሐይቅ በእንግሊዝ አሸነፉ።
- 1890 - በላቲመር ፔንሲልቬኒያ ፖሊሶች 19 የማዕደን ሰራተኞች በእልቂት ገደሉ።
- 1915 - የእንግሊዝ አስተዳደር በፍልስጤም ጀመረ።
- 1982 - የብረት መጋረጃ በኰሙኒስት ሃንጋሪና በኦስትሪያ መሃል ተከፍቶ ወዲያው ብዙ ሺህ ጀርመኖች ወደ ምእራብ ፈለሱ።
- 1994 - አራት አውሮፕላኖች በአረብ ታጣቂዎች ተሰርቀው በአለም ንግድ ሕንጻና በፔንታጎን ተጋጭተው 3000 ያህል ሰዎች ተገደሉ።
መስከረም 2 ቀን: ብሄራዊ ቀን በኬፕ ቨርድ...
- 1184 - በመስቀል ጦርነት የእንግሊዝ ንጉስ 1 ሪቻርድ በሳላዲን ላይ በአርሱፍ ውግያ አሸነፈ።
- 1890 - የዳግማዊ ምኒልክ ሻለቆች የካፋን ንጉስ ጋኪ ሸሮቾ በማማረክ ያንን መንግስት ጨረሱ።
- 1935 - የጓደኞች ወታደርና 1,800 የጣልያ እስረኞች ተሸክማ ላኮኒያ የምትባል መርከብ አፍሪካን ስትቀርብ በጀርመኖች ተተኩሳ ሰጠመች።
- 1970 - የጸረ-አፓርትሃይድ ወኪል ስቲቭ ቢኮ በደቡብ አፍሪካ ፖሊስ ታስሮ ተገደለ።
- 1972 - ነጻነት ለቨንዳ ተሰጠ - ይህ ግን ከደቡብ አፍሪካ ውጭ አልተቀበለም።
- 1985 - መይ ካሮል ጀሚሶን በጠፈር የመጀመርያው ጥቁር አሜሪካዊት ሆነች።
መስከረም 3 ቀን
- 1883 - ሳልስበሪ ሮዴዚያ ተመሰረተች።
- 1893 - በፊሊፒንስ ጦርነት የፊሊፒንስ ተዋጊዎች በአሜሪካ ሠራዊት ላይ ድል አደረጉ።
- 1899 - በአውሮፓ የተደረገ መጀመርያው የአውሮፕላን በረራ።
- 1907 - በ1ኛ አለማዊ ጦርነት የደቡብ አፍሪካ ጭፍሮች ጀርመን ደቡብ-ምዕራባዊ አፍሪካ (ናሚቢያ) ወረሩ።
- 1952 - መጀመርያው ሰው ሰራሽ መንኮራኩር (የሩሲያ) ጨረቃን ደረሰ።
- 1996 - ስዊድን በምርጫ ለዩሮ እምቢ አለች።
መስከረም 4 ቀን
- 1534 - ሳንቲያጎ ቺሌ በኗሪ አርበኞች ጠፋ።
- 1676 - የአውሮፓ ሠራዊት በቪኤና ውግያ ቱርኮችን አሸነፉ።
- 1894 - የአሜሪካ ፕሬዚዳን መኪንሊ ተተኩሰው ሲሞቱ ቴዮዶር ሮዝቬልት ፕሬዚዳን ሆኑ።
- 1953 - "ኦፐክ" - የዘይት አስወጪ አገሮች ድርጅት - ተመሰረተ።
መስከረም ፭ ቀን
- ፲፫፻፵፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያዊው መነኩሴ አባ ኤውስጣቴዎስ በስደት በሚኖሩበት አርመን አገር ላይ ሞቱ።
- ፲፭፻፴፫ ዓ/ም -አጼ ልብነ ድንግል በነገሡ በ፴፪ ዓመታቸው ሐሙስ ዕለት ደብረ ዳሞ ላይ አረፉ። የንጉሠ ነገሥትነት ሥልጣን፣ ዘውድና ዙፋናቸው በዚሁ ዕለት ወደልጃቸው የ፲፰ ዓመቱ አጼ ገላውዴዎስ (ስመ መንግሥት፣ አፅራር ሰገድ) ተላለፈ።
- ፲፮፻፪ ዓ/ም - የእንግሊዝ መርከበኛ ሄንሪ ሀድሰን (በዛሬዋ ኒው ዮርክ ከተማ) በስሙ የተሠየመውን የሀድሰን ወንዝን አገኘ።
- ፲፰፻፭ ዓ/ም - የናፖሌዎን ወራሪ ሠራዊት እንዳይማርከው የሩሲያ ሰራዊት የመስኮብን ከተማ አቃጠለ።
- ፲፰፻፹፫ ዓ/ም በወንጀላዊ ልብ ወለድ ጽሑፎቿ “አቻ የላት” የምትባለው እንግሊዛዊቷ ደራሲ አጋታ ክሪስቲ (Agatha Christie)፣ ቶርኪ (Torquay) በምትባል ከተማ ተወለደች። (ክሪስቲ በ፲፱፻፷፰ ዓ/ም ሞተች)
- ፲፱፻፯ ዓ/ም - የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ላይ ታንክ የተባለው የጦር መሣሪያ አገልግሎት ላይ ዋለ።
- ፲፱፻፵፭ ዓ/ም - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤርትራና ኢትዮጵያ በ«ኅብረታዊ መንግሥት» እንዲዋሃዱ አጸደቀ።
- ፳፻፫ ዓ/ም - በሁለት ትላልቅ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ድርጅቶች የመሪዎች መፈንቅል ተፈጸመ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ላለፉት ስድስት ዓመት ያገለገሉት አቶ ግርማ ዋቄ፣ ሥራቸውን ለቀቁ። አቶ ግርማን የሚተኳቸው ምክትላቸው አቶ ተወልደ ገብረማርያም ይሆናሉ ይባላል። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ቴሌኮሙኒኬሽን ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ላለፉት አራት ዓመታት ያገለገሉት አቶ አማረ አምሳሉም ሥራቸውን ለቀቁ
መስከረም ፮ ቀን
- ፬፻፷፱ - ሮሙሉስ አውግስጦስ የመጨረሻው ምዕራብ ሮማ ንጉስ ወደቀ።
- ፲፮፻፶፩ - ኦሊቨር ክሮምዌል ዓረፉ።
*፲፱፻፸፩ ዓ.ም. - የግብጽ ፕረዚዳንት አንዋር ሳዳት እና የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ሜናኽም ቤጊን በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጂሚ ካርተር ሸምጋይነት፣ ከ ፲፪ ቀናት የምሥጢር ድርድር በኋላ፤ በካምፕ ዴቪድ የካምፕ ዴቪድ ስምምነት ተፈራረሙ።
- ፫፻፹፯ዓ/ም - የሮማ ንጉዛት ክርስቲያናዊ ቄሳር ቀዳማዊ ቴዎዶስዮስ ዘውዱን ለመንጠቅ የተነሳውን አረመኔያዊ የምዕራብ ሮማ መሪ አውግንዮስን በፍሪጊዱስ ውግያ ሲያሸንፍ የሮማ ክርስቲያናዊ ንጉዛት በመጽናቱ የክርስትና ሃይማኖት በአውሮፓ ቀደምትነትን እንዲይዝ አድርጎታል።
- ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሁለተኛው ዋና ፀሐፊ፣ ሲዊድናዊው ዳግ ሀመርሾልድ በ’አየር ዠበብ አደጋ’ በቀድሞዋ ሮዴዚያ (የአሁኗ ዚምባብዌ) ላይ ሞቱ።
- ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. - የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ክቡር ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ ፤ በጣሊያን ወረራ ጊዜ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጋር እንግሊዝ አገር በስደት ላይ እንዳሉ፣ በተወለዱ በስድሳ ዓመታቸው ዓረፉ።
- ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ዛንዚባር ደሴት ላይ የተወለዱት የታንዛንያው ዜጋ ሳሊም አህመድ ሳሊም ስምንተኛው የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ዋና ጸሐፊ በመሆን ሥልጣኑን ከ ኤዲ ኡማሩ ተረከቡ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የቀድሞው የኢትዮጵያ መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ፀሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተ-ወልድ ለደርግ የምርመራ ኮሚሽን ‘ዓለም በቃኝ’ እስር ቤት ሆነው ያዘጋጁትን “የታሪክ ማስተወሻ” ላኩ። በመስከረም ወር ፲፱፻፹፮ ዓ/ም በጦብያ መጽሔት ላይ የወጣው ይኼው የትሪክ ማስታወሻ ለሕይወት ታሪካቸው ዋቢ ምንጭ ሆኗል።
- ፲፱፻፸፪ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የነበረው ኢቲ-ኤጂዩ (ET-AGU) ዲ-ሲ ፫ (Douglas C-47 A -20-DK) አየር ዠበብ በደቡብ-ምዕራብ ኤርትራ፣ ከባረንቱ ማረፊያ ሊነሳ ሲያኮበኩብ በአፍንጫው ተደፍቶ ሲከሰከስ ከጥቅም ውጭ ሆኗል።
- ፲፱፻፸፪ ዓ.ም - የቀድሞዋ መካከለኛ አፍሪቃ ንጉዛት መንግሥት (Central African Empire) መሪ ዣን ቢዴል ቦካሳ በፈረንሳይ መንግሥት ዕርዳታ በተደራጀ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ተወገዱ።
- ፳፻፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ በአዋጅ ቁጥር 654/2001 መሠረት በየዓመቱ በመስከረም ወር በሁለተኛው ሳምንት ዕለተ ሰኞ እንዲከበር በተወሰነው ድንጋጌ የኢትዮጵያ ብሔራዊ አርማ ያለበት ሰንደቅ ዓላማ ቀን።
- ፲፮፻፳፭ ዓ/ም - በዙፋን ስማቸው "መልአክ ሰገድ" የሚባሉት ዓፄ ሱስኒዩስ በጽኑ ደዌ ታመው በዕለተ ዐርብ ሞቱ፤ አዘዞ ላይ ተቀበሩ።
- ፲፱፻፵ ዓ.ም - የክቡር ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ አጽም በስደት ዘመን አርፈው ከተቀበሩበት ከእንግሊዝ አገር ወደ ውድ አገራቸው ኢትዮጵያ ተመልሶ በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ተቀበረ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የሥራ ሚኒስትር ከአሜሪካ ጉዟቸው ሲመለሱ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁለት ቦይንግ ፯መቶ፳-ቢ (Boeing 720B) ጄት አውሮፕላኖች መግዣ እና ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የሚውል ብድር ከ ኤክሲም ባንክ (Export Import Bank) ጋር የስምምነት ውል መፈራረማቸውን ይፋ አደርጉ።
- ፳፻፪ ዓ/ም በምዕራብ ጐጃም የአንድነት ቅርንጫፍ ቢሮ አስተባባሪዎች ላይ ድብደባ ተፈጸመ
- ፲፱፻፴፮ ዓ.ም. - የሙሶሊኒ አዲስ ፋሺስታዊ መንግሥት በአዶልፍ ሂትለር ግፊት እና ድጋፍ 'የጣልያን ሕብረተሰባዊ ሪፑብሊክ' በሚል ስም በሰሜን ጣልያን ጀመረ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. - ቀድሞ "የፈረንሣይ ሱዳን" የተባለው ቅኝ ግዛት የማሊ ሪፑብሊክ ተብሎ ነጻነቱን አወጀ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ የሠራተኞች ማኅበር ፕሬዚደንት፤ ምክትል ፕሬዚደንት እና ዋና ጸሐፊ አዲስ ሥልጣን በያዘው የደርግ ወታደራዊ መንግሥት ትዕዛዝ ተይዘው ታሠሩ።
- ፲፱፻፺፱ ዓ/ም የህውሐት ማእከላዊ ኮሚቴ አቶ መለስ ዜናዊ የድርጅቱ ሊቀ መንበር ሆነው እንዲያገለግሉ በድጋሚ መረጠ፡ ...
- ፮፻፲፭ ዓ/ም - ነቢዩ መሐመድ ከመካ እስከ መዲና ያደረገውን የሱባዔ ጉዞ (ሂጅራ) ፈጸመ።
- ፲፱፻፷፩ ዓ/ም-ስዋዚላንድ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሆነች።
- ፲፱፻፷፱ ዓ/ም - በአፍሪቃ አኅጉር ደቡባዊ አካል፣ በ ኢያን ስሚዝ የሚመራው የሮዴዚያ (የአሁኗ ዚምባብዌ) የነጭ አስተዳደር መንግሥቱን ለበዢው የጥቁር ሕዝብ በሁለት ዓመት ውስጥ ለማስረከብ ተስማማ።
- ፲፱፻፵፫ ዓ/ም -የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ በሰጠው ውሳኔ መሠረት ፥ኤርትራ ከኢትዮጵያጋራ ተዋሃደች።
- ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የየመን አረባዊ ሪፑብሊክ ተመሠረተ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በፈረንሳይ እና ብሪታንያ በኅብረት የተሠራው ‘ኮንኮርድ’ የተባለው አየር ዠበብ ለመጀመሪያ ጊዜ የአትላንቲክ ውቅያኖስን በማቋረጥ የፍጥነት ክብረ ወሰን አስመዘገበ።
- ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - ‘ጁላ’ (MV Joola) የተባለች የሴኔጋል የንግድ መርከብ ከተፈቀደላት የሰው ጭነት በላይ ሦስት እጥፍ ጭና ስትጓዝ ከጋምቢያ ጠረፍ አካባቢ ላይ ሰምጣ ወደ ፩ሺ ፰፻፷፫ መንገደኞች ሕይወታቸውን አጡ።
- ፲፱፻፱ ዓ/ም - በትልቁ የመስቀል በዓል ቀን መኳንንቱ ከነሠራዊቱ፤ ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስና እጨጌ ወልደ ጊዮርጊስ ከነካህናቱ በተሰበሰቡበት በ ፲ ነጥብ የተዘረዘረው የልጅ እያሱ ወንጀል ተነቦ እሳቸውን ሽረው ወይዘሮ ዘውዲቱን ንግሥት፣ ደጃዝማች ተፈሪን ራስ ብለው አልጋ ወራሽና የመንግሥቱ እንደራሴ ተደረጉ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - በፋሺስት ወረራ ጊዜ ኢትዮጵያን በመደገፍ በእንግሊዝ አገር እርዳታ በመሰብሰብ፣ የኢጣልያን ግፍ እና የምዕራባውያንን ድክመት በማጋለጥ የታገሉት ዕመት ሲልቪያ ፓንክኸርስት አረፉ። ሥርዓተ ቀብራቸው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በተገኙበት በመንግሥታዊ ሥርዓት በኢጣሊያ ጦርነት ሰማዕት ለሆኑ ጀግኖች በተዘጋጀው መካነ መቃብር፣ በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡
- ፲፱፻፶፬ ዓ/ም -ሴየራ ሌዎን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሆነች።
- ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ሁለት የአሜሪካ የጦር አየር ዠበቦች፣ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለምን ዙሪያ በአየር በረራ በመቶ ሰባ አምሥት ቀን ካከናወኑ በኋላ ሲያትል ላይ አረፉ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - ማሊ እና ሴኔጋል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባላት ሆኑ።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - በአፍሪቃ አኅጉር ላይ የመጀመሪያውን ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ያካሄዱት የግብጽ ሁለተኛ ፕሬዚደንት የነበሩት ኮሎኔል ጋማል አብደል ናስር አረፉ።
- ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - በሮማው የቅዱስ ጴጥሮስ መንበር በፓፓነት የተመረጡት ቀዳማዊ ዮሐንስ ጳውሎስ በተመረቁ በ ሰላሳ ሦስት ቀናቸው ሞቱ።
- ፳፻፩ ዓ/ም - በጅጅጋ ከተማ "አንድነት" በተባለ ሆቴል በተከሰተ ፍንዳታ አራት ሰዎች ሲሞቱ አስር ሰዎች ቆስለዋል።
- ፲፱፻፴፮ ዓ/ም - የሁለተኛው የዓለም ጦርነት መጀመሪያ ላይ የፋሺስት ኢጣልያ ሠራዊት አገራችንን ኢትዮጵያን ሲወር በድል አድራጊነት አዲስ አበባ የገባው ማርሻል ፒዬትሮ ባዶልዮ፤ ተሸናፊዋን አገሩን በመወከል የሽንፈቱን ስምምነት ፈረመ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስብሰባ ከዚያ በፊት ታይቶም ተሰምቶም በማይታወቅ ሁኔታ በ ሶቪዬት ኅብረት መሪ ኒኪታ ክሩስቾቭ ድንፋታ ተረበሸ። በዚህ ስብሰባ ላይ ክሩስቾቭ ጫማቸውን አውልቀው ጠረጴዛቸውን በመቀጥቀጥ ዓለምን አስገርመዋታል።
- ፳፻፪ ዓ/ም - በሳሞዋ ደሴቶች አጥቢያ የተከሰተው፣ በ ‘ሪክተር ሚዛን’ ስምንት ነጥብ ያስመዘገበው የመሬት እንቅጥቅጥ ‘ሱናሚ’ (tsunami) የሚባለውን የባሕር ነውጥ አስከተለ።
መስከረም ፳ ቀን
- ፲፱፻፶፱ - የብሪታንያ ቅኝ ግዛት የነበረችው የደቡብ አፍሪካዋ ቤችዋናላንድ ነጻነቷን ተቀዳጅታ የቦትስዋና ሪፑብሊክ ተብላ ተሰየመች። ሰሬትሴ ካማ የመጀነሪያው ፕሬዚደንት ናቸው።
- ፲፱፻፹፭ - ሆዜ ኤድዋርዶ ዶስ ሳንቶስ በአንጎላ ፕሬዚዳንት ምርጫ ጆናስ ሳቪምቢን አሸነፉ።
መስከረም ፳፩ቀን
በዚህ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅድስት ማርያምን በዓል በማሰብ ትዘክረዋለች።
- ፲፬፻፵፮ ዓ/ም -ዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትን ግማደ መስቀሉንና ሌሎች ብዙ የቤተ ክርስቲያን ንዋያተ ቅድሳትን አምጥተው በግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም አስቀመጡ።
- ፲፱፻፵፩ ዓ.ም -ማኦ ዘዶንግ የቻይና ሕዝባዊ ሪፑብሊክን መመሥረት ይፋ አደረገ።
- ፲፱፻፶፬ ዓ.ም - በአሜሪካ የጥቁሮች ሰብዓዊ መብት ትግል ጄምስ መሬዲዝ የተባለውን ጥቁር ተማሪ ወደ ሚሲሲፒ ዩኒቨርሲቲ መግባት በተከሰተው ግጭት ሁለት ሰዎች ሲሞቱ ሰባ አምሥት ሰዎች ደግሞ የአካል ጉዳት ደረሰባቸው።
- ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - ለሟቹ የግብጽፕሬዚደንት ጋማል አብደል ናስር የቀብር ስርዓት የወጡ ወደ አምሥት ሚሊዮን የሚገመቱ አዘነተኞች በተነሳ ግርግር እና ግፊያ ብዙ ሰዎች ተጨፍልቀው ሞቱ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በፊሊፒንስ ከተማ ማኒላ ላይ በተካሄደው የቡጢ ውድድር ሞሐመድ አሊ ባላጋራውን ጆ ፍሬዘርን ከአሥራ አራት ዙር ግብግብ በኋላ በነጥብ ብልጫ አሸነፈ።
- ፲፰፻፷፪ ዓ.ም. ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲ ፤ ወይም ማሃትማ ጋንዲ በዛሬው ዕለት ጉጅራት በሚባለው የህንድ ክፍለ ሀገር ውስጥ ፖርባንዳር በምትባል የጠረፍ ከተማ ተወለደ።
- ፲፱፻፲፰ ዓ.ም. በብሪታንያ የስኮትላንድ ተወላጅ የሆነው ጆን ሎጊ ቤርድ ለመጀመሪያ ጊዜ ቴሌቪዥን ፈተነ።
- ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. ጊኒ ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛትነት ተላቃ ነጻነቷን ተቀዳጀች።
- ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. - በጄነራል ኤሚልዮ ደቦኖ የሚመራው የፋሽሽት ኢጣልያ ኃይል ኢትዮጵያን ወረረ።
- ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. - የጀርመን ዳግመኛ መወሐድ፦ ምስራቃዊ የጀርመን አገር የነበረችው የጀርመን ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ከምዕራባዊው የጀርመን አገር ጋር ተቀላቅላ ክልሏ የጀርመን ፈዴራላዊ ሪፑብሊክ አካል ሆኖ ሕዝቦቿም የአውሮፓ ሕብረት ዜጎች ሆኑ።
- ፲፱፻፹፭ ዓ/ም - በሞቃዲሹ የሶማሌውን የጦር ዓለቃ ሞሐመድ ፋራ አይዲድን ለመያዝ በተደረገው ሙከራ አሥራ ስምንት የአሜሪካ ወታደሮች ሲሞቱ አንድ ሺ ያህል ሶማሌዎችም ሕይወታቸውን አጥተዋል።
- ፲፭፻፸፭ ዓ.ም. - የካቶሊኩ ቤተ ክርስትያን ፓፕ ግረጎሪ ፲፫ኛ በኢጣልያ ፤ በፖላንድ ፤ በፖርቱጋል እና በእስፓንያ አገሮች የግሪጎርያዊ ዘመን አቆጣጠርን መሠረተ።
- ፲፭፻፺ ዓ.ም. - የንግሥ ዘመናቸውን (ከ ፲፭፻፶፯ ዓ.ም. እስከ ፲፭፻፺ ዓ.ም.) ሙሉ በቀይ ባሕር በኩል ቱርኮችን (ኦቶማን)፤ በደቡብ የኦሮሞዎችን ጥቃት በመከላከል ያሳለፉት የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ሰርጸ ድንግል በተወለዱ በ ፵፯ ዓመታቸው አረፉ።
- ፲፰፻፲፯ ዓ.ም. - ሜክሲኮ አዲስ ሕገ መንግሥቷን አጽድቃ የፌዴራል ሪፑብሊክ ሆነች።
- ፲፰፻፳፫ ዓ.ም. - ከኔዘርላንድ ጋር በመለያየት የቤልጂግ ሉዓላዊ አገር ተመሠረተ።
- ፲፰፻፵፮ ዓ.ም. - የኦቶማን ግዛት በሩሲያ ላይ ጦርነት አወጀ። ባንድ በኩል ሩሲያ፤ በሌላው በኩል ደግሞ ብሪታንያ፣ ፈረንሳይ እና የኦቶማን ግዛት በትብብር የተዋጉት የሁለት ዓመት በላይ ጦርነት የክራይሚያ ጦርነት የሚባለው ነው።
- ፲፱፻፫ ዓ.ም. - የፖርቱጋል ንጉሥ ማኑዌል ፪ኛ ወደብሪታንያ ኮብልሎ አገሪቱ ሪፑብሊክ ሆነች።
- ፲፱፻፶ ዓ.ም. - ሩሲያ የመጀመሪያዋን ሰው ሰራሽ ሳቴላይት፣ ስፑትኒክ ፩ መሬትን ለመዞር ተኮሰች።
- ፲፱፻፶፱ ዓ.ም. - የብሪታንያ ቅኝ ግዛት የነበረችው፣ በቀድሞ ስሟ ባሱቶላንድ ትባል የነበረችው የደቡባዊ አፍሪካ አካል፣ ነጻነቷን ተቀዳጅታ የሌሶቶ ንጉሥ መንግሥት ተባለች።
ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/መስከረም 25 መስከረም ፳፮ ቀን
- ፲፬፻፬ ዓ/ም - በ፲፫፻፸፭ ዓ/ም በኢትዮጵያ ዙፋን ላይ ተቀምጠው ለሃያ ዘጠኝ ዓመት የነገሡትና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ግማደ መስቀል ወደኢትዮጵያ ያስመጡት ዳግማዊ ዓፄ ዳዊት ፈረሳቸው ረግጧቸው ሞቱ።
መስከረም ፳፯ ቀን
- ፲፱፻፲፪ ዓ/ም - የሆላንድን ዓርማ ያዘለው ‘ኬ. ኤል. ኤም’ (KLM) የተባለው እና ከምሥረታው ጀምሮ እስካሁን ስሙንም ሆነ ዓርማውን ሳይቀይር በመቆየት አንደኝነትን ያስመዘገበው ዓየር መንገድ ተመሠረተ።
- ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - ልዑል ራስ ተፈሪ መኮንን በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ እጅ ዘውድ ጭነው ንጉሥ ተፈሪ ተባሉ።
- ፲፱፻፳፬ ዓ/ም - የደቡብ አፍሪቃው ጳጳስ እና የኖቤል የሰላም ሽልማት ተቀባይ ዴዝሞንድ ቱቱ በዚህ ዕለት ተወለዱ።
- ፲፱፻፵፪ ዓ/ም - የቀድሞው የምሥራቅ ጀርመን ሪፑብሊክ ተመሠረተ።
- ፲፱፻፵፭ ዓ/ም - የሩሲያ የቀድሞ ፕሬዚደንት እና የአሁኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ቭላዲሚር ፑቲን በዚህ ዕለት ተወለዱ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - ናይጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሆነች።
- ፲፱፻፷፬ ዓ/ም -ኦማንየተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓባል ሆነች።
- ፲፱፻፺፱ ዓ/ም -ኤርትራዊው ዘፋኝ፣ ገጣሚ እና የሙዚቃ አቀናባሪ አብርሐም አፈወርቂ ቀይ ባህር ውስጥ ሰምጦ በተወለደ በ ፵ ዓመቱ ሞተ።
- ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው ስብከተኛ እና የሰብዓዊ መብት ታጋይ ጄሲ ጃክሰን በዚህ ዕለት ተወለደ።
- ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - አልጄሪያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሆነች።
- ፲፱፻፷ ዓ/ም - የአርጀንቲናው ተወላጅ ኤርኔስቶ ቼ ጌቫራ ከነአበሮቹ ቦሊቪያ ውስጥ ተያዘ።
- ፲፰፻፺፱ ዓ.ም. - የሴኔጋል መሪ የነበሩት ሌኦፖልድ ሴዳር ሴንግሆር ተወለዱ።
- ፲፱፻ ዓ/ም - የሐረር ገዥ የነበሩት ደጃዝማች ይልማ መኮንን (የራስ መኮንን የመጀመሪያ ልጅ እና የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ታላቅ ወንድም) አርፈው ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በአባታቸው መቃብር ተቀበሩ።
- ፲፱፻፵፭ ዓ/ም - በታላቋ ብሪታኒያ የኢትዮጵያ አራተኛው ዋና መላክተኛ (Envoy Extraordinary and Minister Plenipotentiary) የነበሩት ሐኪም አዛዥ ወርቅነህ (Dr. Charles Martin) በዚህ ዕለት አረፉ።
- ፲፱፻፷ ዓ.ም. - የአርጀንቲና ተወላጅ የነበረው፤ በአብዮት ቅስቀሳና ፍልሚያ፣ በተለይም በኩባ አብዮታዊ ትግል የሚታወቀው ኤርኔስቶ ጌቫራ በቦሊቪያ የአብዮት ፍንዳታ ሊያንቀሳቅስ ሲሞክር በተያዘ በማግስቱ ተረሽኖ ሞተ።
- ፮፻፸፫ ዓ/ም - የቀሊፋ ቀዳማዊ ያዚድ ወታደሮች በካርባላ ጦርነት ላይ የነቢዩ ሞሐመድን የልጅ ልጅ የአሊ ልጅ ሁሴንን አንገቱን በመቁረጥ ሰውት። ሺአቶች ዕለቱን በሐዘን ያስቡታል፡፡
- ፲፱፻፶ ዓ/ም - የጋናው የገንዘብ ሚኒስትር ኮምላ አግቤሊ ግብዴማ፣ በዘረኛነት ጥላቻ ምክንያት በዴላዌር ምግብ ቤት መስተንግዶ በመነፈጋቸው፣ የአሜሪካው ፕሬዚደንት ድዋይት አይዘንሃወር ይቅርታ ጠየቋቸው።
- ፲፱፻፸፫ ዓ/ም - ሁለት ትላልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ነውጦች ኤል አስናም በምትባለዋ የሰሜናዊ አልጄሪያ ከተማ ላይ የ፳ ሺህ ሰዎችን ነፍስ ጥፋትና የብዙ ሺህ ሰዎችን የአካል ጉዳት አስከተሉ።
- ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - ዩጋንዳን መጀመሪያ ወደነጻነትና በጄኔራል ኢዲ አሚን መፈንቅለ መንግሥት እስከወደቁ ጊዜ ድረስ በቀዳማዊ ጠቅላይ ሚንስትርነት፤ ከአሚን ውድቀት በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ በመፈንቅለ መንግሥት እስከተሰደዱ ድረስ ያገለገሉት አፖሎ ሚልተን ኦቦቴ ጆሃንስበርግ ላይ አረፉ::
[ለማስተካከል] ጥቅምት
ጥቅምት ፩ ቀን
- ፲፱፻፶ ዓ/ም - የአሜሪካ ፕሬዚደንት ድዋይት አይዘንሃወር በዘርያነት ምክንያት በዴላዌር ምግብ ቤት መስተንግዶ የተከለከሉትን የጋና ገንዘብ ሚኒስቴር ኮምላ አግቤሊ ግብዴማን ይቅርታ ጠየቁ።
- ፲፱፻፹፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ጉባዔ (Ethiopian Human Rights Council) በ ፴፪ መሥራች አባላት አዲስ አበባ ላይ ተመሠረተ።
ጥቅምት ፪ ቀን
- ፲፯፻፸፫ዓ/ም - በካሬቢያን ባሕር ላይ የተነሳው የአውሎ ንፋስ ማዕበል በማርቲኒክ እና በባርቤዶስ ደሴቶች ላይ ሲጎርፍ እስከ ፳፪ ሺ ሰዎች ጠፍተዋል።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት እና ፓትሪያርክ፣ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ በዚህ ዕለት አረፉ።
ጥቅምት ፫ ቀን
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የክብር ዘበኛ ሠራዊት ሸንጎ ሊቀ መንበር በደርግ ተያዙ። በዚሁ ዕለት የቀድሞው ንጉሠ ነገሥት፣ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በ፩መቶ ሚሊዮን ብር የተገመተ ንብረት ለቀድሞ ባለ-ሥሎጣኖቻቸው ሰጥተዋል ተባለ።
- ፲፱፻፹፯ ዓ/ም - የፍልስጥኤም መሪ ያሲር አራፋት፤ የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ይስሓቅ ራቢን እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ስምዖን ፔሬዝ የዓመቱን የኖቤል ሰላም ሽልማት በኅብረት ተቀበሉ።
ጥቅምት ፬ ቀን
- ፲፱፻፵፯ ዓ.ም - የብሪታንያዋ ንግሥት ዳግማዊት ኤልሳቤጥ ለሁለት ሣምንት ጉብኝት የመጡትን ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን በለንደን ቪክቶርያ የባቡር ጣቢያ ተቀበሉ።
- ፲፱፻፶፭ ዓ.ም - የአሜሪካ ዓየር ኃይል የስለላ አውሮፕላን በኩባ ላይ የሶቭየት ኅብረት የኑክሊየር መሣሪያዎች በመገጣጠም ላይ መሆናቸውን የሚያሳዩ መረጃ ፎቶግራፎች አነሳ። ይኼም የኩባ ሚሳይል ክራይስስ በመባል የተጠራውን አደገኛ መፋጠጥ ያስከተለ ሂደት ነው።
- ፲፱፻፶፯ ዓ.ም - በአሜሪካ የሰብዐዊ መብት እንቅስቃሴ መሪ የነበሩት ጥቁር አሜሪካዊ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጁኒየር የ ኖቤል ሰላማዊ ሽልማት አሸናፊነታቸው ይፋ ተደረገ።
- ፲፱፻፹፯ ዓ.ም - የፍልስጥኤም መሪ ያስር አራፋት እና የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስቴር ይስሓቅ ራቢን እንዲሁም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ (የአሁኑ ፕረዚዳንት) ስምዖን ፔሬስ የዓመቱ የ ኖቤል ሰላማዊ ሽልማት አሸናፊነታቸው ይፋ ተደረገ።
- ፲፱፻፺፪ ዓ.ም. - በምሥራቅ አፍሪቃ የታንዛኒያ መሪ የነበሩት፤ በወገኖቻቸው አቆላማጭ ጥሪ ምዋሊሙ (አስተማሪ) በመባል የሚታወቁት ጁልየስ ካምባራጌ ኔሬሬ በለንደን ሆስፒታል በሉኪሚያ በሽታ ምክንያት አረፉ። እኒህ ታላቅ አፍሪቃዊ መሪ የአፍሪቃ አንድነት ድርጅትን ከመሠረቱት አንዱ ሲሆኑ፤ በአህጉሩ የመጀመሪያው በፈቃዳቸው የፕሬዚዳንትነት ስልጣናቸውን የለቀቁ ናቸው።
ጥቅምት ፭ ቀን
- ፲፭፻፸፭ ዓ.ም. - የግሪጎሪያዊ ዘመን አቆጣጠር በዛሬው ዕለት በኢጣልያ፤ በፖላንድ ፤ በፖርቱጋል እና በእስፓንያ ከመስከረም ፳፭ ቀን በቀጥታ ወደ ጥቅምት ፭ ቀን በመዝለል ተጀመረ።
- ፲፮፻፺፱ ዓ/ም - በዓፄ ተክለ ሃይማኖት (ስመ መንግሥት ልዑል ሰገድ) ትዕዛዝ፣ ሸሽተው ጣና ሐይቅ ላይ በጨቅላ መንዞ ደሴት የነበሩትን አባታቸውን ዳግማዊ ኢያሱ አድያም ሰገድን ጳውሎስ እና ደርመን የተባሉ ነፍሰ ገዳዮች ሕይወታቸውን ካጠፉ በኋላ አስከሬናቸውን በእሳት አቃጠሉት። ከቃጠሎ የተረፈውን ካህናቱ በታንኳ ወስደው ምጽራሓ ደሴት ላይ ቀበሩት።
- ፲፯፻፩ ዓ/ም - ከ፪ዓመት በፊት በዚህ ዕለት ዳግማዊ ዓፄ ኢያሱን (ስመ መንግሥት አድያም ሰገድ) የገደሉትን ጳውሎስ እና ደርመንን ንጉሠ ነገሥቱዓፄ ቴዎፍሎስ የስቅላት ሞት ፍርድ ፈረዱባቸው።
- ፲፰፻፰ ዓ.ም. - የፈረንሳይ ንጉሥ፣ ቀዳማዊ ናፖሌዮን በወተርሉ ጦር ሜዳ ላይ ከተሸነፈ በኋላ በአሸናፊዎቹ በብሪታንያ ቁጥጥር ሥር አትላንቲክ ውቅያኖስ ወደምትገኘው የቅድስት ሔሌና ደሴት ተሰደደ።
- ፲፰፻፴፯ ዓ.ም. - ታዋቂውና ተቀዳሚው የጀርመን ፈላስፋ ፍሬድሪክ ቪልሄልም ኒቺ ተወለደ።
- ፲፱፻፫ ዓ.ም. - ታዋቂው ደራሲ ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁ በደብረ ማርቆስ አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንዳዶም ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ ተወለዱ።
- ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. - በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ በፈረንሳይ አገር የናዚ ጀርመን ደጋፊ የነበረው የቪሺ አስተዳደር ጠቅላይ ሚንስቴር የነበሩት ፒዬር ላቫል በሞት ተቀጡ። ላቫል ከእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከነበሩት ዊሊያም ሆር ጋር በታኅሣሥ ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. ኢትዮጵያን ለፋሽሽት ኢጣልያ በሚያመች መልክ ለመከፋፈል የምስጢራዊ ስምምነት የፈጸሙ ናቸው።
- ፲፱፻፴፱ ዓ.ም. - በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወንጀለኛነቱ የሞት ቅጣት የተፈረደበት ኸርማን ጎሪንግ ለቅጣቱ መፈጸሚያ ጥቂት ሰዐታት ሲቀሩ ሳያናይድ መርዝ በመውሰድ ራሱን ገደለ
- ፲፱፻፶፯ ዓ.ም. - የቀድሞዋ የሶቪዬት ሕብረት መሪ የነበሩት ኒኪታ ክሩስቼቭ ከሥልጣን ተሽረው፣ በጠቅላይ ሚኒስቴርነት በአሌክሲ ኮሲጊን፤ በኮሙኒስት ፓርቲ ሊቀመንበርነት ደግሞ በሌዮኒድ ብሬዥኔቭ ተተኩ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የቀድሞው ንጉሠ ነገሥት የልጅ ልጅ መቶ-ዓለቃ ልዑል መኮንን መኮንን ትምህርት ላይ ከነበሩበት ከአሜሪካ ወደአገራቸው በአስቸኳይ እንዲመለሱ ደርግ ትዕዛዝ አስተላለፈ።
- ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. - የቀድሞዋ የሶቪዬት ሕብረት መሪ የነበሩት ሚካይል ጎርባቾቭ የኖቤል ሰላማዊ ሽልማት አሸናፊ መሆናቸው ይፋ ተደረገ።
- ፲፱፹፮ ዓ.ም. - የደቡብ አፍሪቃ መሪዎች ኔልሰን ማንዴላና ፍሬድሪክ ዊሌም ደክለርክ የዓመቱ የኖቤል ሰላማዊ ሽልማት አሸናፊዎች መሆናቸው ይፋ ተደረገ።
- ፲፱፻፺፮ ዓ.ም. - የቻይና ሕዝባዊ ሬፑብሊክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው የያዘች የሰማይ መንኮራኩር ተኮሰች።
ጥቅምት ፮ ቀን
- ፲፰፻፸፱ ዓ/ም - የእስራኤል የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስቴር እንዲሁም የመከላከያ ሚኒስቴር በመሆን ያገለገሉት ዴቪድ ግሪን ወይም ዴቪድ ቤንጎርዮን ተወለዱ።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - የቻይና ሕዝባዊ ሬፑብሊክ የመጀመሪያዋን አቶሚክ ቦንብ አፈነዳች።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - በጋማል አብደል ናስር ሞት ምክንያት በግብጽ አንዋር ሳዳት የአገሪቱ ፫ኛ ፕሬዚዳንት ሆኑ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የዋቢ ሸበሌ ሆቴል ድርጅት በደርግ መንግሥት ተወረሰ።
- ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - በቫቲካን የተሰበሰቡ የዓለም ካቶሊካዊ ሊቀ ጳጳሳት፣ በ ፬፻ ዓመታት ለመጀመሪያ ጊዜ፣ ጣሊያናዊ ያልሆኑትን በ ፖላንድ የክራካው ካርዲናል የነበሩትን ካሮል ዮሴፍ ቮይትዋን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት (ፖፕ) በማድረግ መረጡአቸው። ዳግማዊ ዮሐንስ ጳውሎስ በተመረጡ በ ፴፫ ቀናቸው በድንገት በሞት የተለዩትን የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ ቀዳማዊ ዮሐንስ ጳውሎስን በመተካት ፪፻፷፬ናው ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሆነዋል።
- ፲፱፻፸፯ ዓ/ም - በአንግሊካን ቤተ ክርስቲያን የኬፕ ታውን ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ደቡብ አፍሪቃዊው ዴዝሞንድ ቱቱ የ ኖቤል ሰላማዊ ሽልማት ተቀባይነታቸው ይፋ ተደረገ።
- ፲፱፻፸፬ ዓ/ም - ስመ ጥሩው የእስራኤል ጄኔራል፤ እንዲሁም በአገሪቱ የመከላከያ ሚንስቴርነት እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርነት ማዕረግ የበቁት ሞሼ ዳያን በተወለዱ በ፶፮ ዓመታቸው በሞት ተለዩ።
- ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - ኦማር ሀሳን አህመድ አል-በሽር የሱዳን ፕሬዚዳንት ሆኑ።
ጥቅምት ፯ ቀን
- ፲፱፻፳፮ ዓ.ም - ታዋቂው አይሁዳዊው የጀርመን ጉስነኛ(physicist) አልበርት ኣይንስታይን በትውልድ አገሩ እየገነነ ከመጣው የናዚ ጭቆናና ሥርዐተ መንግሥት ሸሽቶ አሜሪካ አገር ገባ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ.ም - አረባዊ የነዳጅ አምራች አገሮች፣ እስራኤልን ረድታችኋል በማለት የወነጀሏቸውን ምዕራባዊ አገሮችችና በጃፓን ላይ ለአንድ ዓመት ሙሉ የነዳጅ ክልከላ ስልት አካሄዱ።
- ፲፱፻፺ ዓ.ም - የአርጀንቲና ተወላጁ ታዋቂው አብዮታዊ ተዋጊ ኤርኔስቶ ቼ ገቫራ፤ በቦሊቪያ ተግድሎ በተቀበረ በ፴ ዓመቱ አጽሙ ወደ «ሁለተኛ አገሩ» ኩባ ተመልሶ በክብር ተቀበረ።
ጥቅምት ፰ ቀን
- ፲፱፻፲፭ ዓ.ም. - ቢቢሲ (BBC (British Broadcasting Corporation)) በብሪታንያ አገር ውስጥ የራዲዮ ስርጭት አገልግሎት እንዲሰጥ ተመሠረተ።
- ፲፱፻፳፬ ዓ.ም. - የኤሌክትሪክ መብራትን እንዲሁም አምፑልን በመፍጠር የሚታወቀው አሜሪካዊው ቶማስ አልቫ ኤዲሰን በ ኒው ጀርሲ ክልል ዌስት ኦሬንጅ ላይ በተወለደ በ ፹፬ ዓመቱ አረፈ።
- ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. - የአሜሪካውን ፴፭ኛ ፕሬዚዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲን ገድለሃል በመባል የተያዘው ሊ ሃርቪ ኦዝዋልድ በዛሬው ዕለት ተወለደ። ኬኔዲ በሞቱ በሁለተኛው ቀን እሱም ተገደለ።
- ፲፱፻፸ ዓ.ም. - የምዕራብ ጀርመን ወታደራዊ ጸረ ሽብርታዊ ቡድን በሽብርተኞት ተጠልፎ ሞጋዲሹላይ ያረፈውን የሉፍትሃንሳ አውሮፕላን ካስገደዱት አራት ሽብርተኞች መኻል ሦስቱን በመግደል የተያዙትን ፹፮ ሰላማዊ ተሳፋሪዎች ነጻ አወጣ።
- ፲፱፻፹፪ ዓ.ም. - በቀድሞው የምሥራቃዊ ጀርመን ዴሞክራቲክ ሪፑብሊክ መሪ የነበሩት ኤሪክ ሆኔካ ከሥልጣን ወረዱ።
ጥቅምት ፱ ቀን
- ፲፱፻፳፰ ዓ/ም -የዓለም መንግሥታት ማኅበር በግፍ ኢትዮጵያን በወረረችው ፋሺስት ኢጣልያ ላይ የዱኛ ማዕቀብ ውሳኔ አስተላለፈ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኅብረተ-ሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት፣ የቀድሞ የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት ባለሥልጣናት የሚዳኝ ወታደራዊ የፍትሕ ሸንጎ መሠረተ።
- ፲፱፻፸፪ ዓ.ም.- ስመ ጥሩው የቡልጋ ተወላጅ አርበኛና የጥንታዊት ኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች ማኅበር ሊቀ መንበር፣ ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን በ ፷፬ ዓመታቸው መስኮብ ላይ አረፉ።
- ፲፱፻፸፱ ዓ/ም - የሞዛምቢክን ፕሬዚደንት ሳሞራ ማሼልን እና አብረዋቸው የሚጓዙ ፴፫ ሰዎችን የጫነው አየር ዠበብ በአገሪቱ ውስጥ ሌቦምቦ ተራራ ጋር ሲጋጭ ተሳፋሪዎቹ ሕይወታቸው አልፏል።
- ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - የቀድሞው የኢራቅ ፕሬዚደንት ሳዳም ሁሴን በነፍሰ ገዳይነት እና በሰፊው በሰው ልጅ ላይ ወንጀል ሠርተዋል በመባል ፍርድ ቤት ሲቀርቡ፣ ከተከሰሱባቸው ወንጀሎች ሁሉ ነፃ መሆናቸውን መሰከሩ።
- ፲፱፻፺፱ ዓ/ም - በከፍተኛ ወንጀል ተጠርጥረው በፖሊስ የሚፈለጉ ኢትዮጵያውያንን በሞያሌ በኩል ሸኝተው ለማስኮብለል የሞከሩ የውጭ ዜጋ የሆኑ ሁለት የአውሮፓ ኮሚሽን ሠራተኞች በወንጀል ከተጠረጠሩት ኢትዮጵያውያን ጋር በዛሬው እለት እጅ ከፍንጅ ተያዙ ከተባለ በኋላ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ዋና መምሪያ ይህን ህገ ወጥ ተግባር የፈፀሙት ሁለቱ የውጪ ዜጎችም ከአገር እንዲወጡ መወሰኑን ገለፀ፡፡
- ፲፯፻፴፫ ዓ/ም - “የአውስትሪያ አልጋ የውርስ ጦርነት” ዐቢይ ምክንያት የሚባለው፣ ንግሥትማሪያ ተሬዛ አባቷ ንጉሥ ቻርልስ ስድስተኛ በዛሬው ዕለት አርፎ እሷ ዙፋኑን መውረሷ ነው።
- ፲፰፻፵፯ ዓ.ም. - በ ፲፱ኛው ክፍለ ዘመን ሐረር ላይ ሰፍሮ ይኖር የነበረው፣ ፈረንሳዊው ግጥም ተቃኝ አርተር ራምቦ (Arthur Rimbaud)በዚህ ዕለት ተወለደ።
- ፲፰፻፹፬ ዓ.ም -በጎረቤት አገር በኬንያ አገራቸውን ከብሪታንያ ቅኝ ግዛትነት ነጻ ለማውጣት በመጋደል ቆይተው አገሪቱ ነጻ ስተውጣም የመጀመሪያው ፕሬዚደንት የነበሩት ጆሞ ኬንያታ ተወለዱ።
- ፲፱፻፲ ዓ/ም - የትግራይ ግዛት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ጴጥሮስ ቡልጋ ውስጥ አርፈው በእቲሳ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ተቀበሩ።
- ፲፱፻፵፭ ዓ.ም - በብሪታንያ ቅኝ ግዛት፣ ኬንያ ውስጥ ለነጻነት ይካሄድ የነበረውን የማው ማው ትግልን ለማክሸፍ በሚል ምክንያት የግዛቷ ዋና አስተዳዳሪ የነበረው ኤቨሊን ቤሪንግ “አደገኛና አስቸኳይ ሁኔታ” አውጆ የሽብሩ መሪዎች የነበሩትን እነጆሞ ኬንያታን በእሥራት ቁጥጥር አዋለ።
- ፲፭፻፲፫ ዓ.ም - የፖርቱጋል ተወላጅ ፈርዲናንድ ማጄላን በደቡብ አሜሪካ ደቡባዊ ጫፍ ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ወደ ሰላማዊ ውቅያኖስ መርከብ የሚያስተላልፍ በስሙም የሚጠራውን የማጄላን ስትሬይት (Magellan Straits) አገኘ።
- ፲፯፻፺፰ ዓ.ም. - በታዋቂው የብሪታንያ የባህር ኃይል አበጋዝ ሆሬሽዮ ኔልሰን መሪነት ከፈረንሳይና ከእስፓኛ ከተውጣጣ የባሕር ኃይል ጋር የትራፋልጋር ውጊያ (Battle of Trafalgar) እየተባለ በታሪክ በሚታወቀው ጦርነት የብሪታንያ ኃይል ድልን ተቀናጀ። ሆሬሽዮ ኔልሰንም በዚሁ ውጊያ ሞተ።
- ፲፰፻፳፮ ዓ.ም. - ዳይናማይትን የፈጠረ፤ ፖካርሲ(chemist) ፤ መሐንዲስ እና የጦር መሣሪያ ሠሪ የነበረው እንዲሁም የኖቤል ሽልማትን የመሠረተው የስዊድን ተወላጅ አልፍረድ በርንሃርድ ኖቤልበዚህ ዕለት ተወለደ።
- ፲፰፻፵፯ ዓ.ም - የመጀመሪያዋ ሐጽናሚ(Medical Nurse) በመባል ስሟ የሚታወቀው ፍሎሬንስ ናይቲንጌል ከ፴፰ ሐጽናሚያን ጋር ወደ ክራይሚያ ጦርነት ዘመቱ።
- ፲፰፻፸፩ ዓ.ም - ከጨሊዛ(carbon) የተሠራ ክር በመጠቀም ቶማስ አልቫ ኤዲሰን የመጀመሪያውን የጾፓስ(electric) መብራት ብልቃጥ ሞከረ። ይኼውም መብራት ከመቃጠሉ በፊት ለ ፲፫ ሰዐት ተኩል አበራ።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - የሮማ ኦሊምፒክ የማራቶን ድል አድራጊው አበበ ቢቂላበቶክዮ ውድድር የራሱን የኦሊምፒክ ክብረ ወሰን በመስበር በ2 ሰዓት 12 ደቂቃ 11.2 ሰከንድ አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ድልን ተቀዳጀ። ከዚህ ድል ከሰላሳ ስድስት ቀናት በፊት ትርፍ አንጀቱን በቀዶ ሕክምና አስወግዶ ስለነበረ፣ ድሉን ለሁለተኛ ጊዜ ብቻ ሳይሆን ሳያገግም በአዲስ ክብረ ወሰን ማሸነፉ በማራቶን ውድድር እስካሁን ድረስ አቻ የለሽ ጀግና አድርጎ አስመስክሮለታል።
- ፲፱፻፹፩ዓ.ም - የቀድሞው የፊሊፒንስ ፕሬዚደንት ፈርዲናንድ ማርቆስና ሚስታቸው ኢሜልዳ ማርቆስ በማጭበርበር ወንጀል ኒው ዮርክ ተከሰሱ።
- ፲፯፻፺ ዓ/ም - በፓሪስ ከተማ፣ ሦስት ሺህ ሁለት መቶ ጫማ ሽቅበት ላይ አንድሬ-ዣክ ጋርኔራን የተባለ ሰው በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በመዝለያ ጥላ (parachute) ዘለለ።
- ፲፰፻፵ ዓ/ም - ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴ የሸዋን ንጉዛት ወርሰው በዙፋኑ ተቀመጡ። ሸዋን ለሠላሳ ዐራት ዓመታት የገዙት አባታቸው ንጉሥ ሣህለ ሥላሴ ደብረ ብርሃን ላይ አረፈው በአንኮበር ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - የአሜሪካ ፕሬዚደንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በኩባ ደሴት ላይ የሶቪዬት ሕብረት የኑክሊየር መሣሪያዎች ማስቀመጧን በስለላ መረጃዎች ካረጋገጡ በኋላ፤ በደሴቷ ዙሪያ በአየርም ሆነ በባሕር ላይ የእንቅስቃሴ እገዳ ትእዛዝ አስተላለፉ።
- ፲፰፻፷ ዓ/ም - ግብጻዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ሰላማ አርፈው በመቅደላ መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ።
- ፲፱፻፬ ዓ/ም - በቱርክና በኢጣሊያ መካከል በነበረው ጦርነት የቱርኮችን የጦር ግንባር ከአየር ለመሰለል የኢጣልያ አውሮፕላን ከሊቢያ ተነሳ። ይሄም ድርጊት አውሮፕላን በጦርነት ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለበት ዕለት ነው።
- ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ፔሌ በሚል ቅጽል ስሙ የሚታወቀው የብራዚል እግር ኳስ ተጫውች ኤዲሶን አራንቴስ ዶ ናሲሜንቶ ተወለደ። ፔሌ በዓለም የኦሊምፒክ ሸምቡድ (International Olympic Committee) “የ፳ኛው ክፍለ ዘመን አትሌት” ብሎታል።
- ፲፱፻፴፰ ዓ/ም - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በዚህ ዕለት በአሜሪካ ርዕሰ ከተማ ዋሺንግቶን ዲ.ሲ. ተመሠረተ።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - የብሪታኒያ ቅኝ ግዛት የነበረችው የቀድሞዋ ‘ሰሜን ሮዴዚያ’፣ የዛምቢያ ሪፑብሊክ ተብላ ነጻነቷን ተቀዳጀች።
- ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአሜሪካ ዋና ተወካይ አድላይ ስቲቨንሰን፣ የሶቪዬት ሕብረት በኩባ ደሴት ላይ የኑክልዬር መሣሪያዎችን ማስቀመጧን የሚያሳዩ ከአየር የተነሱ ማስረጃ ምስሎችን ለጸጥታ ጉባዔው አቀረቡ።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በአፍሪቃ ከብሪታንያ ነጻነቷን በመቀዳጀት ዘጠነኛዋ አገር፣ የቀድሞዋ የሰሜን ሮዴዥያ፤ አዲሷ ዛምቢያ ኬኔዝ ካውንዳን የመጀመሪያው ፕሬዚደንት አድርጋ መረጠች።
- ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተ.መ.ድ.) ታይዋንን ከአባልነት አስወጥቶ የቻይና ሕዝባዊ ሪፑብሊክን በአባልነት እንድትገባ የሚያስችለውን ድንጋጌ በሁለት ሦስተኛ ድምጽ አጸደቀ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ስመጥሩው ኢትዮጵያዊ የማራቶን ጀግና አበበ ቢቂላ አረፈ። አበበ በ፲፱፻፶፪ ዓ.ም በሮማ የኦሊምፒክ ውድድርና በ፲፱፻፶፮ በቶክዮ የኦሊምፒክ ውድድር አሸናፊ ሲሆን በኦሊምፒክ ውድድር የወርቅ ሽልማት በማግኘት የመጀመሪያው የሰሃራ በታች አፍሪቃዊ ነው።
- ፲፱፻፸፮ ዓ/ም - በ ካሬቢያን ባሕር ላይ በምትገኘው የግሬናዳ ደሴት ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት በተካሄደበት ሣምንት ውስጥ የአሜሪካው ፕሬዚደንት ሮናልድ ሬጋን “የአሜሪካን ዜጋዎች ደኅንነት” ለመጠበቅ በሚል ምክንያት ደሴቷን በአገራቸው ሠራዊቶች አስወረሩ።
- ፲፱፻፸፯ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ውስጥ በተከሰተው ድርቅ ምክንያት በረሀብ ለተጎዱት ወገኖች እርዳታ የአውሮፓ ሕብረት 1.8 ሚሊዮን ፓውንድ (£1.8 million) ዕርዳታ ለገሠ።
- ፲፱፻፲፪ ዓ.ም - የመጨረሻው የኢራን ንጉሠ ነገሥት ሞሐመድ ሬዛ ፓህላቪ በዚህ ዕለት ተወለዱ
- ፲፱፻፵ ዓ.ም - የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚደንት ቢል ክሊንተን ሚስትና ስድሳ ሰባተኛዋ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሂላሪ ሮዳም ክሊንተን ተወለዱ።
- ፲፱፻፵፬ ዓ.ም - በብሪታንያ ብሔራዊ ምርጫ በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚንስቴር በነበሩት በዊንስተን ቸርቺል የሚመራው የኮንሰርቫቲቨ ፖለቲካ ቡድን አሸናፊ ሆኖ ቸርቺልም ለሁለተኛ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስቴር ሆኑ።
- ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. - የፓን አሜሪካ አየር መንገድ ቦይንግ 707 አውሮፕላን ለመጀመሪያ ጊዜ ከኒው ዮርክ ከተማ ተነስቶ በፈረንሳይ አገር ፓሪስ ከተማ ድረስ በረረ።
- ፲፱፻፷ ዓ.ም - ለ ሀያ ስድስት ዓመት በኢራን አልጋ ላይ ከተቀመጡ በኋላ ሞሐመድ ሬዛ ፓህላቪ በ፵፰ኛው የልደት በዓላቸው፣ በራሳቸው እጅ ዘውድ ጫኑ። የሚስታቸውን የንግሥት ፋራንም ዘውድ ጫኑላቸው።
- ፲፱፻፺፬ ዓ.ም - ብዙ ተችዎች በኢትዮጵያ በ ፳፻፩ ዓ.ም የኢ.ሕ.አ.ዴ.ግ መንግሥት ያጸደቀውን “ጸረ ሽብር” ሕግ ምሳሌ ሆኖለታል የሚባለው የአሜሪካው “ፔትርዮትስ አክት” (Patriots Act) ህግ ሆኖ ጸደቀ።
- ፲፱፻፱ ዓ.ም. - የወሎው ንጉሥ፤ የልጅ እያሱ አባት ንጉሥ ሚካኤል የልጃቸውን ከሥልጣን መውረድ አዋጅ ተቃውመው በጦር ኃይል ለማክሸፍ ከነሠራዊታቸው ወደ አዲስ አበባ ሲዘምቱ በአልጋ ወራሹ ራስ ተፈሪ መኮንን መሪነት እና በጦር ሚኒስቴሩ በፊታውራሪ ኃብተ ጊዮርጊስ አበጋዝነት የዘመተው ሠራዊት በሰገሌ ጠራ ሜዳ ወረዳ ላይ ገጥመው ከ፭ ሰዐት ውጊያ በኋላ የወሎ ሠራዊት ድል ሆነ። ንጉሡም ተማረኩ።
- ፲፱፻፶፩ ዓ.ም. - በፓኪስታን የአገሪቱ የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ኢስካንደር ሚርዛ በ ጄኔራል አዩብ ካን በሚመራ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ወረዱ።
- ፲፱፻፷፬ ዓ.ም. - የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ስሟን ቀይራ ዛይር ተብላ ተሰየመች።
- ፲፱፻፸፩ ዓ.ም - ሦስተኛው የግብጽ ፕሬዚደንት አንዋር ሳዳት እና የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስቴር ሜናኽም ቤጊን የዓመቱ የኖቤል የሠላም ሽልማት ተሸላሚዎች መሆናቸው ይፋ ሆነ።
- ፲፭፻፳፬ ዓ.ም. - የአምባሰል ጦርነት፦ በአህመድ ኢብን ኢብራሂም አል-ጋዚ ግራኝ አህመድ የሚመራው የአዳል ሠራዊትና በኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ልብነ ድንግል ሠራዊት መኻል በተደረገው ጦርነት የግራኝ አህመድ ወገን አሸነፈ። የደቡብ ኢትዮጵያ ግዛቶችም በአዳሎች ቁጥጥር ስር ዋሉ።
- ፲፱፻፲፩ ዓ.ም - በአንደኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ፤ ለ ፫፻ ዓመታት በአውስትሪያ ሁንጋሪያ ሥር የነበረችው ቼኮስሎቫኪያ ነጻነቷን ተቀዳጀች።
- ፲፱፻፶፭ ዓ.ም. - የሶቪዬት ሕብረት መሪ ኒኪታ ክሩስቼቭ አገራቸው በኩባ ደሴት ላይ በድብቅ ያስቀመጠችውን የኑክሊዬር መሣሪያ እንዲወገድ ማዘዛቸውን አስታወቁ።
- ፲፱፻፸፬ ዓ.ም - በሐረር ቢራ፤ በመብራት ኃይል፤ በኢትዮጵያ ቡና የ እግር ኳስ ቡድኖች እንዲሁም በየመን አል ሻአብ ቡድን በተከላካይነት መደብ የሚሰለፈው ኳስ ተጫዋች ሰሎሞን መልካሙ አንዳርጋቸውበዚህ ዕለት ተወለደ።
ጥቅምት ፲፱
- ፲፰፻፶፮ ዓ.ም. - ጀኔቭ ላይ የተሰበሰቡ የአሥራ ስድስት አገሮች ልዑካን የዓለም አቀፍ ቀይ መስቀል ማኅበር ለመመሥረት ተስማሙ። የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ተመሥርቶ በ፲፱፻፵፫ ዓ.ም. የዓለም አቀፋዊው ማኅበር አባል ሆነ።
- ፲፱፲፭ ዓ.ም. - የኢጣልያው ንጉሥ ቪክቶር ኢማኑኤል ሦሥተኛ ለፋሽሽት መሪው ለቤኒቶ ሙሶሊኒ የጠቅላይ ሚኒስቴርነት ሥልጣን ሰጡ።
- ፲፱፻፲፮ ዓ.ም - በአንደኛው የዓለም ጦርነት የተሸነፈውና የተሠባበረው የኦቶማን ግዛት አክትሞ በቦታው የቱርክ ሪፑብሊክ ተመሠረተ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የሱዳን መሪ ጄኔራል ሞሐመድ አቡድ በኢትዮጵያ የአንድ ሳምንት ጉብኝታቸውን ጀመሩ። በዚህ ጉብኝትም በንጉሠ ነገሥቱ ፴ኛ የዘውድ በዐል አከባበር ተሳትፈዋል።
- ፲፱፻፶፯ ዓ.ም. - በምሥራቅ አፍሪቃ ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው የታንዛኒያ ሕብረት ሪፑብሊክን መሠረቱ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) ሥልጣን ሲጨብጥ ቀርበው እንዲመረመሩ ባዘዛቸው መሠረት ባለመገኘታቸው የቀድሞው ንጉሠ ነገሥት የልጅ-ልጅ የልዑል መኮንን መኮንንን እና የትግሬውን አገረ ገዥ የልዑል-ራስ መንገሻ ሥዩምን ንብረት ወረሰ። እንዲሁም ደርግ ባስተላለፈው አዋጅ መሠረት በ”ብሔራዊ የሥራ ዘመቻ” ላይ ሳይሳተፉ የሚቀሩ ተማሪዎችን በጽኑ እንደሚቀጣ በዚሁ ዕለት አስታወቀ።
- ፲፱፻፵ ዓ.ም. - “የንግድና የዋጋ ስምምነት” (General Agreement on Tariffs and Trade (GATT)) ተመሠረተ። ይሄው ተቋም በ፲፱፻፹፰ ዓ.ም. በዓለም የንግድ ድርጅት (World Trade Organisation (WTO)) ተተካ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በኪንሻሳ ከተማ “የጫካው ጉርምርምታ” በተባለው የቦክስ ውድድር፣ ሙሐመድ አሊ በስምንተኛው ዙር ላይ ጆርጅ ፎርማንን በመዘረር አሸንፎ ‘የዓለም ቻምፒዮና’ ማዕርጉን አስመለሰ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) የቀድሞውን ንጉሥ ነገሥት ንብረት በዝርዝር የሚያዘጋጅ ኮሚቴ ሠየመ።
- ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. - ቦናንዛ በሚባለው የአሜሪካ የቴሌቪዥን ትርዒት ላይ ሊትል ጆን ካርትራይትን ሆኖ በመጫወት በዓለም ስመጥሩነትን ያተረፈው ተዋናይ ማይክል ላንደንበዚህ ዕለት ተወለደ።
- ፲፱፻፸፯ ዓ.ም. - የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኢንዲራ ጋንዲ በሁለት የሲክ የጥበቃ ወታደሮቻቸው እጅ ተገደሉ። ይሄንንም ሁኔታ ተከትሎ በኒው ዴሊ በፈነዳው የሕዝብ ሽብር ወደ ሁለት ሺህ የሚጠጉ የሲክ ተወላጆች ሕይወታቸውን አጡ።
- ፲፭፻፭ ዓ.ም. - በቫቲካን ውስጥ የሚገኘው የቅዱስ ጴጥሮስ ካቴድራል፣ በልዩ ሲስቲን ጸሎት ቤት ጣሪያ ላይ በሚካኤል አንጀሎ የተሳለው ታሪካዊ ስዕል ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕዝብ ታየ።
- ፲፱፻፳፫ ዓ/ም - በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የንግሥ በዓል ዋዜማ፤ የታላቁ ንጉሠ ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አጠገብ፤ ለበዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ(ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ ተመረቀ።
- ፲፱፻፵፭ ዓ.ም. - አሜሪካ በዓለም የመጀመሪያውን የሃይድሮጅን ቦምብ በማፈንዳት ማርሻል ደሴቶች (Marshall Islands) ላይ ፈተነች።
- ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. - በአሜሪካ የፕሬዚደንትነት ምርጫ ዘመቻቸው ላይ ለዕጩነት የቀረቡት ጆን ኤፍ ኬኔዲ፣ የሰላማዊ ተልእኮ ወይም (Peace Corps) በሚል ያቀዱትን ኃሣብ ይፋ አደረጉ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም
-
- - የጀርመን ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ (ምሥራቅ ጀርመን) አዲስ አበባ ላይ ቤተ-ልዑካን (ኤምባሲ) ከፈተ።
- - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ቤጂንግ የበረራ መሥመር ጀመረ።
- - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጎ አድራጎት ድርጅት የዓመቱ ሽሽልማት ተቀባይ፣ የሴኔጋል ፕሬዚደንት ሊዮፖልድ ሴዳር ሴንግሆር አዲስ አበባ ገቡ።
- - የቆጵሮስ ደሴት ፕሬዚደንት አቡነ መቃሪዮስ የንጉሠ ነገሥቱን ፵፫ኛ የዘውድ በዐል ያካተተ የአምስት ቀን ጉብኝት ለማድረግ አዲ አበባ ገቡ።
-
- ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. - የሠላሳ አራተኛው የአሜሪካ ፕሬዚደንት የድዋይት ዴቪድ አይዘንሃወር ባለቤት ሜሚ አይዘንሃወር በተወለዱ በ ሰማንያ ሁለት ዓመታቸው አረፉ።
- ፲፱፻፸፬ ዓ.ም. - በካሪቢያ ባሕር ላይ የሚገኙት የአንቲጉዋ እና ባርቡዳ ደሴቶች ነጻነታቸውን ከብሪታንያ ተቀዳጁ።
- ፳፻ ዓ.ም - በሁለተኛው የዓለም ጦርነት መደምደሚያ ላይ ሂሮሺማ ላይ የአቶም ቦምብ የጣለውን የአሜሪካ አየር ኃይል ዠበብ ያበረሩት ብርጋዴር ጄኔራል ፖል ቲቤትስ (Brigadier Gen. Paul Tibbets) በተወለዱ በዘጠና ሁለት ዓመታቸው አረፉ።
- ፲፱፻፯ ዓ.ም. - በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ሩሲያ በኦቶማን ንጉዛት ላይ ጦርነት አወጀች።
- ፲፱፻፱ ዓ/ም - ታዋቂው ደራሲ ክቡር ዶክቶር ከበደ ሚካኤል በደብረ ብርሃን ከተማ፣ ገርም ገብርኤል አጥቢያ ላይ ተወለዱ።
- ፲፱፻፳፫ ዓ.ም. - በኢትዮጵያ፣ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ በድንገተኛ ሞት ከአለፉ በኋላ አልጋ ወራሹ ንጉሥ ተፈሪ መኮንን ተተክተው በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የንጉሠ ነገሥትነት ዘውድ ጭነው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተባሉ።
- ፲፱፻፶፯ዓ.ም. - የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ለመጀመሪያ ጊዜ፤ በአዲስ አበባ አካባቢ ማሰራጨት ጀመረ።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - የዓመቱ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጎ አድራጎት ድርጅት ሽልማት ከ ፵ሺ የኢትዮጵያ ብር ጋር ለብሪታኒያዊው የታሪክ ምሁር፣ ባዝል ዴቪድሶን (Mr. Basil Davidson) ተሰጠ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዲሱ የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) የታወጀውን “ብሔራዊ የሥራ ዘመቻ” እንደምትደግፍ አስታወቀች።
- ፲፱፻፸፮ ዓ.ም. - የአሜሪካው ፕሬዚደንት ሮናልድ ሬጋን በየዓመቱ የማርቲን ሉተር ኪንግ መታሰቢያ ቀን እንዲከበር የሚያስችለውን ብሔራዊ ሕግ ፈረሙ።
- ፳፻ ዓ.ም. - በሰሜን ሸዋ አስተዳደር፣ በሀገረ-ማርያም ከሰም ወረዳ፣ ኮረማሽ አጥቢያ የሚገኘው የየለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በዘመናዊ መልክ ከተገነባ በኋላ ተመርቆ አገልግሎት ላይ ዋለ።
- ፲፬፻፹፮ ዓ.ም - የጄኖአው ተወላጅ ክሪስቶፎሮ ኮሎምቦ (Christopher Colombus) የአትላንቲክ ውቅያኖስን ከአውሮፓ ወደምዕራብ የማቋረጥ ሁለተኛው ጉዞው፤ ለመጀመሪያ ጊዜ የዶሚኒካ ደሴትን አገኘ።
- ፲፰፻፹፮ ዓ.ም. -ፓናማ በአሜሪካ ማበረታታት ተነስታ ከኮሎምቢያ ቅኝ ግዛትነት ነጻነቷን አወጀች። የአሜሪካው ፕሬዚደንት ቴዎድሮስ ሩዝቬልት የፓናማ ቦይን ለመቅደድ ፈልገው ኮሎምቢያ ለዚሁ ሥራ መከፈል የፈለገችውን ዋጋ ስላልተስማሙበት ፓናማ ነጻ አገር እንድትሆን ጥረታቸው ተሳካ።
- ፲፱፻፹፱ ዓ.ም - የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ አገርን በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከያዙ በኋላ ራሳቸውን በዘውድ ያነገሡት ዣን ቢዴል ቦካሳ በተወለዱ በሰባ አምስት ዓመታቸው አረፉ።
- ፲፱፻፺፯ ዓ.ም. - የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጆርጅ ወከር ቡሽ ለሁለተኛና ለመጨረሻ ጊዜ ተመረጡ።
- ፲፰፻፹፪ ዓ.ም - የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ በ እንጦጦ “መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም” ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሊቀ ጳጳሱ በአቡነ ማቴዎስ እጅ ቅብዓ መንግሥት ተቀብተው፣ ዳግማዊ ምኒልክ ተብለው የንጉሠ ነገሥት ዘውድ ጫኑ።
- ፲፱፻፵፱ ዓ.ም. - በሁንጋሪያ በጠቅላይ ሚኒስቴሩ በኢምሬ ናጊ መሪነት የተነሳውን ብሔራዊ የሕዝብ ዐመጽ ለመደምሰስ የሶቪዬት ሕብረት ወታደሮች የቡዳፔስትን ከተማ ወረሩ።
- ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. - የኢራን ሻህ ሬዛ ፓህላቪ በሕዝብ ፍንቀላ ከሥልጣን ከወረዱ በኋላ አብዮታዊ ተማሪዎች የአሜሪካን ኤምባሲ በኃይል ደምሥሠው ገብተው ዘጠና የአሜሪካ ዜጎችን በቁጥጥራቸው ስር አዋሉ።
- ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - በኢትዮጵያ እና በታላቋ ብሪታኒያ መኻል የስልክ ግንኙነት ተጀመረ። አገልግሎቱ በወቅቱ ከሰኞ እስከ ዓርብ ብቻ ከጧቱ ፭ ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ ፮ ሰዓት ከሩብ ድረስ የተወሰነ ሲሆን ከብሪታኒያ በደቂቃ አንድ ፓውንድ ስተርሊንግ ከሩብ (£1.25) ይፈጅ ነበር።
- ፲፱፻፺፫ ዓ.ም. - በደርግ ዘመን ሕይወታቸው የጠፋው የመጨረሻው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የቀብር ስርዐታቸው ተፈጸመ።
- ፲፱፻፺፱ ዓ.ም. - የቀድሞው የኢራቅ ፕሬዚደንት ሳዳም ሁሴን በአገራቸው ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተመሠረተባቸው ክስ በሰው ዘር ላይ አድርገዋል በተባሉባቸው ወንጀሎች ኃላፊነታቸው ተረጋግጦ የስቅላት ሞት ተፈረደባቸው።
- ፳፻ ዓ.ም. - የቻይና ሕዝባዊ ሬፑብሊክ የመጀመሪያዋ የጠረፍ መንኲራኩር በጨረቃ ዙሪያ መንሳፈፏን ጀመረች።
- ፲፰፻፹፮ ዓ.ም. - የክላሲክ ሙዚቃ ፈጣሪና አቀናባሪ የሩሲያው ዜጋ ፒተር ኢልዪች ቻይኮቭስኪ በፔትሮግራድ ከተማ አረፈ።
- ፲፱፻፴፯ ዓ.ም. - በአሜሪካ ፕሉቶንዬም ለመጀመሪያ ጊዜ ለቦምብ መሥሪያ ተዘጋጅቶ “ፋት ማን” በመባል የሚታወቀውን በጃፓን ናጋሳኪ ላይ የተጣለውን የአቶም ቦምብ ተሠራበት።
- ፲፱፻፵፱ ዓ.ም. - የግብጽ ፕሬዚደንት ጋማል አብደል ናሰር በወቅቱ በብሪታንያ እና በፈረንሳይ ቁጥጥር ስር የነበረውን የሱዌዝ ቦይ የግብጽ ብሔራዊ ንብረት ሲያደርገው የብሪታንያና የፈረንሳይ ሰራዊቶች በቦዩ አካባቢ ግዛቶች ከግብጽ ሰራዊት ጋር ተዋጉ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞንሮቪያ፣ ሌጎስ እና አክራ ከተማዎች አዲስ የበረራ መሥመር አስመረቀ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - “ሚቸል ኮትስ” (Mitchell Cotts) የተባለው የብሪታንያ ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ከኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጋር በአዋሽ ሸለቆ የተንዳሆን የጥጥ እርሻ ልማት የስምምነት ውል ለመፈራረም አዲስ አበባ ገቡ።
- ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - በሆላንድ እና በኢትዮጵያ ኅብረት የተቋቋመው የመተሀራ ስኳር ፋብሪካ ተመርቆ ተከፈተ።
- ፲፱፻፷፬ ዓ.ም. - አምቺትካ ደሴት ላይ የአሜሪካ የአቶሚክ ኃይል ድርጅት በምድር ውስጥ “ካኒኪን” በሚል ቅጽል ስም የተሰየመውን ኃይለኛ የሃይድሮጅን ቦምብ በማፈንዳት ፈተሸ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) እና የብሪታኒያ መንግሥት በወሎ ክፍለ-ሀገር የመጋቢ መንገዶችን ማሠሪያ ላይ የሚውል የ ፰ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር ውል ተፈራረሙ።
ጥቅምት ፳፰
- ፲፮፻፷፩ ዓ/ም - በዕለተ እሑድ ፀሐይ ደም መስላ እንደታየችና ሁለመናዋ በጉም እና ጭለማ እንደተከበበች (በግዕዙ፦”…ወተወለጠ ኵለንታሃ በኅብረ ጢስ ዘጸሊም” ይለዋል) የዘመኑ ‘ዜና-መዋዕል’ አስፍሮታል። ይህ የፀሐይ ግርደት በከፊል እስከ እንግሊዝ አገር ድረስም እንደታየ በፈረንጆቹ ተዘግቧል።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) በወቅቱ በብሪታኒያ ሕክምና ላይ የነበሩትን ፀሐፊ-ትዕዛዝ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስን እና ወንድማቸውን አቶ መኮንን ወልደ ዮሐንስን በሦስት ቀናት እጃቸውን እንዲሰጡ አዘዘ።
- ፲፱፻፹ ዓ.ም. - የቱኒዚያው ፕሬዚደንት ሀቢብ ቡርጊባ ከሥልጣናቸው ተፈንቅለው በጠቅላይ ሚኒስቴሩ በዚኔ ኤል አቢዲን ቤን አሊ ተተኩ።
- ፲፱፻፺፫ ዓ.ም. - የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚደንት ዊሊያም ጄፈርሰን ክሊንተን ባለቤት፣ ሂላሪ ሮዳም ክሊንተን ለአሜሪካ ሴኔት አባልነት በኒው ዮርክ ግዛት ተመረጡ።
- ፲፰፻፹፪ ዓ.ም. - በአሜሪካ ሰሜን ምዕራብ የሚገኘውና ስሙ ከስፓኝኛ ቋንቋ ሞንታኛ (ተራራ) የመጣው ሞንታና የተባለው ክልል የአሜሪካ ሕብረትን በመቀላቀል አርባ አንደኛው ክፍለ ግዛት ሆነ።
- ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. - በጀርመን ከተማ በሚዩኒክ የቢራ አዳራሽ ውስጥ የወደፊቱ መሪና የናዚ ቡድን ሊቀ መንበር አዶልፍ ሂትለር ውጤቱ ያልተሳካ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራውን አንቀሳቀሰ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. - በአሜሪካ የፕሬዚደንታዊ ውድድር በጊዜው ምክትል ፕሬዚደንት የነበሩትን ሪቻርድ ኒክሰንን በማሸነፍ ጆን ፊትዝጄራልድ ኬኔዲ የአገሪቱ ሠላሳ አምስተኛው ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ።
- ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የአድአን አካባቢ በዘመናዊ ግብርና ለማልማት የሚያስችል፣ በ፵ ዓመት የሚከፈል የሦስት ተሩብ ሚሊዮን ብር (E$3.25 million) ብድር ውል ከአሜሪካ መንግሥት ጋር ተፈራረመ።
- ፲፰፻፵፰ ዓ/ም - የሸዋ ንጉሥ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሴ በድንገተኛ ኅመም አርፈው በደብረ በግዕ ተቀበሩ።
- ፲፱፻፲፩ ዓ.ም. - የጀርመን ቄሳር ዳግማዊ ዊልሄልም ከዙፋናቸው እንደሚወርዱ በይፋ አሰታወቁ።
- ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. - በጀርመን እና በአውስትሪያ አገሮች ናዚዎች የይሁዳውያን መቅደሳትና መደብሮችን በዝብዘው በእሳት አጋዩ። ይሄም ታሪካዊ ምዕራፍ “Kristallnacht” የመስተዋት መስበሪያ ምሽት በመባል ይታወቃል።
- ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. - በሰሜን ምሥራቅ አሜሪካ ግዛቶችና በካናዳ ለአሥራ ሦስት ሰዐት ተኩል ያህል ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ ስምንት መቶ ሺህ ሰዎች በኒው ዮርክ ውስጠ መሬት ባቡር ላይ ተደንቅረው አመሹ። ችግሩ በግምት የሃያ አምስት ሚሊዮን ሕዝቦችን ኑሮ አዛብቷል።
- ፲፱፻፹፪ ዓ.ም. - በኮሙኒስታዊ የምሥራቅ ጀርመን ሪፑብሊክ የበርሊን ግንብ ፈረሰ። አገሪቷም ዙሪያ ድንበሮቿን በመክፈት ሕዝቦቿ ወደምዕራብ በነፃ እንዲጓዙ አመቻቸች።
- ፲፱፻፷፫ ዓ.ም. - በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የአገራቸውን አርበኞች የመሩ እና ታዋቂው የፖለቲካ ሰው፣ የፈረንሳይ ፕሬዚደንት ሻርል ደጎል በተወለዱ በ ሰባ ዘጠኝ ዓመታቸው አረፉ።
[ለማስተካከል] ኅዳር
- ፲፰፻፷፬ ዓ.ም. - ለስድስት ዓመታት አፍሪቃ ውስጥ ጠፍቶ የነበረው የስኮትላንድ ተወላጅ ዶክተር ዴቪድ ሊቪንግስተን በታንጋኒካ ሐይቅ አካባቢ ኡጂጂ በሚባል ሥፍራ ላይ፣ በ ጋዜጠኛው ሄንሪ ሞርቶን ስታንሊ ተገኘ።
- ፲፱፻፲፪ ዓ.ም. በኮንጎ የካታንጋን ግዛት ነጥሎ ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. የዚያው ክልል ፕሬዚደንትነት የተመረጠውና የወቅቱ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስቴር ፓትሪስ ሉሙምባን ያስጠለፈና ያስገደለው ሞይስ ቾምቤ ተወለደ።
- ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. - የቀድሞው ኦቶማን ግዛት ከአከተመ በኋላ፣ አዲሷን የቱርክ ሪፑብሊክን የመሠረተው ሙስታፋ ካማል አታቱርክ አረፈ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት፣ የዋቢ ሸበሌን ወንዝ ፍሰት እና ልማት ጥናት ለማካሄድ ‘ኢንግራ’ ከተባለ የዩጎዝላቪያ ተቋም ጋር የ፲ ዓመት ስምምነት ፈረመ።
- ፲፱፻፹፰ ዓ.ም. - በናይጄሪያ ታዋቂው ደራሲና የተፈጥሮ ጉዳይ ተከራካሪ ኬን ሳሮ ዊዋ፣ ሰፊ የዓለም አቀፍ ተቃውሞ ቢኖርም በአገሪቱ መንግሥት ከ ሌላ ስምንት ሰዎች ጋር በሰቀላ የሞት ቅጣት ተቀጣ።
- ፲፱፻፲፩ ዓ.ም. - ከአራት ዓመት ጦርነት በኋላ የአንደኛው የዓለም ጦርነት በአንድ በኩል ንምሳ በሌላ በኩል ተቃዋሚዎቿ አባር አገሮች በስምምነትና በፊርማ ውጊያው ከጧቱ አምስት ሰዐት ላይ እንዲያቆም ተስማሙ። ይሄ ድርጊት በየዓመቱ ከጧቱ አምስት ሰዐት ላይ በሁለት ደቂቃ ሕሊናዊ ጸሎት ይከበራል።
- ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. - በቀድሞዋ ሰሜን ሮዴዚያ፤ በዛሬይቷ ዚምባብዌ በነጩ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኢያን ስሚዝ የሚመራው መንግሥት ከህግ ውጭ አገሪቱን ከብሪታንያ ነጻነት አወጀ።
- ፲፱፻፺፯ ዓ.ም - የፍልስጥኤም ነጻነት ግንባርን እና የፍልስጥኤምን ሕዝብ ከአርባ ዓመት በላይ የመሩት ያሲር አራፋት በተወለዱ በሰባ አምሥት ዓመታቸው በፓሪስ ሆስፒታል አረፉ፡ ወዲያው ማህሙድ አባስ በእሳቸው ምትክ የድርጅቱ መሪ ሆነው ተመረጡ።
- ፲፰፻፴፬ ዓ/ም - በእስክንድርያው ፓትርያርክ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስነት የተሾሙት አቡነ ሰላማ በዚህ ዕለት ደረስጌ ሲገቡ ደጃዝማች ውቤ በደማቅ ሥርዓት ተቀበሏቸው።
- ፲፱፻፳ ዓ.ም. - በሶቪዬት ሕብረት የሥልጣን ውድድር ሊዮን ትሮትስኪ በግዞት ከአገር ውጭ እንዲወጣ ሲደረግ የጠቅላይ መሪነት ሥልጣን ወደ ጆሴፍ ስታሊን ተላለፈ።
- ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. - በአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን በነበረ ቴዎድሮስ ኸርዝል በሚባል ጋዜጠኛ ለመጀመሪያ የተጠቆመውን ማለትም ማዳጋስካርን “የአይሁዶች አገር” ይደረግ የሚለውን ሐሣብ፤ በ ጀርመን የናዚው የፕሮፓጋንዳ ሚኒስቴር ኸርማን ገሪንግ ዕቅድ አቀረበ።
- ፲፱፻፸፭ ዓ.ም. - በፖሎኝ በገዢው የኮሙኒስት ፓርቲ “ህገ ወጥ” ተብሎ የታገደው የ “ሶሊዳሪቲ” ቡድን (Solidarity Party) መሪ የነበረው፣ በኋላ የአገሪቱ ፕሬዚደንት የሆነው ሌክ ቫሌሳ ከአሥራ አንድ ወራት እሥራት በኋላ ተፈታ።
- ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. - በጃፓን፣ አልጋ ወራሹ አኪሂቶ የአገሪቱ መቶ ሃያ አምስተኛው ንጉሠ ነገሥት ሆነው ንጉሠ ነገሥት አኪሂቶ በመባል በአባቶቻቸው ዙፋን ላይ ተቀመጡ።
- ፲፱፻፺፩ ዓ.ም. - ኢትዮጵያዊው 'የቀለም ሰው' ክቡር ዶክቶር ከበደ ሚካኤል በተወለዱ በሰማንያ ሁለት ዓመታቸው አረፉ።
ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ኅዳር 4 ኅዳር ፭
- ፲፱፻፲፩ ዓ.ም.- የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት ሲያከትም፣ የቀድሞዋ ቼኮዝሎቫኪያ ሪፑብሊክ ሆነች።
- ፲፱፻፷፬ ዓ.ም. - በእስክንድርያ (ኮፕት) ቤተ ክርስቲያን አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ፓትርያርክ ሆነው በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ተቀመጡ።
- ፲፰፻፶፯ ዓ/ም - በአሜሪካ የ ዕርስ በ ዕርስ ጦርነት የሕብረት ወገን ጄኔራል ዊሊያም ተኩምሰ ሸርማን የጆርጂያን ከተማ አትላንታን አቃጠለ።
- ፲፰፻፹፪ ዓ/ም - በብራዚል ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት፣ ንጉሠ ነገሥቱን ዳግማዊ ፔድሮን ከሥልጣን አውርደው አገሪቱን ሪፑብሊክ አደርጓት።
- ፲፱፻፲፫ ዓ/ም - የዓለም መንግሥታት ማኅበር የመጀመሪያ ስብሰባውን በጄኔቭ ከተማ አካሄደ።
- ፲፱፻፸፭ ዓ/ም - በሞስኮ የቀድሞው የሶቪዬት ሕብረት ፕሬዚደንት ሊዮኒድ ብሬዥኔቭ የቀብር ስነ ስርዐት ተፈጸመ።
- ፲፱፻፸፮ ዓ/ም - በቆጵሮስ ደሴት በቱርክ ብቻ ሉዐላዊነቷ የሚታወቅላት የሰሜን ቆጵሮስ ቱርካዊ ሪፑብሊክ ተመሠረተች።
- ፲፱፻፹፩ ዓ/ም- የፍልስጥኤም ብሔራዊ ሸንጎ ሉዐላዊ ነጻ የፍልስጥኤም ግዛት አወጀ።
- ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - በቻይና ሕዝባዊ ሪፑብሊክ ሁ ጂንታኦ የኮሙኒስት ቡድን መሪ ሆኑ።
- ፲፫፻፸፯ ዓ/ም - ንግሥት ጃድዊጋ በፖሎኝ ንጉሥ ተብላ በወንድ ስም ዘውድ ጫነች። ከሞተችም በኋላ የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ሄድዊግ ብሏታል።
- ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - ከግብጽ ሠራዊቶች ጋር ጉንደት በተባለ ሥፍራ ላይ የዓፄ ዮሐንስ አራተኛ ኢትዮጵያ ሠራዊት ጦርነት ገጥመው ወገኖቻችን በግብጾች ላይ ድል ተቀዳጁ።
- ፲፱፻፴፰ዓ/ም - በየተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የትምሕርት፤ ሰገላዊ እና ባህላዊ ድርጅት (UNESCO) ተመሠረተ። የድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤት ፓሪስ ከተማ ላይ ነው።
- ፲፱፻፷፪ዓ/ም - በደጃዝማች ታከለ ወልደ ኃዋርያት መሪነት የተደራጀ የመኮንኖች ቡድን ንጉሠ ነገሥቱን ለመግደል ያደረገው ሙከራ በደኅንነትና ጸጥታ አባላት ተደርሶበት ከሸፈ። ደጃዝማች ታከለም እጃቸውን ላለመስጠት ቆርጠው እራሳቸውን ገደሉ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የቃሊቲ የምግብ ማሸጊያ ፋብሪካ በቀድሞው ንጉሠ ነገሥት ሕገ ወጥ በሆነ የተያዘ ነው በሚል የኢትዮጵያ ግዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) በመንግሥት ስም ወረሰው።
- ፲፭፻፶፩ ዓ.ም. - በእንግሊዝ ቀዳማዊት ንግሥት ማርያም ስትሞት እህቷ ቀዳማዊት ኤልሳቤጥ አልጋውን ወርሳ ዘውድ ጫነች።
- ፲፰፻፵፰ ዓ.ም. - ዴቪድ ሊቪንግስተን በዛሬዎቹ ዛምቢያና ዚምባብዌ ላይ የሚገኘውን ታላቅ ፏፏቴ በማየት የመጀመሪያው አውሮፓዊ ሆነ። ይሄንኑም ፏፏቴ ለንግሥቱ ክብር የቪክቶሪያ ፏፏቴ ብሎ ሰየመው።
- ፲፰፻፷፪ ዓ.ም. - የሜዲተራንያ ባሕርንና ቀይ ባሕርን ያገናኘው የሱዌዝ ቦይ በደመቀና በታላቅ ሥነ ስርዐት ተመረቀ።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - ፲፩ ነጥብ ፬ ‘ሜጋዋት’ የሚያመነጨው የጢስ እሳት መብራት ኃይል ማመንጫ በዚህ ዕለት ተመርቆ ሥራ ላይ ዋለ።
- ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - የሶቪዬት ኅብረት፣ አሰብ ላይ በዓመት ፭፻ ሺ ቶን የድፍድፍ ነዳጅ ማጣሪያ ለመገንባት የሚያስችለውን ውል ከኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጋር ተፈራረመ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - ሻለቃ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም (በኋላ ኮሎኔል) የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) አንደኛ ምክትል ሊቀ መንበር ስማቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ ተደረገ።
- ፲፱፻፺ ዓ.ም. - በግብጽ ስድስት አመጸኛ አክራሪዎች በሉክሶር ጥንታዊውን የ”ሀትሼፕሱት መቅደስ” ለመጎብኘት የመጡ ሠላሳ ስምንት የስዊስ፤ አሥር የጃፓን ፤ ስድስት የብሪታንያ እንዲሁም አራት የጀርመን ዜጎችን ረሽነው ገደሏቸው።
- ፲፱፻፺፮ ዓ.ም.- የአውስትሪያው ተወላጅና የፊልም ተዋናይ አርኖልድ ሽቫርትዘኔገር የካሊፎርኒያ ሠላሳ ስምንተኛው ገዥ በመሆን መሀላውን ሰጥቶ ስልጣኑን ተቀበለ።
- ፲፬፻፹፮ ዓ.ም. ክሪስቶፎሮ ኮሎምቦ የተባለው ኢጣልያዊ መርከበኛ በሰሜናዊ አሜሪካ ምሥራቃዊ ድንበር በአትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ የምትገኘውን የፑዌርቶ ሪኮ ደሴትን አገኘ።
- ፲፩፻፲፩ ዓ.ም. በባልቲክ ባሕር የምትገኘው ላትቪያ ከሩስያ ነጻ የሆነች ሉዐላዊ አገር መሆኗን አወጀች።
- ፲፱፻፲፱ ዓ.ም. በደብሊን አየርላንድ የተወለደው ታዋቂ የሥነ ጽሑፍ ሰው ጆርጅ በርናርድ ሾው የተሸለመውን ኖቤል ቢቀበልም ለዚሁ ሽልማት የተወሰነውን 118,165 የስዌድ ክሮና ግን አልቀበልም አለ። በኋላ ግን በገንዘቡ በስዌድ ቋንቋ የተጻፉ መጻሕፍት ወደ እንግሊዝኛ እንዲተረጎሙበት አደርገ። ጆርጅ በርናርድ ሾው የሽልማቱ አሸናፊነቱ ይፋ በሆነ ጊዜ፤ “አልፍሬድ ኖቤል ዲናሚት መፍጠሩን ይቅር ልለው እችላለሁ፤ ነገር ግን የኖቤል ሽልማትን ለመፍጠረ የሚበቃ ግን በሰው የተመሰለ ሰይጣናዊ መንፈስ ነው” አለ።
- ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - ልዑል ራስ ካሣ ኃይሉ በዚህ ዕለት በሞት ተለዩ።
- ፲፱፻፷፱ ዓ.ም. የእስፓኝ የሕዝብ ምክር ቤት፣ አገሪቱን ከ ሠላሳ ሰባት ዓመት የ”አምባገነን” መንግሥት ስርዐት በኋላ፣ ወደዴሞክራሲያዊ ስርዐት የሚያሸጋግር ህግ አጸደቀ።
- ፲፯፻፺፰ ዓ/ም - የሱዌዝ ቦይን የገነባው መሐንዲስ እና የፈረንሳይ ወኪል ፈርዲናንድ ደ ለሴፕስ በዚህ ዕለት ተወለደ
- ፲፰፻፴፬ ዓ/ም - በሸዋ ንጉዛት ከተማ አንጎለላ ላይ ሣህለ ሥላሴ ንጉሠ ሸዋ ከብሪታንያ መንግሥት ጋር "የወዳጅነትና የመነገድ አንድነት" ውል ተፈራረሙ።
- ፲፰፻፶፯ ዓ/ም - የአሜሪካው ፕሬዚደንት አብርሃም ሊንከን በጌቲስበርግ ፔንሲልቫኒያ የወታደሮች መቃብር በመረቁበት ጊዜ በታሪክ የ”ጌቲስበርግ ንግግር” አሰሙ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የቀድሞ ባለ-ሥልጣናትን በሙስና እና የአስተዳደር ጉድለት ወንጀል በሕግ ለመመርመር የተሠየሙትን ሁለት ልዩ ወታደራዊ ፍርድ ቤቶች ሕጋዊ የሚያደርገው አዋጅ ቁጥር ፯ በኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት (ደርግ) ይፋ ተደረገ።
- ፲፱፻፸ ዓ/ም - የግብጽ ፕሬዚደንት አንዋር ሳዳት በእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስቴር ምናኽም ቤጊን ግብዣ በአገሪቱ የሕዝብ ተወካዮች ሸንጎ “ክኔሰት” ንግግር አደርጉ። ሳዳትም ይኼን ታሪካዊ ድርጊት በመፈጸም የመጀመሪያው አረባዊ መሪ ናቸው።
- ፲፱፻፺፩ ዓ/ም- በአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (US Congress)፣ የሕግ ሸንጎ በሞኒካ ሌዊንስኪ የአመንዝራ ኃጢአት በፈጸሙት በፕሬዚደንት ዊሊያም ጀፈርሰን ክሊንተን ላይ የክሱ ዝርዝር እና ምስክሮች መሰማት ጀመረ።
ኅዳር ፲፩ ቀን
- ፲፱፻፲፰ ዓ/ም - በአሜሪካ የ፲፱፻፷፩ ዓ.ም. የፕሬዚደንትነት ምርጫ ተወዳዳሪ እና የሟቹ የፕሬዚደንት ጆን ፊትዝጄራልድ ኬኔዲ ታናሽ ወንድም ሮበርት ፍራንሲስ ኬኔዲ በዚህ ዕለት ተወለዱ።
- ፲፱፻፵ ዓ/ም - የብሪታንያ አልጋ ወራሽ ልዕልት ኤልሳቤጥ (የአሁኗ ዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ) በለንደን ዌስትሚኒስተር አቤ ሌፍተናንት (አሁን ልዑል የኤዲንበራ ዱከ) ፊሊፕ ማውንትባተን አገባች።
- ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - የልደታን አየር ዠበብ ማረፊያ የተካው አዲሱ የቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ(የቀድሞው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አውሮፕላን ማረፊያ) በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተመርቆ ተከፈተ። በዚሁ ዕለት ንጉሠ ነገሥቱ የዓመቱን የፓርላማ ጉባዔ ከፈቱ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በአስተዳደር ጥፋት እና በሙስና ወንጀል ተከሰው በልዩ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የቀረቡትን የቀድሞ ባለ-ሥልጣናት መመርመሪያ እንዲሆን የተዘጋጀው አዲስ ሕግ በነጋሪት ጋዜጣ አዋጅ ቁጥር ፰ ታውጆ ወጣ። ይህ ድንጋጌ ባ፲፱፻፵፱ ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ ላይ ተጨማሪ ነው።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - ከወላይታ-ሶዶ ተነስቶ በምዕራብ ወለጋ ዞን ወደምትገኘው በጊ መንገደኞችን የጫነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዲ-ሲ ፫ (Douglas C-47A-30-DL) ለመነሳት ሲያኮበክብ ተከስክሶ ከጥቅም ውጭ ሆኗል። በዚህ አደጋ ሦስቱ አብራሪዎቹ ሕይወታቸው አልፏል።
- ፲፱፻፹፰ ዓ/ም - የብሪታንያ አልጋ ወራሽ የልዑል ቻርልስ ሚስት ልዕልት ዳያና ስለጋብቻቸው መፍረስ እና እርሷም ከሌሎች ወንዶች ጋር ስለማመንዘሯ በቢ. ቢ. ሲ. ቴሌቪዥን ቃለ ምልልስ አደረገች።
- ፲፬፻፸ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዓፄ በእደ ማርያም፤ የዓፄ ዘርአ ያዕቆብ ልጅ በተወለዱ በ ሠላሳ ዓመታቸው፤ በነገሡ በአሥር ዓመታቸው ባልታወቀ ህመም ሞቱ። ልጃቸው ዓፄ እስክንድር ወይም ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ ተተክተው ነገሡ።
- ፲፰፻፸ ዓ/ም - አሜሪካዊው የሰገላዊ-ፈጠራ ሰው ቶማስ አልቫ ኤዲሰን ድምጽን መቅረጽና መልሶ ማሰማት የሚያስችለውን “ፎኖግራፍ” የተባለውን ፈጠራውን አሳየ።
- ፲፱፻፸፪ ዓ/ም - የኢራን ሃይማኖታዊ-መሪ አያቶላ ኾሜኒ በአሜሪካ ላይ ያላቸውን የጥላቻ መልዕክት የራዲዮ ስርጭት ተከትሎ፤ በፓኪስታን ርዕሰ ከተማ እስላማባድ አክራሪ አመጸኞች የአሜሪካን ኤምባሲ በእሳት ሲያወድሙት አምሥት ሰዎችም ሕይወታቸውን አጥተዋል።
- ፲፱፻፹፬ ዓ/ም - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታ ምክር ቤት የግብጽ ተወላጅ የሆኑትን ቡትሮስ ቡትሮስ ጋሊን ለድርጅቱ ስድስተኛ ዋና ጸሐፊነት መረጣቸው።
- ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - “የሰሜን አትላንቲክ የቃል-ኪዳን ድርጅት” (ኔቶ-NATO) ሰባት የቀድሞው የ”ምሥራቃዊ ኃይል” አባላት አገሮችን ለድርጅቱ አባልነት ጋበዛቸው። የተጋበዙት አገሮች፦ ቡልጋሪያ፣ ኤስቶኒያ፣ላትቪያ፣ ሊቱዌኒያ፣ ሩማንያ፣ ስሎቫኪያ እና ስሎቬኒያ ናቸው።
- ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በዳላስ፣ ቴክሳስ ሠላሳ አምሥተኛው የአሜሪካ ፕሬዚደንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በጠመንጃ ጥይት ተገድለው ሞቱ። በሚጓዙበት ተሽከርካሪ ውስጥ አብረዋቸው የነበሩትም የቴክሳስ ገዥ ጆን ኮናሊ በጥይት ተመተው ቆስለው ነበር። በዚህም ታሪካዊ ድርጊት የተወነጀለው ሊ ሃርቪ ኦዝዋልድ ተይዞ በቁጥጥር ሥር ሆነ። የዚያኑ ዕለት ምክትል ፕሬዚደንቱ ሊንደን ቢ ጆንሰን ሠላሳ ስድስተኛው ፕሬዚደንት ሆነው የመሀላ ሥርዐታቸውን በመፈጸም ስልጣኑን ተቀበሉ።
- ፲፱፻፷፰ ዓ/ም - በእስፓኝ አምባ ገነኑ ፕሬዚደንት ፍራንሲስኮ ፍራንኮ በሞቱ በሁለተኛው ቀን ቀዳማዊ ሁዋን ካርሎስ የአገሪቷ ንጉሥ ተባሉ።
- ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - በናይጄሪያ በወቅቱ ሊካሄድ በታቀደው ከ”ወይዘሪት ዓለም” የቁንጅና ውድድር ጋር በተያያዘ ጉርምርምታ መነሻነት “ThisDay” በተባለ የናይጄሪያ ጋዜጣ ላይ የወጣው ‘ሐይማኖት ነክ’ አንቀጽ ባስከተለው ሽብር ከሁለት መቶ በላይ ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ። ውድድሩም በዚሁ ሽብር ምክንያት ወደ ለንደን ተዛወረ።
- ፲፱፻፺፯ ዓ/ም - በዩክራይን የተካሄደውን የፕሬዚደንታዊ ምርጫ ሕዝቡ ትልቅ ጭብርብርነት ተፈጽሟል በሚል መነሻነት፣ በብዙ አሥራት ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች፣ የዕጩዋቸውን፣ የቪክቶር ዩሽቼንኮን ስም እየጠሩ የኪዬቭን ከተማ አጥለቀለቋት። ይሄውም የተቃውሞ ሰልፍ “የብርቱካን አብዮት” (Orange Revolution) ተብሎ የተሰየመውን ቅስቀሳ የተጀመረበት ዕለት ነው።
- ፲፱፻፺፰ ዓ/ም - በጀርመን ፌዴራላዊ ሪፑብሊክ፣ አንጌላ መርክል የአገሪቷ የመጀመሪያዋ ሴት ርዕሰ መንግሥት (Chancellor) በመሆን የመሀላ ስርዐት ፈጽመው ሥልጣን ተቀበሉ።
- ፲፱፻፳፯ ዓ.ም. - የወልወል ጦርነት በኢትዮጵያና በጣሊያን ተጀመረ
- ፲፱፻፷፬ ዓ.ም. - የቻይና ሕዝባዊ ሬፑብሊክ ልዑካን ለመጀመሪያ ጊዜ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ እና በድርጅቱ የጸጥታ ምክር ቤት የቻይናን መቀመጫ ቦታዎች ያዙ።
- ፲፱፻፹፱ ዓ.ም. - የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በ3 ሰዎች ተጠለፎ ነዳጅ በመጨረሱ ቆሞሮስ ደሴት አካባቢ ተከሰከሰ።
- ፲፱፻፹፱ ዓ.ም. - የአንጎላ ሪፑብሊክ የዓለም ንግድ ማኅበር አባል ሆነች።
- ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. - የአፍሪቃ አኅጉር የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዚደንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ የላይቤሪያ መሪ ሆኑ።
፲፰፻፷ ዓ.ም. የስዌድ ተወላጁ አልፍሬድ ኖቤል የዲናሚት ፈጠራውን የባለቤትነቱን መብት አስመዘገበ።
፲፱፻፶፮ ዓ.ም. በዳላስ፣ ቴክሳስ ላይ በሰው እጅ የተገደሉት ሠላሣ አምሥተኛው የአሜሪካ ፕሬዚደንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ በአርሊንግተን ብሔራዊ መቃብር በታላቅ ሥነ ስርዐት ተቀበሩ። በዚሁም የቀብር ስርዐት ለመሳተፍ ከዓለም ዙሪያ ብዙ መሪዎች መጥተው ነበር። ከነዚህም መሃል የፈረንሳይ ፕሬዚደንት ሻርል ደ ጎል፤ የአየርላንድ ፕሬዚደንት ደ ቫሌራ፤ የምዕራብ ጀርመን ቻንስለር ኤርሃርድና የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ይገኙበት ነበር።
፲፱፻፸፯ ዓ.ም. በኢትዮጵያ ውስጥ ለተከሰተው ታላቁ ድርቅና ረሐብ እርዳታ እንዲሆን በብሪታንያ ሠላሣ ስድስት የሙዚቃ ባለሙያዎች “ባንድ ኤይድ” በሚል ስም ተሰባስበው፤ “የክርስቶስ ልደት መሆኑን ያውቁታል ወይ?” (Do They Know It's Christmas) የተባለውን ዘፈን ቀረጹ።
፲፱፻፸፱ ዓ.ም. በአሜሪካ የ”ኢራን ኮንትራ አፌር” የተባለው የፖለቲካ ቅሌት ፈነዳ። ፕሬዚደንቱ ሮናልድ ሬጋን እና አቃቤ ሕጉ በስልጣን የነበሩ ሽርከኞች በምስጢር ለኢራን የጦር መሣሪያ እየሸጡ የሚገኘውን ትርፍ ደግሞ ለኒካራጓ ሽብርተኞች በምስጢር እንዳስተላለፉ ይፋ አደረጉ። ሁለት ባለሥልጣናት ወዲያው እንደተሻሩም ፕሬዚደንቱ ገለጹ።
፲፱፻፹፭ ዓ.ም. የቼኮስሎቫኪያ ፌዴራላዊ ሸንጎ አገሪቱ ከሚቀጥለው የአውሮፓውያን ዘመን መግቢያ ጀምሮ ለሁለት እንድትከፈል ደነገገ። ይሄም የአሁኖቹን የቼክ ሪፑብሊክ እና ስሎቫኪያ ሉዐላዊ አገሮችን የፈጠረው ድርጊት ነው።
፲፯፻፹፪ ዓ.ም. የአሜሪካን ሕገ መንግሥት መቋቋም በማስታወስ እግዚአብሔርን ማመስገኛ ብሔራዊ በዓል በፕሬዚደንቱ ጆርጅ ዋሽንግተን አሳሳቢነት በኮንግረስ የጸደቀ ህግ ተደነገገ።
፲፱፻፴፬ ዓ.ም. የአሜሪካ ፕሬዚደንት ፍራንክሊን ዲ ሩዝቬልት በአውሮፓውያን አቆጣጠር የኅዳር ወር አራተኛው ሐሙስ እግዚአብሔርን ማመስገኛ ብሔራዊ በዓል እንዲሆን የሚያስገድደውን ህግ ፈርሙ።
፲፱፻፶፰ ዓ.ም. ሃማጉይር በሚባል የሠሐራ በረሀ ሥፍራ ላይ፣ ፈረንሳይ ለመጀመሪያ ጊዜ የጠረፍ መንዂራኩር ተኮሰች።
፲፱፻፺፮ ዓ.ም. ኮንኮርድ የተባለው ዓየር-ዠበብ ተሽከርካሪ ለመጨረሻ ጊዜ በረረ። ፲፱፻፴፬ ዓ/ም የፋሺስት ኢጣልያን የመጨረሻውን ይዞታ ጎንደርን ለማስለቀቅ አባቶቻችን አርበኞች ከእንግሊዝ ሠራዊት ጋር በከተማዋ ዙሪያ ውጊያቸውን ጀመሩ። በዚሁ ዕለት ጄኔራል ናሲ ከነሠራዊቱ እጁን ሰጥቶ የአገራችን ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በፋሲለደስ ግንብ ላይ ተውለበለበ። በታሪክ መዝገብ የድል ቀን ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፬፻፴፫ዓ/ም ቢባልም ኢትዮጵያ ከፋሺስቶች የተላቀቀችበት ዕለት ግን ኅዳር ፲፰ ቀን ፲፱፻፴፬ ዓ/ም ነው።
፲፱፻፴፭ ዓ.ም. በከፊል በናዚ ጀርመን ቁጥጥር ስር፤ በከፊል ደግሞ በጀርመን ደጋፊው የቪሺ አስተዳደር ስር የነበረችው የፈረንሳይ የባሕር ኃይል ቱሎን ወደብ ላይ የተሰበሰቡትን መርከቦቿን፣ በናዚዎች ቁጥጥር ስር እንዳይውሉ አሰመጧቸው።
፲፱፻፶፯ ዓ.ም. የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጃዋሃርላል ኔህሩ አሜሪካ እና የሶቪዬት ሕብረት የኑክሊዬር መሣሪያዎችን መፈተሻቸውን እንዲያቆሙና እንዲያውም ያላቸውን የኑክሊዬር መሣሪያዎች እንዲያጠፉ አቤቱታቸውን አቀረቡ።
፲፱፻፷፫ ዓ.ም. የካቶሊክ ጳጳስ ጳውሎስ ስድስተኛ ለጉብኝት ፊሊፒን አገር ሲደርሱ በማኒላ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ የቄስ ልብስ የለበሰና ጩቤ የያዘ የቦሊቪያ ተወላጅ፣ ጳጳሱን በመውጋት አቆሰላቸው።
፲፱፻፹፫ ዓ.ም. በብሪታንያ የወግ አጥባቂ (Conservative party) ፓርቲ መሪዋንና የአገሪቷን ጠቅላይ ሚኒስቴር ማርጋሬት ታቸርን ከሥልጣን ካወረደ በኋላ ተተኪ እንዲሆኑ ጆን ሜጀርን የቡድኑ መሪ አድርጎ መረጣቸው። ፲፭፻፲፫ ዓ.ም. በፈርዲናንድ ማጄላን መሪነት የተቀናጁ ሦሥት የፖርቱጋል መርከቦች በደቡብ አሜሪካ ደቡባዊ ጫፍ የባሕር መስመር አልፈው ከአትላንቲክ ውቅያኖስ ወደ ሰላማዊ ውቅያኖስ በመሸጋገር የመጀመሪያዎቹ አውሮፓውያን ሆኑ።
፲፰፻፴፮ ዓ.ም. በሐዋይ ደሴቶች የነጻነት ዕለት ነው። የብሪታንያ እና የፈረንሳይ መንግሥታት የሐዋይን ደሴቶች ንጉዛት (ንጉሣዊ + ግዛት)ሉዐላዊነት አወቁ፣ አከበሩ።
- ፲፰፻፵፭ ዓ/ም - የደጅ አዝማች ካሣ (በኋላ ዓፄ ቴዎድሮስ)ሠራዊትና የጎጃሙ የደጅ አዝማች ጎሹ ተከታዮች ጉራምባ ላይ ተዋግተው ድሉ የደጅ አዝማች ካሣ ሆነ። ደጅ አዝማች ጎሹም በነፍጥ ተመተው ሞቱ።
፲፱፻፭ ዓ.ም. አልባኒያ ከኦቶማን ግዛትነት ነጻነቷን አወጀች።
፲፱፻፴፮ ዓ.ም. የአሜሪካው ፕሬዚደንት ፍራንክሊን ሩዝቬልት፣ የብሪታንያው ጠቅላይ ሚኒስቴር ዊንስተን ቸርቺል እና የሶቪዬት ሕብረት መሪ ጆሴፍ ስታሊን ኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ላይ ተገናኝተው ከናዚ ጀርመን ጋር ለሚያካሂዱት ጦርነት የሕብረት ስልት አውጥተው፣ ተስማምተው ተለያዩ።
፲፱፻፶፩ ዓ.ም. ቅኝ ግዛቶች የነበሩት ቻድ፣ የኮንጎ ሪፑብሊክ እና ጋቦን በፈረንሳይ ቤተሰብ ስር እራሳቸውን ማስተዳደር ጀመሩ።
፲፱፻፶፫ ዓ.ም. ሞሪታንያ ከፈረንሳይ ቅኝ ግዛትነት ነጻነቷን ተቀዳጀች።
፲፱፻፷፰ ዓ.ም. የፖርቱጋል ቅኝ ግዛት የነበረችው ምሥራቅ ጢሞር፣ ገዥዋ ስትተዋት የራሷን ነጻነት አወጀች። ከዘጠኝ ቀናት በኋላ ግን በኢንዶኔዚያ ሠራዊቶች ተወራ የኢንዶኔዚያ ሃያ ሰባተኛ አውራጃ ሆነች።
፲፱፻፹፫ ዓ.ም. በብሪታንያ “ኮንሰርቫቲቭ” የቀኝ ፖለቲካዊ ቡድን መሪ የነበረችው ማርጋሬት ታቸር ከመሪነቷ ካስወገዷት በኋላ የጠቅላይ ሚኒስቴርነቱን ስልጣን ለአገሪቷ ንግሥት ዳግማዊት ኤልሳቤጥ አስረከበች። ከአሥራ አምሥት ደቂቃ በኋላ ንግሥቲቱ አዲሱን የ”ኮንሰርቫቲቭ” ቡድን መሪ ጆን ሜጀርን አቅርባ፣ አዲስ አስተዳደር በጠቅላይ ሚኒስቴርነት እንዲመራ ሾመችው። ፲፯፻፸፬ ዓ.ም. በሊቨርፑል የብሪታንያ ከተማ የተመዘገበ የአፍሪቃ ሰዎችን በግዳጅ ለአገልግሎት የሚሸጥ ድርጅት ንብረት የነበረችው “ዞንግ” የምትባለው መርከብ ከጫነቻቸው ሰዎች መቶ ሠላሳ ሦሥቱን አፍሪቃውያኖች መርከበኞቹ በሕይወት እያሉ ወደ ባሕር ጥለው ገደሏቸው። በአሥራ ስምንተኛው ክፍለ ዘመን ለባርነት የሚጫኑ የአፍሪቃ ዜጎች በአውሮፓ ሕግ ፊት እንደ ዕቃ ንብረት እንጂ እንደ ሰው ስለማይቆጠሩ፣ ይሄንን ታላቅ ወንጀል የፈጸሙት ሰዎች አልተከሰሱም። የመርከቧ ባለቤቶች ግን “ለጠፋው ንብረት’’ የዋስትና ውል የሰጣቸውን ድርጅት በፍርድ ቤት የኪሳራቸውን ዋጋ እንዲከፍላቸው ክስ አቀረቡ።
፲፰፻፳፫ ዓ.ም. በፖሎኝ የሩሲያን በላይነት እና አስተዳደር በመቃወም የ”ትጥቅ ትግል” ተጀመረ።
፲፱፻፵ ዓ.ም. የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፍልስጥኤምን በሐይማኖት መሠረት ለሁለት ከፍሎ አንደኛው የይሁዳዊ መንግሥት፤ ሁለተኛውን ክፍል ደግሞ የአረብ መንግሥት እንዲመሠረት የሚያስችለውን “ውሳኔ ፻፹፩” አጸደቀ። ይሄው ውሳኔ በድምጽ ሠላሣ ሦስት አገሮች ሲደግፉት፤ አሥራ ሦሥት አገሮች ተቃውመው አሥር አገሮች ደግሞ የድጋፍም የቅራኔም ድምጽ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ኢትዮጵያ እና ብሪታንያ ከነኝህ ከአሥር አገሮች መሀል ይገኛሉ።< ፲፱፻፵፮ ዓ.ም. በኡጋንዳ የቡጋንዳ ንጉሥ ዳግማዊ ኤድዋርድ ሙቴሳ በአገሪቱ የብሪታንያ አስተዳደሪ ‘ሰር አንድሩው ኮሄን’ ተሽረው በስደት ወደለንደን ሄዱ።
፲፱፻፶፫ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጋና፤ ላይቤሪያ፤ ቶጎ፤ ብራዚል ፤ ናይጄሪያ እና ካሜሩን የሚያካሂዱትን ጉብኝት ለመፈጸም ከአዲስ አበባተነሱ። ዳሩ ግን ዕቅዳቸውን ሳያጠናቅቁ በኢትዮጵያ የታኅሣሥ ግርግር መነሳት ምክንያት ጉዟቸውን አቋርጠው ይመለሳሉ።
፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ዩ ታንትሦስተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሆነው ተመረጡ። በኮንጎ በአየር አደጋ የሞቱትን ሁለተኛውን የድርጅቱን ዋና ጸሐፊ ዳግ ሃመርሾልድን ይተካሉ።
፲፱፻፶፱ ዓ.ም. የባርባዶስ ደሴት ከብሪታንያ ነጻነቷን ተቀዳጀች።
፲፱፻፷ ዓ.ም. የየመን ሕዝባዊ ሪፑብሊክ ከብሪታንያ ነጻነቷን ተቀዳጀች።
፲፱፻፷ ዓ.ም. በፓኪስታን በኋላ የአገሪቱ መሪ የሆኑት እና በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ወርደው በስቅለት ሞት የተቀጡት ዙልፊቃር አሊ ቡቶ የፓኪስታን ሕዝባዊ ፓርቲን መሠረቱ።
፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የነዳጅ ክምችቱን ለማፈንዳት የተደረገው ሙከራ ከሽፏል
፲፱፻፺፰ ዓ.ም. በካምፓላ ኡጋንዳ የተወለዱት ጆን ታከር ሙጋቢ ሴንታሙ ዘጠና ሰባተኛው የዮርክ ሊቀ ጳጳስ ሆኑ። በዚህ ቤተ ክርስቲያን ይሄንን ታላቅ ሥልጣን የተቀበሉት የመጀመሪያው ጥቁር ጳጳስ ናቸው። ፲፱፻፵፰ ዓ.ም. በአላባማ ግዛት ውስጥ በሞንትገመሪ ከተማ፣ ልብስ ሰፊዋ ሮዛ ፓርክስ ወጥቶ እብስ ላይ መቀመጫዋን፣ (በወቅቱ ዘረኛ የከተማዋ ሕግ መሠረት)፣ ለነጭ ሰው አልለቅም በማለቷ የ”ሞንትገመሪ ወጥቶ እብስ አድማ” ተከሰተ።
፲፱፻፶፩ ዓ.ም. የፈረንሳይ ቅኝ ግዛት የነበረችው የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ በዛሬው ዕለት ነጻነቷን ተቀዳጀች።
፲፱፻፹፫ ዓ.ም. በእንግሊዝ ባህር ስር በብሪታንያ እና በፈረንሳይ አገሮች መካከል የውስጠ መሬት የባቡር መሥመር የተመሠረተበት ቡርቦራ ከባሕሩ በታች አርባ ሜትር ጥልቀት ላይ ተገናኘ።
፲፱፻፺፬ ዓ.ም. የኢትዮጵያ አየር መንገድን የመሠረተው የአሜሪካው ትራንስ ወርልድ አየር መንገድ (Trans World Airlines) ከሰባ ስድስት ዓመታት አገልግሎት በኋላ በአሜሪካ አየር መንገድ (American Airlines) ተገዛ።
- ፲፯፻፺፯ ዓ.ም. ፓሪስ በሚገኘው የእመቤታችን (Notre Dame) ካቴድራል፣ አምባገነኑ ናፖሌዮን ቦናፓርት በፈረንሳይ ከአንድ ሺህ ዓመት በኋላ እራሱን ንጉሠ ነገሥት አድርጎ በማንገሥ ዘውዱን በራሱ ላይ ጫነ።
- ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - የአሰብ ወደብ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተመርቆ ተከፈተ።
- ፲፱፻፷፬ ዓ.ም. አቡ ዳቢ፣ አጅማን፣ ሻርጃ፣ ዱባይ እና ኡም አል ቁዌይን በስምምነት የአረብ ኤሚሬት ሕብረትን መሠረቱ።
፲፰፻፲፩ ዓ.ም. በመካከለኛው አሜሪካ የምትገኘው የኢሊኖይ ግዛት በሃያ አንድኛ ደረጃ ከአሜሪካ ሕብረት ጋር ተዋሃደች።
፲፱፻፷ ዓ.ም. በደቡብ አፍሪቃ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶክቶር ክርስቲያን ባርናርድ የመጀመሪያው የሰው ልብ በ ’ቀዶ ጥገና’ ጥበብ ከሟቹ ‘ዴኒስ ዳርቫል’ ወደተቀባዩ የልብ በሽተኛ ‘ሌዊስ ዋሽካንስኪ’ አጠናቀቁ።
፲፱፻፷፱ ዓ.ም. በጃማይካ የ’ሬጌ’ ሙዚቃ ባላባት ቦብ ማርሌይ ላይ የገደላ ሙከራ ተደረገ። በሁለት ጥይቶች ቢመታም ማርሌይ ከሁለት ቀን በኋላ መድረክ ላይ ወጣ።
፲፱፻፸፬ ዓ.ም. ሕንድ አገር ውስጥ በቦፓል ከተማ ፥ የአሜሪካው ዩኒየን ካርባይድ ( Union Carbide) የኬሚካል ኩባንያ ውስጥ በተከሰተው አደጋ መርዛዊ ኬሚካል አየሩን በክሎት ሦስት ሺህ ስምንት መቶ ሰዎች ሲሞቱ እስከ ስድስት መቶ ሺህ ሰዎች በአደጋው ምክንያት ጤናቸው እንደተበላሸ ይገመታል። ፲፭፻፷ ዓ/ም - የዓፄ ልብነድንግል ሚስት እቴጌ ሰብለ ወንጌል በዚህ ዕለት አመድ በር በምትባል ሥፍራ አረፉ።
፲፮፻፲፪ ዓ.ም. ሠላሣ ስምንት ከብሪታንያ የመጡ አቅኝዎች ቨርጂኒያ ላይ አርፈው ለ እግዚአብሔር ምስጋናቸውን አቀረቡ። ይሄም ድርጊት በአሜሪካ የመጀመሪያው የምሥጋና ሰርዐት ዕለት ነበር ይባላል።
፲፯፻፹፬ ዓ.ም. በዓለም የመጀመሪያው የ’ዕሑድ ጋዜጣ’ የብሪታንያው ‘ኦብዘርቨር’ ‘The Observer’ የተባለው ጋዜጣ የመጀመሪያው ዕትም ወጣ።
፲፱፻፴፰ ዓ.ም. በአሜሪካ የሕዝብ እንደራሴዎች ‘United States Senate’ አባላት በስድሳ አምሥት ለ ሰባት ድምጽ አሜሪካ ጥቅምት ፲፬ ቀን ፲፱፻፴፰ ዓ.ም. የተመሠረተው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዓባል እንድትሆን አጸደቁ።
፲፱፻፶፩ ዓ.ም. የቀድሞዋ ዳሆሚ የዛሬዪቷ ቤኒን ከ ፈረንሳይ ቁጥጥር ውጭ ዕራሷን በራሷ የመግዛት ስርዐት ጀመረች።
፲፱፻፶፬ ዓ.ም. የብሪታንያ መንግሥት ለሴቶች ዜጋዎቹ የ’ጽንሰት መከላከያ’ መድሐኒት በብሔራዊ የጤና ጥበቃ አገልግሎት በነጻ መቀበል እንዲችሉ አደርገ።
፲፱፻፸ ዓ.ም. የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ ፕሬዚደንት ጃን ቤደል ቦካሳ ዕራሳቸውን በራሳቸው ቀዳማዊ ቦካሳ በሚል ስም በማንገሥ የአገሪቱም ስም ተቀይሮ ‘የመካከለኛው አፍሪካ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት’ በሚል ስም ተሰየመች።
፲፱፻፹፬ ዓ.ም. የፓን አሜሪካ አየር መንገድ ከ ስድሳ አራት ዓመታት አገልግሎት በኋላ አከተመ።
፲፱፻፹፭ ዓ.ም. በሶማሊያ አገር ውስጥ በተከሰተው የ’ዕርስ በርስ ጦርነት’ የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጆርጅ ኸርበርት ዎከር ቡሽ የ’ሰብዓዊ ርሕራሔ’ ምክንያት በሚል መነሻ ሃያ ስምንት ሺህ የአሜሪካ ወታደሮችን ወደ ሶማሊያ ላኩ።
- ፲፬፻፹፭ ዓ.ም. ክሪስቶፎሮ ኮሎምቦ የሂስፓኒዮላን ደሴት (የአሁኗ ሀይቲ ደሴት]]ን እና የዶሚኒካን ሪፑብሊክን በመርገጥ የመጀመሪያው አውሮፓዊ ሆነ።
- ፲፱፻ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት እና የታላቋ ብሪታኒያ መንግሥታት፤ ከዶሎ እስከ ሱዳንግዛት ድረስ ያለውን የኢትዮጵያን ድንበር ለማስመር ስምምነት ፈረሙ።
- ፲፰፻፳፬ ዓ.ም. የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚደንት ጆን ክዊንሲ አዳምስ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (House of Representatives) በዓባልነት ተመርጠው መቀመጫቸውን ያዙ።
- ፳፻፩ ዓ.ም. በሩሲያ ውስጥ የአሜሪካ እና የሩሲያ ባለ ሙያዎች በ፲፱፻፹፬ ዓ.ም. ተቆፍሮ የተገኘውን የሰው አጽም የአገሪቱ የመጨረሻ ንጉሥ ዳግማዊ ዛር ኒኮላስ አጽም መሆኑን አረጋገጡ።
፲፯፻፹፫ ዓ.ም. የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከኒው ዮርክ ከተማ ወደ ፊላዴልፊያ ከተማ ተዛወረ።
፲፰፻፺ ዓ.ም. በዓለም የታክሲዎችን አገልግሎት በ ሕጋዊ ረገድ በማስተናገድ ሎንዶን ከተማ የመጀመሪያዋ ሆነች።
፲፱፻፶ ዓ.ም. አሜሪካ ወደጠረፍ መንኲራኩር ለመተኮስ የመጀመሪያ ሙከራዋ በኬፕ ካናቨራል ከሸፈ።
፲፱፻፺፩ ዓ.ም. በቬኔዙዌላ አገር ወታደራዊው መኮንን ሁጎ ሻቬዝ ፍሪያስ በፕሬዚደንትነት ተመረጠ። ፲፱፻፴፬ ዓ.ም. የጃፓን ንጉሠ ነገሥት የባሕር ኃይል የአሜሪካንን የሰላማዊ ውቅያኖስ የባሕር ኃይል እና አብሮ የተሰለፈውን የጦር ኃይል በ ሃዋይ ደሴቶች ላይ ባለችው ፐርል ሃርበር ‘Pearl Harbour’ በተሰኘችው ወደብ ላይ እንዳሉ ከፍተኛ አደጋ ጥላባቸው አሜሪካን የሁለተኛው ዓለም ጦርነት ውስጥ እንድትገባ የገፋፋትን ታሪካዊ ሁኔታ ከሰተች።
፲፱፻፸፪ ዓ.ም. በሮዴዥያ የሽግግር መንግሥትን እንዲያስተዳድሩ የተመረጡት የዊንስተን ቸርችል አማች የነበሩት እንግሊዛዊው ‘ሎርድ ሶምስ’ (Lord Soames) እጩነታቸው ይፋ ተደረገ።
፲፱፻፹፮ ዓ.ም. አገራቸውን አይቮሪ ኮስትን ከፈረንሳይ ነጻነቷን ከተቀዳጀችበት ፲፱፻፶፫ ዓ.ም. እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ በፕሬዚደንትነት የመሩት ፊሊክስ ሁፌ ቧኜ በተወለዱ በ ሰማንያ ስምንት ዓመታቸው አረፉ።
፲፱፻፹፰ ዓ.ም. የአሜሪካ የጠረፍ መንኲራኩር ‘ጋሊሌዎ’ ከምድር በተተኮሰች በስድስት ዓመቷ ጁፒተር ዘንድ ደረሰች። ፲፱፻፲፰ ዓ/ም ጥቁር አሜሪካዊው ዘፋኝ፤ ዳንሰኛ እና የፊልም ተዋናይ ሳሚ ዴቪስ ጁንየርበዚህ ዕለት ተወለደ።
፲፱፻፴፬ ዓ/ም የጃፓን ዓየር ኃይል በሃዋይ የፐርል ሀርበርን ወደብ ባጠቃ በማግሥቱ የአሜሪካ የሕዝብ ምክር ቤት አባላት በጃፓን ላይ የጦርነት አዋጅ አወጁ።
፲፱፻፸፩ ዓ/ም በአሁኑ ጊዜ በየመን ለአል ሳቅር ቡድን የሚጫወተው ኢትዮጵያዊው የእግር ኳስ ተጫዋች አንዋር ሲራጅየልደቱ ቀን ነው።
፲፱፻፸፫ ዓ/ም በኒው ዮርክ ከተማ የቀድሞው የቢትልስ መሥራችና ዓባል ጆን ሌነን መኖሪያ ቤቱ ፊት ለፊት ላይ ‘ማርክ ዴቪድ ቻፕማን’ በተባለ ሰው በሽጉጥ ተገደለ። ፲፰፻፵፰ ዓ/ም የሸዋው ንጉሥ እና የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ አባት ንጉሥ ኃይለ መለኮት በኃይል ሊያስገብሯቸው ከመጡት ከዓፄ ቴዎድሮስ ጋር ለጦርነት ሲዘጋጁ በድንገት ታመው አረፉ።
፲፰፻፸፭ ዓ/ም በሉዊዚያና ግዛት ‘ ፒ. ቢ. ኤስ. ፒንችባክ’ የመጀመሪያው ጥቁር አሜሪካዊ ገዥ ሆነ ።
፲፰፻፺፰ ዓ/ም በፈረንሳይ መንግሥትን እና ቤተ ክርስቲያንን የሚለየው ህግ ጸደቀ።
፲፱፻፶፬ ዓ/ም የቀድሞዋ ታንጋኒካ ከብሪታንያ ነጻነቷን ተቀዳጀች። ከነጻነት በኋላ በ፲፱፻፶፯ ዓ/ም ታንጋኒካ ከዛንዚባር ጋር ተዋሕዳ የዛሬይቱን የታንዛኒያ ሪፑብሊክ መሠረቱ።
፲፱፻፹፫ ዓ/ም በፖሎኝ አገር ሌክ ቫሌሳ የመጀመሪያው በሕዝብ የተመረጠ ፕሬዚደንት ሆነ ።
፳፻፩ ዓ/ም በአሜሪካ የኢሊኖይ ገዥ ሮድ ብላጎዬቪች በብዙ ወንጀሎች ተከሶ በፌዴራል ህግ አስከባሪዎች ተያዘ። ፈጽሟል ከተባሉት ወንጀሎች አንዱ በፕሬዚደንትነት የተመረጡትን የባራክ ኦባማን የእንደራሴዎች ምክር ቤት (United States Senate) አባልነት በገንዘብ ሊሸጥ ሞክሯል በመባል ነው ።
[ለማስተካከል] ታኅሣሥ
ታኅሣሥ ፩ ቀን
- ፲፰፻፷፩ ዓ/ም - በዓለም የመጀመሪያው የመንገድ ተሽከርካሪዎች መቆጣጠሪያ መብራት በእንግሊዝ ዋና ከተማ በለንደን ላይ የፓርላማ ሕንጻ (የዌስትሚንስተር ቤተ መንግሥት) ‘Palace of Westminster’ ፊት ለፊት ተተክሎ አገልግሎት ላይ ዋለ።
- ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በብሪታንያ በንጉሡ የፍቅረኛቸውን ምርጫ ምክንያት በተከሰተው ቀውስ፥ ንጉሥ ኤድዋርድ ስምንተኛ ሥልጣናቸውንና ዘውዳቸውን መልቀቅ የሚያስችላቸውን ህግና ስምምነት ፈረሙ።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎ ላይ በተካሄደ ሥነ ሥርዐት ላይ ጥቁር አሜሪካዊው የሰብአዊ መብት ዋና ተሟጋችና ሰማዕት ማርቲን ሉተር ኪንግ የኖቤል ሰላማዊ ሽልማት ተቀበሉ።
- ፲፱፻፸፬ ዓ/ም - የብሪታንያው ቢ.ቢ.ሲ. በአሜሪካ አሥራ አምሥት ግዛቶች ውስጥ ‘ሰዶማውያን’ን የሚያጠቃ ያልታወቀ አዲስ በሽታ እንደገባ እና በእነኚሁ ግዛቶች ውስጥ ሰባ አምሥት ሰዎች፥ በእንግሊዝ አገር ደግሞ አንድ ሰው በዚሁ በሽታ መሞታቸውን ዘገበ። ይሄ በሽታ በኋላ ኤይድስ የተባለው በሽታ ሲሆን ሠላሣ ዓመታት እንኳን ባልሞላ ጊዜ ውስት በዓለም ላይ ወደ ሃያ አራት ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ሕይወት ወስዷል።
- ፲፱፻፸፯ ዓ/ም - የደቡብ አፍሪቃዊው ጳጳስ ዴዝሞንድ ቱቱ የኖቤል ሰላማዊ ሽልማት ተቀበሉ።
- ፲፱፻፹፩ ዓ/ም -በቀድሞው የሶቪዬት ሕብረት ግዛት ውስጥ በአርሜኒያ ክልል ውስጥ በተከሰተው የምድር እንቅጥቅጥ አርባ አምሥት ሺህ ሰዎች ሲሞቱ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች ደግሞ መኖሪያ ቤታቸውን አጥተዋል። ስፒታክ የምትባል የሃያ አምሥት ሺህ ነዋሪዎች ከተማ በዚሁ እንቅጥቅጥ ፈጽማ ወድማለች።
- ፲፱፻፹፯ ዓ/ም -የፍልስጥኤም መሪ ያሲር አራፋት እና የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስቴር ይስሐቅ ራቢን እንዲሁም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ሥምዖን ፔሬዝ በጋራ የተሰጡትን የኖቤል ሰላማዊ ሽልማት ተቀበሉ።
ታኅሣሥ ፪ ቀን
- ፲፱፻፲፩ ዓ/ም - የሩሲያው ተወላጅና የሥነ ጽሑፍ ሰው አሌክሳንደር ሶልዤኒትሲን በዛሬው ዕለት በኪስሎቮድስክ ተወለደ። ሶልዤኒትሲን በስታሊን ዘመን አድሀሪ በመባል ተወንጅሎ በሳይቤሪያ ግዛት ውስጥ በእሥራትና በግዞት በነበረበት ወቅት የጻፈው “የጉላግ አርቺፒላጎ” በተባለው ድርሰቱ በዓለም ታዋቂነትን ያተረፈ ጸሐፊ ነበር።
- ፲፱፻፴ ዓ/ም - የፋሺስት ኢጣልያ መንግሥት ኢትዮጵያ አገራችንን በግፍ ከወረረች በኋላ የተሰነዘረባትን ነቀፋ እና የንግድ እገዳ ምክንያት በማድረግ ከየዓለም መንግሥታት ማኅበር አባልነት ወጣች።
- ፲፱፻፴፱ ዓ/ም -የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የዓለም አቀፍ ሕጻናት ዕርዳታ ድርጅት (UNICEF] ተመሠረተ።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - ታዋቂው የአብዮት መሪ ቼ ጉቬራ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጉባዔ ላይ ንግግር ሲያደርግ ያልታወቀ ሽብርተኛ ከውጭ በሕንጻው ላይ የሞርታር ጥይት ተኮሰ።
- ፲፱፻፸፬ ዓ/ም -የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት የፔሩውን ተወላጅ ሃቪዬር ፔሬዝ ደ ኩዌያርን የድርጅቱ አምስተኛ ዋና ጸሐፊ እንዲሆኑ መረጣቸው።
ታኅሣሥ ፫ ቀን
ይቺ ዕለት በኢትዮጵያ ታሪክ ሁነኛ ስፍራ አላት። ታላቁ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክና የጦሩ ፊታውራሪ፣ ፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ ያረፉበት ዕለት ናት፡፡ ዕለቱ ተመሳሳይ ይሁን እንጂ ሁለቱ ያረፉት በተለያዩ ዓመታት ነው፡፡ ‹‹አባ ዳኘው›› የተባሉት፣ ዳግማዊ ምኒልክ ፳ኛው ምዕት ዓመት በባተ በስድስተኛው ዓመት ላይ በ፲፱፻፮ ዓ.ም. ሲያርፉ ‹‹አባ መላ›› የተሰኙት ፊታወራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ደግሞ በ፲፱፻፲፱ ዓ.ም. አርፈዋል። ዓመታቱ ይለያዩ እንጂ ሁለቱም ያረፉት ዓርብ ታኅሣሥ ፫ ቀን ነበር፡፡
- ፲፰፻፲ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የዘመነ መሣፍንት ሲጀመር ከዙፋናቸው ወርደው አክሱም በስደት ላይ የነበሩት እና “ተፍጻሜተ ነገሥት” የሚባል ቅጽል ስም የተሰጣቸው ቀዳማዊ ዓፄ ተክለ ጊዮርጊስ አረፉ።
- ፲፱፻፬ ዓ/ም - የቀድሞዋ የሕንድ ርዕሰ ከተማ ካልከታ በአዲሷ ደልሂ ተተካች። በዚሁ ዕለት የብሪታንያ ንጉሥ ጆርጅ አምሥተኛ (የዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ አያት) እና ንግሥታቸው የ ሕንድ ንጉሠ ነገሥት እና እቴጌ የሚል ማእረግ ተጨመረላቸው።
- ፲፱፻፮ ዓ/ም - መጀመሪያ የሸዋ ንጉሥ በኋላም የዘመናዪቱ ኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት፤ በአድዋ ጦርነት የኢጣሊያን ሠራዊቶች ድል የመቱት ታላቁ መሪ፤ “ዕምዬ ምኒልክ” ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ባደረባቸው ህመም በዛሬው ዕለት አረፉ።
- ፲፱፻፲፱ ዓ/ም - በዳግማዊ ምኒልክ፣ በልጅ ኢያሱ እና በንግሥት ዘውዲቱ ዘመናት የጦር ምኒስትር የነበሩት ፊታውራሪ ሁብተ ጊዮርጊስ ዲነግዴ የሚወዷቸው ዕምዬ ምኒልክ ባረፉበት ዕለት ሞቱ።
ታኅሣሥ ፬ ቀን
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - በወንድማማቾች መንግሥቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ የተሰነጸጸው የታኅሣሥ ግርግር መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ተጀመረ።
- ፲፱፻፹፫ ዓ/ም - በደቡብ አፍሪቃ ፕሬዚደንት ደ ክለርክ በእሥራት ላይ ከነበሩት ከኔልሰን ማንዴላ ጋር እቢሯቸው ተገናኝተው የተጠላውን የጭቆና ሥርዐት (አፓርታይድ)ን የሚወድምበትን ሁኔታ ተመካከሩ።
- ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታ ምክር ቤት አባላት የጋናውን ተወላጅ ኮፊ አናንድን ሰባተኛው የድርጅቱ ዋና ጸሐፊነት መረጧቸው።
- ፲፱፻፺፮ ዓ/ም - የቀድሞው የኢራክ ፕሬዚደንት ሳዳም ሁሴን ከሥልጣናቸው ሸሽተው ከተደበቁ በኋላ በአሜሪካ ሠራዊቶች በተወለዱበት ቲክሪት ከተማ አካባቢ ጉድጓድ ውስጥ ተደብቀው ተገኙ።
ታኅሣሥ ፭ ቀን
- ፲፱፻፴፱ ዓ/ም -የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጽሕፈት ቤቱ በኒው ዮርክ ከተማ እንዲሆን ወሰነ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - በወንድማማቾች መንግሥቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ የተሰነጸጸው የታኅሣሥ ግርግር መፈንቅለ መንግሥት ዓላማውን ይፋ አደረገ። አብሮም የለውጥ ፈላጊ ናቸው የሚባሉትን ልዑል ራስ እምሩ ኃይለ ሥላሴን በጠቅላይ ሚኒስትርነት መሾማቸውንና አልጋ ወራሹን አስፋ ወሰንን (“አስገድደው”) በማስማማትም መንግሥት በቆረጠላቸው ደመወዝ እየተዳደሩ ለሕገ መንግሥት የሚገዙ ንጉሥ ሆነው እንደሚያገለግሉ እራሳቸው ለሕዝቡ በራዲዮ እንዲያስተላልፉ አደረጉ።
- ፲፱፻፶፬ ዓ/ም -ታንዛንያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሆነች።
- ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - ዲክ ታይገር (ሪቻርድ ኢሄቱ) የሚባለው ናይጄሪያዊ ቦክሰኛ በተወለደ በ ፵፪ ዓመቱ በጉበት ነቀርሳ ምክንያት አረፈ። ዲክ ታይገር የባያፍራን የመገንጠል ሙከራ ደጋፊ ነው በሚል ወደአገሩ እንዳይመለስ ተከልክሎ በስደት አሜሪካ ይኖር ነበር።
- ፲፱፻፺፱ ዓ/ም - የደቡብ ኮርያው ተወላጅ፣ ባን ኪ ሙን ስምንተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሆኑ።
ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 6 ታኅሣሥ ፯ ቀን
- ፲፰፻፪ ዓ/ም የፈረንሲስ ንጉሠ ነገሥት ናፖሌዎን ቦናፓርት ከሚስቱ ከንግሥት ጆሴፊን ጋር ተፋታ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም በወንድማማቾች መንግሥቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ የተሰነጸጸው የታኅሣሥ ግርግር መፈንቅለ መንግሥት ኃይል እየተዳከመ በአንጻሩ ደግሞ ተቃዋሚዎቻቸው እያደር እየጎለመሱ መሄዳቸውን የተገነዘቡት ሽብርተኞች በቁጥጥራቸው ላይ የነበሩትን ሃያ መሳፍንት፣ መኳንንት፣ ሚኒስትሮችንና መኮንኖችን ወደ አረንጓዴ ሳሎን ያዛውሩና አልጋወራሹንና አዲሱን ጠቅላይ ሚኒስትር ለብቻቸው እንዲጠበቁ ያደርጋሉ። ጄነራል ጽጌ ዲቡ ወዲያው ከተቃራኒ ወገን በተተኮሰ ጥይት ሲገደሉ፣ እነ ጄነራል መንግሥቱ የያዟቸውን እስረኞት ረሽነው ለማምለጥ ወስነው ሜጄር ጄኔራል ሙሉጌታ ቡሊ፤ ራስስዩም መንገሻ፤ ራስ አበበ አረጋይ፤ አቶ መኮንን ሀብተወልድ፤ አባ ሐና ጅማ፤ በጠቅላላው አሥራ አምስት ሰዎች ተረሽነው ሞቱ። የክብር ዘበኛ መኮንን የነበሩት ሻምበል ደረጀ ኃይለ ማርያም ሽብርተኞቹን በመቃወም የቤተ መንግሥቱን አጥር በታንክ ደምስሰው ሲገቡ ከሽብርተኞት ወገን በተተኮሰ ጥይት ተገደሉ። ሻምበል ደረጀ የስመ ጥሩው አርበኛ የኃይለ ማርያም ማሞ ልጅ እና የንጉሠ ነገሥቱ የልጅ ልጅ የልዕልት ሶፊያ ደስታ ባል ነበሩ።
- ፳፻፫ ዓ/ም የኢትዮጵያና የቅዱስ ጊዮርጊስ ቡድኖች እግር ኳስ ተጫዋችና አሰልጣኝ የነበረው በኩሩና ኮከቡ መንግሥቱ ወርቁ፣ በ፸ ዓመቱ አረፈ። መንግሥቱ ወርቁ በስድስት የአፍሪካ ዋንጫዎች የፍጻሜ ግጥሚያዎች የተሳተፈ ሲሆን፣ በ፫ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ ግብፅን ፬ ለ ፪ አሸንፋ ዋንጫ እንድታገኝ ሁለቱን ግቦች ያስቆጠረና በዚሁ በ፫ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ፫ ግብ በማስቆጠሩም የኮከብ ግብ አግቢነት ክብር አግኝቷል፡፡
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም በወንድማማቾች መንግሥቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ የተሰነጸጸው የታኅሣሥ ግርግር መፈንቅለ መንግሥት ኃይል ተደምስሶ ንጉሠ ነገሥቱ ከብራዚል ተመልሰው በአስመራ በኩል አዲስ አበባ ገቡ።
- ፲፱፻፹፰ ጋናዊው ኮፊ አናንድ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ሆኑ።
ታኅሣሥ ፱ ቀን
- ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - ንጉሠ ነገሥቱ ገነተ ልዑል ይባል የነበረውን ቤተ መንግሥት የከፍተኛ ትምህርት ማእከል እኒዲሆን ሰጥተው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መርቀው ከፈቱ።
- ፲፱፻፸፮ ዓ/ም - አንድ ነጥብ ስምንት ኪሎ-ግራም የሚመዝነው የመጀመሪያው የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር የዡልስ ሪሜ የወርቅ ዋንጫ ከብራዚል የእግር ኳስ ጥምረት ዋና መሥሪያ ቤት
ተሰረቀ። ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 10 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 11 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 12 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 13 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 14 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 15 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 16 ታኅሣሥ ፲፯
- ፲፱፻፹ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ባዘጋጀችው የምሥራቅና መካከለኛው አፍሪቃ የእግር ኳስ ዋንጫ (ሴካፋ) ዚምባብዌን በፍጹም ቅጣት ምት በማሸነፍ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫውን ከፍ ያደረገችበት ነበር፡፡ ዋንጫውን ለብሔራዊ ቡድኑ አምበል ገብረ መድኅን ኃይሌ የሰጡት የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ (ኢሕዲሪ) ፕሬዚዳንት፣ መንግሥቱ ኃይለ ማርያም ሲሆኑ፣ የተሰማቸውን ደስታ የገለጹት ፻ ሺሕ ተመልካች የሚይዝ ስታዲየም ለመሥራት ቃል በመግባት ነበር፡፡
- ፲፱፻፺፯ ዓ/ም - በሕንድ ውቅያኖስ ሥር የተነሳው የመሬት እንቅጥቅጥ ያስከተለው ኃይለኛ የባሕር ሞገድ በስሪ ላንካ፣ ሕንድ፣ ኢንዶኔዚያ፣ ታይላንድ እና ማሌዚያ አገራት ከ፪መቶ ፴ሺ በላይ የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት አጥፍቷል።
- ፳፻ ዓ/ም - በኬንያ የፕሬዚደንታዊ ምርጫ ምዋይ ኪባኪ አሸናፊ ናቸው ተብሎ ሲታወጅ በመላ አገሪቱ የተከተለው የተቃውሞ ረብሻ በአገሪቱ ለተከሰቱት ፖለቲካዊ፤ ምጣኔ-ኃብት እና ሰብዓዊ ነውጦች ዋና መንስዔ ሆኗል።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ደርግ በኢትዮጵያ ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ስርጭት የወሰነውን ማሻሻያ ይፋ አደረገ። በዚህ መሠረት በራዲዮ የኦሮምኛ ሥርጭት ለመጀመሪያ ጊዜ ሲወጠን በአንጻሩ የፈረንሳይኛ ሥርጭትን ሰረዘ። የእንግሊዝኛ ፕሮግራሞቹን ደግሞ በራዲዮም በቴለቪዥንም ቅነሳ እንደሚደረግ አስታወቀ።
- ፲፱፻፩ ዓ/ም - በሲሲሊ ደሴት፣ መሲና ከተማ አካባቢ የተነሣው የመሬት እንቅጥቅጥ ከ፸፭ሺህ በላይ የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት አጠፋ።
- ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች ማኅበር ሊቀ መንበር፣ ጥላሁን ግዛው በፖሊስ ተገደለ። ይህ ድርጊት በርዶ የነበረውን የተማሪዎች አመጽ እንደገና አፋፍሞታል።
- ፳፻፩ ዓ/ም - በሶማሊያ የሥልጣን ትግል ውጊያ የአገሪቱ ጊዜያዊ ፌዴራላዊ መንግሥት ሠራዊት እና አጋሮቻቸው የኢትዮጵያ ወራሪ ኃይል የሞቃዲሹን ከተማ በቁጥጥራቸው ሥር አዋሉ።
ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 20 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 21 ታኅሣሥ ፳፪
- ፲፱፻፵፰ ዓ/ም - የሱዳን ሪፑብሊክ ነጻነቷን ከምስር ሪፑብሊክ እና ከታላቋ ብሪታኒያ እና የአየርላንድ ሕብረታዊ ንጉዛት ተቀዳጀች።
- ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - የካሜሩን ሪፑብሊክ ነጻነቷን ከ ፈረንሳይ እና ከታላቋ ብሪታኒያ እና የአየርላንድ ሕብረታዊ ንጉዛት ተቀዳጀች።
- ፲፱፻፹፭ ዓ/ም - የቀድሞዋ ቼኮዝሎቫኪያ በሰላማዊ ስምምነት ለሁለት ተከፍላ የቼክ ሪፑብሊክ እና ስሎቫኪያ በተባሉ ሉዐላዊ አገራት ተተካች። መገናኛ ብዙሀን ይሄንን ከፈላ ‘የሐር ፍች’ (Velvet Divorce) የሚል ሥያሜ ሰጥተውታል።
- ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ ተመሰረተ።
- ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - ጋናዊው ዲፕሎማት ኮፊ አናን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ፯ተኛው ዋና ጸሐፊ ሆነው ተሾሙ።
ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 24 ታኅሣሥ ፳፭ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፲፭ተኛው እና የመፀው ወቅት መጨረሻውና ፺ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፪፻፶፩ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፶ ቀናት ይቀራሉ። ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ታኅሣሥ 26 ታኅሣሥ ፳፯ ቀን
- ፲፱፻፸፯ ዓ/ም - የ፳ኤል መንግሥት ‘ኦፐሬሽን ሙሴ’ በሚል ሥያሜ ኢትዮጵያውያን ፈላሻዎችን ከኅዳር ፲፪ ቀን ፲፱፻፸፯ ዓ/ም ጀምሮ በድብቅ ወደ ፳ኤል ካጓጓዘ በኋላ የዚህ ምሥጢራዊ የአየር ውፅዓተ-ነገድ ወሬ በመሰማቱ በዛሬው ዕለት የማቆሚያ ትዕዛዝ ተላለፈ። በዚህ የስድስት ሳምንት ውፅዓት ፰ሺ ፈላሻዎች ሲሰደዱ ከ፮ ዓመት በኋላ በተደገመው ‘ኦፐሬሽን ሰሎሞን’ ደግሞ ፲፭ሺ አይሁዳዊ ኢትዮጵያውያን ወደ ፳ኤል ተሰደዋል።
ታኅሣሥ ፳፰
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች በዘመነ ዮሐንስ የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት ያከብራሉ። ልደትን የምታከብሩ ሁሉ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም ያደረሳችሁ
- ፲፱፻፳፰ ዓ/ም የቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ቡድን አዲስ አበባ፣ አራዳ አካባቢ ላይ ተመሰረተ።
ታኅሣሥ ፳፱
- ፲፰፻፸፱ ዓ/ም የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊትና የሐረሩ አሚር ዐብዱላሂ ሠራዊት በሜታ ወረዳ፣ ምሥራቅ ሐረርጌ ውስጥ በምትገኘው ጨለንቆ ላይ ገጥመው ከ፴ ደቂቃ ውጊያ በኋላ የዐሚሩ ሠራዊትተሸንፎ ወደሐረር ሸሸ። ወዲያው ሐረር በሸዋው ንጉሥ እጅ ገባች።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፤ አረባዊ ነዳጅ አምራች አገሮች በወቅቱ የነዳጅ ምርታቸውን የፖለቲካ መሣሪያ በማድረጋቸው በአፍሪቃውያን አገሮች ላይ የሚያስከትለውን ተጽዕኖ ለማጥናት አዲስ አበባላይ ተሰበሰቡ።
[ለማስተካከል] ጥር
ጥር ፩ ቀን
- ፲፰፻፸ ዓ/ም ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛትነት የተመኟት እና የአድዋ ጦርነት እንዲጀመር ያዘዙት የኢጣልያ ንጉሥ ቀዳማዊ ኡምቤርቶ በዛሬው ዕለት ሲሞቱ ዳግማዊ ቪቶሪዮ ኢማኑኤል ዙፋኑን ወረሱ።
- ፲፱፻ ዓ/ም - ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ እና በኢትዮጵያ የፈረንሳይ መንግሥት ዋና መላክተኛ ክሎቡኮውስኪ የንግድ እና ወዳጅነት ስምምነት አዲስ አበባ ላይ ተፈራረሙ
- ፲፱፻፵፫ ዓ/ም ኒው ዮርክ ከተማ የሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ሕንጻ ተመረቀ።
- ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ‘አፕል’ (Apple Computer Inc.) የተባለው የአሜሪካ የመቀምር ድርጅት ‘አይ ቲዩንስ’ (iTunes) የተባለውን የሙዚቃ ተሰኪ ስብስብ አካል (software) ሳን ፍራንሲስኮ ላይ አስተዋወቀ።
- ፲፱፻፺፱ ዓ/ም ‘አፕል’ (Apple Computer Inc.) “አይ ፎን” (iPhone) የተባለውን ተንቀሳቃሽ ስልክ አስተዋወቀ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በገጠሪቱ ኢትዮጵያ የሚገኘውን ሕዝብ ለመርዳትና ለማስተማር፣ የመጀመሪያዎቹ "የእድገት በኅብረት የእውቀትና የሥራ ዘመቻ" ወጣቶች ከአዲስ አበባ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ዘመቱ።
- ፲፰፻፺፫ ዓ/ም - የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት አርፈው በደብረ ማርቆስ ተቀበሩ።
ጥር ፬ ቀን፦
- ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በዛንዚባር ደሴት በጊዜው በሱልጣን ይመራ የነበረውን አረባዊ መንግሥት በጆን አኬሎ የሚመራ ሽብርተኛ ቡድን ፈንቅሎ የዛንዚባር ሪፑብሊክን መሠረተ።
- ፲፰፻፹፰ ዓ/ም የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የባቡር ኩባንያ የሀዲድ ሥራውን ውል ተፈራረመ።
ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ጥር 6 ጥር ፯ ቀን
- ፲፱፻፴፮ ዓ.ም. ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ በአዲስ አበባ አዲስ የተሠራውን የመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴን ቤተ ክርስቲያን መርቀው፣ በአምስቱ ዓመት የፋሺስት ጣሊያን ወረራ ወቅት ሰማዕት የኾኑ አርበኞችን ዐፅም አገቡ።
ጥር ፰ ቀን፣
- ፲፱፻፶ ዓ/ም - በኦክላሆማ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ((እንግሊዝኛ) Oklahoma State University) እርዳታ የተመሠረተው የዓለማያ እርሻ ኮሌጅ (ያሁኑ ሐሮማያ ግብርና ዩኒቨርሲቲ) ተመርቆ ተከፈተ፡፡
- ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - የ[:[ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፑብሊክ|ኮንጎ]] የእርስ በእርስ መፈጃጀት በተፋፋመበት ወቅት፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ዳግ ሀመርሾልድ የኢትዮጵያን የሠራዊት ዕርዳታ ለማረጋገጥ ከንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጋር ምጽዋ ላይ ተገናኙ።
ጥር ፱ ቀን
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም የፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ዦርዥ ፖምፒዱ፣ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ግብዣ ኢትዮጵያን ለሦስት ቀናት ለመጎብኘት አዲስ አበባ ገቡ።
ጥር ፲ ቀን፣
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች በዚህ፣ የትልቁ የጥምቀት በዓል ሥነ ሥርዓት መጀመሪያ ዕለት የአጥቢያቸውን ታቦተ ሕግ በማጀብ ወደከተራው ተጉዘው እዚያው ያድራሉ።
- ፲፱፻፹፭ ዓ/ም በ አምሳዎቹም የአሜሪካ ሕብረት ግዛቶች አሁን በየዓመቱ በልደቱ አካባቢ የሚከበረው የጥቁር አሜሪካዊው መሪ የማርቲን ሉተር ኪንግ ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ ተከበረ።
- ፲፱፻፺፯ ዓ/ም እስከ ፭ መቶ ፳፭ መንገዶኞችን የሚያስተናግደው፣ ወደረ ቢሱ ኤየርባስ ኤ፫፻፹ (Airbus A380) የተሰኘው አየር ዠበብ በቱሉስ የፈረንሳይ ከተማ ለዓለም ተገለጸ።
- ፲፱፻፺፱ ዓ/ም በምዕራብ አውሮፓ አገሮች የተነሳ ኃይለኛ አውሎ ንፋስ፣ በብሪታኒያ አሥራ አራት፤ በአለማኝ አሥራ ሦስት ሰዎችን ሲገል በሀያ አገራት ውስጥ አርባ አራት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
ጥር ፲፩ ቀን፣
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ በ፴ ዓ/ም በመጥምቁ ዮሐንስእጅ በዮርዳኖስ ባሕር የተጠመቀበትን ዕለት የሚያስታውሰው፣ ኤጲፋንያ በመባልም የሚታወቀው ደማቅ የጥምቀት በዓል ነው።
- ፲፱፻፶፰ ዓ/ም ኢንዲራ ጋንዲ በሕንድየመጀመሪያዋ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተመረጡ። አባታቸው ጃዋህራል ኔህሩ የአገሪቱ የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር ነበሩ።
ጥር ፲፪ ቀን፣
- ፲፱፻፳፱ ዓ/ም የፋሺስት ኢጣልያ የጦር ዓለቃ ማርሻል ግራትዚያኒ በራሡ መሪነት የራስ ደስታ ዳምጠውን ሠራዊት በሲዳሞ እና የደጃዝማች ገብረ ማርያምን ሠራዊት በ ባሌ ለመውጋት ዘመተ።
ጥር ፲፫ ቀን፣
- ፲፰፻፷፬ ዓ.ም.፣ ደጃዝማች ካሳ ምርጫ (አባ በዝብዝ) በአክሱም ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ስመ መንግሥታቸው "ዮሐንስ ራብዓዊ" (ዮሐንስ ፬ኛ) ተብሎ፣ በጳጳሱ በብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ እጅ ተቀብተው በሥርዓተ መንግሥት ንጉሠ ጽዮን፣ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተብለው ነገሡ። በታሪክ እንደተመዘገበው በዚሁ ንግሥ ምክንያት ሦስት ቀን በዓል ሆኖ፣ ለግብር ፬ ሺህ ሰንጋ ታርዶ፣ ፶ ጉንዶ ማር የፈጀ፣ ፻፶ ሺህ ገንቦ ጠጅ ቀርቦ፣ በደስታ ሲበላ ሲጠጣ ሰንብቷል።
- ፲፱፻፴፫ ዓ/ም የፋሺስት ኢጣሊያን ሠራዊት ጠራርጎ ለማስወጣት የተቀጣጠለውን ዘመቻ ከፍጻሜ ለማድረስ ከሱዳን ድንበር ወደ ኢትዮጵያ የዘለቁት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ አርበኞችና የእንግሊዝ ጦር፣ በኦሜድላ ላይ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ የሆነውንና የይሁዳ አንበሳ ከመሐሉ የሚገኝበት የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማን ተከሉ፤ አውለበለቡ።
- ፲፱፻፵፬ ዓ.ም. ለአዲስ አበባ ሕዝብ የውሃ አገልግሎት የሚሰጠው የገፈርሳ ግድብ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተመረቀ።
- ፲፱፻፶፬ ዓ.ም. ኢትዮጵያ ሦስተኛውን የአፍሪቃ እግር ኳስ ውድድር የግብፅን ቡድን አራት ለ ሁለት አሸንፋ ዋንጫውን ተሸለመች። ለኢትዮጵያ ቀዳሚውን ግብ ያስቆጠረው የቴሌው ግርማ ዘለቀ ሲኾን፣ የጊዮርጊሱ መንግሥቱ ወርቁ በ፹፬ኛውና በ፻፲፯ኛው ደቂቃ ሁለተኛና አራተኛውን፣ ኢታሎ ቫሳሎ በ፻፩ኛው ደቂቃ ሦስተኛውን ለማስገባት ችለዋል። ያልተደገመውንና ሕዝቡም እየናፈቀ ያለው የአፍሪቃ ዋንጫ ለኢትዮጵያ ያስገኙት ፩. ጊላ ሚካኤል ተስፋ ማርያም ፪. ክፍሎም አርአያ ፫. አስመላሽ በርሔ ፬. በርሔ ጎይቶም ፭. አዋድ መሐመድ ፮. ተስፋዬ ገብረ መድኅን ፯. ግርማ ዘለቀ/ተክሌ ኪዳኔ ፰. መንግሥቱ ወርቁ ፱. ሉቻኖ ቫሳሎ (አምበል) ፲. ኢታሎ ቫሳሎ ፲፩. ጌታቸው ወልዴ ሲሆኑ ተጠባባቂዎች ደግሞ ጌታቸው መኩሪያ፣ እስማኤል ጊሪሌ፣ ብርሃኔ አስፋው፣ ኃይሌ ተስፋ ጋብር፣ ነፀረ ወልደሥላሴ ነበሩ። አሰልጣኞች ይድነቃቸው ተሰማ፣ ፀሐየ ባሕረና አዳሙ ዓለሙ፣ ወጌሻው ጥላሁን እሸቴ ነበሩ፡፡
ጥር ፲፬ ቀን፣
- ፲፰፻፲፮ ዓ/ም - በቀድሞዋ 'ጎልድ ኮስት' (አሁን ጋና) የአሻንቲ ብሔረሰብ ሠራዊት የእንግሊዝን ሠራዊት በውጊያ አሸንፈው በአፍሪቃአኅጉር፣ የነጭ ቅኝ ገዥ ሠራዊትን በማሸነፍ የመጀመሪያው ብሔረሰብ ሆኑ።።
- ፲፰፻፸፩ ዓ/ም - በዛሬዪቷ ደቡብ አፍሪካ በእንግሊዝ ሠራዊት እና በዙሉ ብሔረሰብ መኻል በተካሄደው የ'ኢሳንድልዋና'(Battle of Isandlwana) ውጊያ ዙሉዎች አሸናፊ ሆኑ።
- ፲፰፻፺፫ ዓ/ም - በታላቋ ብሪታኒያ እና አየርላንድ ንጉዛት ዙፋን ላይ ለ፷፬ ዓመታት የነገሡት ንግሥት ቪክቶርያ በተወለዱ በ ፹፪ ዓመታቸው አረፉ።
- ፲፱፻፷፪ ዓ/ም የቦይንግ 'ጃምቦ ጄት' በመባል የሚታወቀው ቢ ፯፻፵፯ (Boeing 747) አየር ዠበብ ለመጀመሪያ ጊዜ ተሳፋሪ መንገደኞችን ጭኖ ከኒው ዮርክ ኬኔዲ አየር ጣቢያ ተነስቶ ሎንዶን ሂዝሮው አየር ጣቢያ አረፈ።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም በአገር ውስጥ በረራ ከባህር ዳር ወደ ጎንደር በመብረር ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ DC-3 አየር ዠበብ በአራት የኤርትራ ነጻነት ግንባር አባላት ተጠልፎ ሊቢያ ውስጥ ቤንጋዚ ከተማ አረፈ።
ጥር ፲፭ ቀን፣
- ፲፭፻፵፬ ዓ/ም - በታሪክ ዘገባ በብዛት የሰው ነፍስ የጠፋበት ታላቁ የ'ሻንግዚ' የመሬት እንቅጥቅጥ በቻይና ሲከሰት እስከ ፷ መቶ ፴ ሺህ ሰዎች እንደሞቱ ይገመታል።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - የአዋሽ ፩ኛ እና ፪ኛ ግድቦች የመሠረት ድንጋይ ማስቀመጫ ሥነ ሥርዓት ላይ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መርቀው መሠረቱን ተከሉ።
- ፲፱፻፹፩ ዓ/ም በቀድሞው የሶቪዬት ሕብረት ክልል ፤ በአሁኑ ታጂኪስታን ውስጥ የተከሰተ የመሬት እንቅጥቅጥ ፪፸፬ ሰዎች ገደለ።
- ፲፱፻፷፬ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት በጃፓን ሠራዊት ውስጥ ተሰልፎ የነበረው ፶ ዓለቃ ሾዪቺ ዮኮይ ጦርነቱ ባከተመ በ ሃያ ሰባት ዓመቱ ተደብቆ በኖረበት በጉዋም ጫካ ውስጥ ተገኝቶ ወደአገሩ ሲመለስ «በሕይወቴ ስመለስ ትልቅ እፍረት እየተሰማኝ ነው።» ብሎ ተናገረ። ሾዪቺ ከተመለሰ በኋላ ለሃያ አምስት ዓመታት ኖሯል።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የናዚዎችንና የፋሺስትን ሥርዓት በመጻረር ዝና ያተረፉት ታላቅ የብሪታኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር፤ ወታደር፤ የታሪክ እና የሥነ ጽሑፍ ምሁር እንዲሁም በሥነ ጽሑፍ የኖቤል ሽልማት ተቀባይ የነበሩት ዊንስተን ቸርቺል በተወለዱ በዘጠና አንድ ዓመታቸው አረፉ ።
- ፲፭፻፷፯ ዓ/ም - የቡርቱጋል መርከበኛ ፓውሎ ዲያስ ደ ኖቬሽ የአንጎላን ዋና ከተማ ሉዋንዳ ቆረቆረ።
- ፲፱፻፲፩ ዓ/ም - አንደኛው የዓለም ጦርነት ከተገባደደ በኋላ የዓለም መንግሥታት ማኅበር (The League of Nations) ተመሠረተ።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - የቀድሞው የኡጋንዳ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚልተን ኦቦቴ በሲንጋፖር ላይ በሚካሄደው የጋራ ሀብት አገሮች ጉባዔ ላይ እንዳሉ በጄኔራል ኢዲ አሚን በተመራ ወታደራው መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ወረዱ።
- ፳፻፪ ዓ/ም - ከቤይሩት ከተማ ፹፪ መንገደኞችንና ፰ አብራሪዎችና አስተናጋጆችን ጭኖ ወአዲስ አበባ እያመራ የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ ፯፻፴፯ አየር ዠበብ፣ በረራ ቁጥር ፬፻፱ ባልታወቀ ምክንያት ሜዲተራኒያን ባሕር ላይ ወድቆ ሲሰምጥ ፺ዎቹም ተሳፋሪዎች በሙሉ ተፈጅተዋል። ከነዚህ መኀል ፴፩ ኢትዮጵያውያን ነበሩ።
ጥር ፲፰ ቀን
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - የታላቋ ብሪታኒያ ዳግማዊት ንግሥት ኤልሣቤጥ የ'ፊልድ ማርሻል' (Field Marshal) ማዕርግ ለቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሰጡ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ሌሊቱን በደም ቋጠሮ ምት ታመው በአስቸኳይ ወደእንግሊዝ አገር የእንግሊዝ የጦር አየር ዠበብ ለሕክምና እንዲወስዳቸው ተለመነ። የጦር አየር ዠበብ በማግሥቱ ይዟቸው ወደሎንዶን በረረ።
- ፲፱፻፺፫ ዓ/ም ጉጅራት በሚባለው የሕንድ ግዛት የተከሰተው ዐቢይ የመሬት እንቅጥቅጥ እስከ ፳ሺህ ሰዎችን ሕይወታቸውን አጥፍቷል።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን በአስቸኳይ ለሕክምና በእንግሊዝ የጦር አየር ዠበብ ተሳፍረው ወደሎንዶን በረሩ።
- ፲፱፻፸፪ ዓ/ም - በቀድሞዋ ሮዴዚያ (የአሁኗ ዚምባብዌ) የነጻነት ትግል መሪ ሮበርት ሙጋቤ ከአምስት ዓመት ስደት በኋላ አገራቸው ተመልሰው ሲገቡ እጅግ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።
- ፲፱፻፹፰ ዓ/ም - በኒጄር ለመጀመሪያ ጊዜ በሕዝብ የተመረጡትን ፕሬዚደንት ማማን ኡስማን፣ በኮሎኔል ኢብራሂም ባሬ ማኢናሳራ የተመራ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን አወረዳቸው።
- ፲፱፻፵ ዓ/ም - ሕንዳዊው የሰላማዊ እንቅስቃሴ መሪ ማሀትማ ጋንዲ (Mohandas Karamchand Gandhi} በነፍሰ ገዳይ እጅ ተገደሉ።
- ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - ቻሌንጀር የተባለችው የአሜሪካ የጠረፍ መንኮራኲር ሰባት ጠፈረኞችን ጭኖ እንደተተኮሰ አየር ላይ ፈንድቶ ሲከሰከስ ሰባቱም አሜሪካውያን ሞተዋል።
- ፲፱፻፺፪ ዓ/ም የኬንያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር ፬ መቶ ፴፩ አይቮሪ ኮስት ጠረፍ አትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ ሲወድቅ ፻፷፱ ሰዎች ሞቱ።
- ፲፮፻፸ ዓ/ም - በካቶሊኩ የኢትዮጵያ ንጉሥ ሱሰንዮስ ዘመን መንግሥት፣ በትግራይ የካቶሊክ ሚሲዮንን በማስፋፋት ላይ ተሰማርቶ የነበረው የኢየሱሳዊ ሚሲዮን አባል እና የቡርቱጋል ተወላጁ ጀሮኒሞ ሎቦ አረፈ።
- ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - ኮለምቢያ የተሰኘችው የአሜሪካ የጠፈር መንኲራኩር ከተልዕኮዋ ተመልሳ የምድር የአየር ክልል ውስጥ ስትገባ በደረሰባት የፍጻሜ አደጋ ሰባቱም አብራሪዎቿ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
- ፲፰፻፺፫ ዓ/ም ከረጅም ዘመናት የብሪታንያ ንግሥትነትና የሕንደኬ ንግሥተ ነገሥትነት በኋላ ያረፉት ቪክቶሪያ በዚህ ዕለት ተቀበሩ።
- ፲፱፻፹፪ ዓ/ም የአፓርታይዳዊዋ ደቡብ አፍሪቃ ፕሬዚደንት ደ ክለርክ ለሠላሳ ዓመታት በሕግ ተከልክሎ የነበረውን የአፍሪቃ ብሔራዊ ምክር ቡድን (African National Congress) ሕጋዊ መሆኑንና በወቅቱ በእሥራት ላይ የነበሩትን ኔልሰን ማንዴላ እንደሚፈቱ አስታወቁ።
- ፲፰፻፹፰ ዓ/ም - ወረሂመኑ ተንታ ላይ ልጅ ኢያሱ ከአባታቸው ከራስ ሚካኤል (በኋላ ንጉሥ) እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ሸዋረጋ ምኒልክ (የዳግማዊ ምኒልክ ልጅ) ተወለዱ።
ጥር ፳፮፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፵፮ ኛው ዕለት ሲሆን፤ የበጋ ወቅት ፴፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፪፻፳ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስ፣ ዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፲፱ ቀናት ይቀራሉ።
- ፲፱፻፶፯ ዓ.ም. የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ሕንፃ ተመረቀ። በሕንፃው መግቢያ ላይ የተለጠፈው ሰሌዳ እንዲህ ይላል፤
ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ለመናገሻው ከተማ ለአዲስ አበባ ሕዝባቸው፣ ለማኅበራዊ ኑሮው፣ ለኤኮኖሜውና ለባህሉ ዕድገት አማካይ የአገልግሎት ቤት ይሆን ዘንድ ፈቅደው ያሠሩትን ይህን ሕንፃ፣ በሠላሳ አራተኛው ዘመነ መንግሥታቸው መርቀው ከፈቱ።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - የቻይና ሕዝባዊ ሪፑብሊክ በአዲስ አበባ ኤምባሲ ከፈተች።
- ፲፯፻፷፯ ዓ/ም - የሸዋው መስፍን መርዕድ አዝማች አምኃ ኢየሱስ፣ ሐር-አምባን እንደ እልፍኝ፤ አንኮበርን እንድ አዳራሽ አድርገው ለ፴፬ ዓመታት ከገዙ በኋላ አርፈው እሳቸው ባሠሩት የአንኮበር ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ። ልጃቸው መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ተተክተው የሸዋ መስፍን ሆኑ።
- ፲፰፻፸፯ ዓ/ም - ካይሚ የተባለ የጣልያን የባህር ኃይል መኮንን ምጽዋ ወደብን ይዞ የአገሩን ሰንደቅ ዓላማ ካውለበለበ በኋላ፣ የግብጽ እና የብሪታኒያ መንግሥቶች ወደቡን እንድይዘው ፈቅደውልኛል ብሎ አወጀ።
- ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - ዝነኛው የሬጌ ሙዚቀኛ ሮበርት ኔስታ ማርሊ ተወለደ።
- ፲፰፻፴፬ ዓ/ም - በዘመነ መሣፍንት፣ የራስ አሊ አሉላ ሠራዊት ደብረ ታቦር ላይ ከሰሜኑ ገዥ ደጃዝማች ውቤ ኃይለ ማርያም ሠራዊት ጋር በጦርነት ገጥሞ ድሉ የራስ አሊ ሆነ።
- ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - በፍልውሃ አቅራቢያ በዘመናዊ ዕቅድ አዲስ የተሠራው ኢዮቤልዩ (የአሁኑ ብሔራዊ) ቤተ መንግሥት ተመረቀ
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የአፍሪቃ ኢኮኖሚ ኮሚሲዮን ዋና መሥሪያ ቤትና በአዲስ አበባ ከተማ ለሚደረገው ልዩ ልዩ የአፍሪቃ መንግሥታት ጉባኤዎች መሰብሰቢያ፣ በኢዮቤልዩ ቤተ መንግሥት ፊት ለፊት የተሠራውን የአፍሪካ አዳራሽ፣ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተመርቆ ተከፈተ።
- ፲፱፻፸፭ ዓ/ም - ለባንኮች የስፖርት ክለብ የእግር ኳስ ቡድን እና ለኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን በመሀል ሜዳ መደብ የሚጫወተው ተሾመ አዳሙ ጌጡ በዚህ ዕለት ተወለደ። ተሾመ ወደ ባንኮች ከመዛወሩ በፊት ለመብራት ኃይል የእግር ኳስ ክለብ ይጫወት ነበር።
[ለማስተካከል] የካቲት
የካቲት ፩ ቀን
- ፫፻፹፮ ዓ/ም - በክርስትና ሃይማኖት የተከሰቱትን ተቃራኒ ትምህርቶች በጉባኤ ለመወሰን የቁስጥንጥንያው ንጉሥ ቀዳማዊ ቴዎዶስዮስ ባስተላለፈው ጥሪ መሠርተ ፩፻፶ ሊቃውንት፣ ኤጲስ ቆጶሳት በቁስጥንጥንያ ጉባኤ ተሳትፈው መቅዶንዮስን፤ አፖሊናሪዮስን እና ሌሎችን መናፍቃንን አወገዙ።
- ፲፱፻፵፬ ዓ/ም - በታላቋ ብሪታኒያ እና ሰሜን አየርላንድ ንጉዛት ልዕልት ኤልሳቤጥ አባታቸው ንጉሥ ጆርጅ ሳድሳዊ ሲያርፉ ዙፋኑን ተቀብለው ዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ ሆኑ።
የካቲት ፪ ቀን
- ፲፱፻፴ ዓ/ም - ቡልጋ ጨመሪ ላይ እነ ደጃዝማች ኃብተ ሥላሴ በላይነህ እና ሌሎችም አርበኞችና የፋሺስት ኢጣሊያ ጦር ገጥመው ትልቅ ውጊያ ተደረገ።
- ፲፯፻፰ ዓ/ም - በእስራት ላይ የነበሩት የ ፳፩ ዓመቱ ጎልማሳና የንጉሥ ኢያሱ አድያም ሰገድ ልጅ ዳግማዊ ዓፄ ዳዊት እንደነገሡ አዋጅ ተነገረ።
- ፲፰፻፵፯ ዓ/ም - ደጃዝማች ካሳ (ዓፄ ቴዎድሮስ)ና ደጃዝማች ውቤ ቧሂት ላይ ድንኳን ተክለው ተገናኙ። ደጃዝማች ካሳም የእንግሊዙን ሊቀ መኳስ ዮሐንስን (John Bell)በመንጥር አይተህ ንገረኝ አሉት። የሸማ ድንኳን ባየ ጊዜ ነገራቸው። ደጃዝማች ካሳም «አያሳድረኝ አላሳድረውም» ብለው ተናገሩ። ያንግዜውንም ተነሣ አሉ። ባሰለፉትም ጊዜ እንዴህ ብለው በፍከራ ትንቢት ተናገሩ። «እንኳን ይህን ቁርጥማታም ወሎን፣ መትቼ የሻዋውን ንጉሥ እይዘዋለሁ። ስሜን ስሜን እንግርሀለሁ ያልሁህ ወታደር ስሜም ቴዎድሮስ ነው» አሉ። አስቀድሞ ገና በንጉሥ አምላክ በል። ስሜን ስሜን እነግርሀለሁ ብለው ነበርና። ያንግዜውን እንዴህ አሉ። «ወታደር አይዞህ አትፍራ። የውቤ ነፍጥ የውቤ ነፍጥ ቢልህ የተለጎመው ጨርቅና ባሩድ ነው። አይነካህም» አሉት። እኔ የክርስቶስ በርያ ሁሉንም አሳይሀለሁ ወታደር ባሉ ግዜ ሰልፍ ገጠመ። ደጃች ውቤም ተያዙ።
- ፲፱፻፱ ዓ/ም - ንግሥት ዘውዲቱ፣ "ግርማዊት ዘውዲቱ፣ ንግሥተ ነገሥት ዘኢትዮጵያ" ተብለው በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በሊቀ ጳጳሱ በአቡነ ማቴዎስ እጅ ቅብዐ መንግስት ተቀብተው የንጉሠ ነገሥቱን ዘውድ ጫኑ።
- ፲፱፻፲ ዓ/ም - «ብርሃን ዘ ኢትዮጵያ » በሚል ቅፅል ስም የሚታወቁት የዳግማዊ ምኒልክ ባለቤት፣ እቴጌ ጣይቱ ብጡል አረፉ። ሥርዓተ ቀብራቸውም በእንጦጦ መንበረ ፀሓይ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ተፈጸመ። በኋላ ግን አጽማቸው ተነስቶ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ለአባታቸው ዳግማዊ ምኒልክ አጽም ማሣረፊያ በተሠራው የታዕካ ነገሥት በዓታ ቤተ ክርስቲያን ተቀብሯል።
- ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት በኢራቅ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ለተተካው የኮሎኔል አብዱል ሳላም አሪፍ መንግሥት ሕጋዊ ዕውቀት መስጠቱን አስታወቀ።
- ፲፮፻፹፭ ዓ/ም - ንጉሡ አጼ ኢያሱ ከጳጳሱ አባ ሲኖዳ እና እጨጌ ዮሐንስ ጋር አክሱም እንዳሉ ሙራድ የተባለ ታላቅ ግብጻዊ ነጋዴ በሕንድ ውቅያኖስ መጥቶ ከሆላንድ ንጉሥ ያመጣውን ሰላምታ እና ደብዳቤ አቀረበ።
- ፲፯፻፰ ዓ/ም - ማክሰኞ ዕለት የአጼ ኢያሱ አድያም ሰገድ ልጅ ንጉሥ ዳዊት፣ አጼ ዳዊት አድባር ሰገድ ተብለው ዘውድ ጭነው ነገሡ።
- ፲፰፻፵፯ ዓ/ም - ደጃዝማች ካሳ ደረስጌ ማርያም ላይ አቡነ ሰላማ ቀብተዋቸው ዘውድ ጭነው ዓፄ ቴዎድሮስ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ ተባሉ።
- ፲፭፻፶፭ ዓ/ም - የ ፲፪ ዓመቱ ልጅ ማር (ጌታ) ሠርፀ ድንግል፣ አባታቸው አጼ ሚናስ ሲሞቱ በስመ መንግሥት መለክ ሰገድ ተብለው ነገሡ። አጼ ሠርፀ ድንግል የመንግሥት ሥራቸውን የሚሠሩት በእናታቸው በእቴጌ አድማስ ሰገድ ሥሉስ ኃይላ አማካይነት ነበር።
- ፲፭፻፶፭ ዓ/ም ኢትዮጵያን ከአራት ዓመታት በንጉሥነት የመሯት አፄ ሚናስ (ስመ መንግሥት፣ ቀዳማዊ አድማስ ሰገድ) በዕለተ እሑድ አረፉ፡፡ አጼ ሚናስ የአጼ ገላውዴዎስ ወንድምና የአጼ ልብነ ድንግል ልጅ ነበሩ።
- ፲፱፻፲፮ ዓ/ም - ‘የዓለም አቀፍ የንግድ ሒሣብ መሣሪያዎች ድርጅት’ አይ.ቢ.ኤም(IBM) ተመሠረተ።
- ፲፱፻፴፰ ዓ/ም በዓለም የመጀመሪያው ሁለ-ገብ መቀምር (Electronic Numerical Integrator And Computer) ወይም ኮምፕዩተር ይፋ ተደረገ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የመከላከያ ንዑስ ሸንጎ አባላት አዲስ አበባ ላይ ስብሰባቸውን ጀመሩ።
- ፲፭፻፴፬ ዓ/ም - ኢትዮጵያን ሊረዳ የመጣው የቡርቱጋል ሠራዊት ጦር መሪ ዶም ክርስቶፍ ዳጋማ በአህመድ ግራኝሠራዊት ላይ አምባ ስንኢት በሚባል ሥፍራ ዘመተ።
- ፲፱፻፳፯ ዓ/ም - በሆለታ ገነት፣ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ስም የጦር ተማሪ ቤት ተከፈተ።
- ፲፱፻፵፬ የታላቋ ብሪታኒያ የንግሥት ኤልሳቤጥ አባት ንጉሥ ጆርጅ ሳድሳዊ በዊንድሶር ግምብ በሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎት ቤት ውስጥ ተቀበሩ።
- ፲፱፻፶፬ ዓ/ም - እቴጌ መነን አስፋው በዚህ ዕለት በተወለዱ ፸፫ ዓመታቸው አረፉ።
- ፲፰፻፹፱ ዓ/ም - ራስ አሉላ እንግዳ(አባ ነጋ) በዚህ ዕለት አረፉ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - በአዲስ አበባ የብሥራተ ወንጌል ራዲዮ ጣቢያን ለመትከል በኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት እና የሉተራውያን የዓለም ኅብረት መሃል የውል ስምምነት ተፈረመ።
- ፲፯፻፴፮ ዓ/ም - አጼ ኢያሱ ብርሃን ሰገድ ከጳጳሱ አባ ዮሐንስ እና ከ እጨጌ ኤውስጣቴዎስ ጋር ሆነው አንድ የሶርያ ተወላጅ ነጋዴ በሐሰት ጳጳሱ እኔ ነኝ እያለ ብዙ ሰዎችን በማሳሳቱ አስረው ወደአገሩ አባረሩት።
- ፲፯፻፷፪ ዓ/ም - የስኮትላንድ ተወላጁ ሐዋጼ አህጉር (explorer) ጄምስ ብሩስ በዕለተ ሐሙስ ጎንደር ገባ። እዚሁም እስከ ታኅሣሥ ወር ፲፯፻፷፬ ዓ/ም ድረስ ተቀመጠ።
- ፲፰፻፹፫ ዓ/ም - ታላቁ ደራሲና ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ራስ ቢትወደድ መኰንን እንዳልካቸው ተወለዱ።
- ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በጋቦን የተከሰተው መፈንቅለ መንግሥት ፕሬዚደንት ሌዮን ምባን ከሥልጣን አስወረደ።
- ፲፫፻፳፬ ዓ/ም - ቀዳማዊ አጼ አምደ ጽዮን በደቡብ ኢትዮጵያ እስላማዊ ግዛቶችን ለማስገበር ዘመቱ።
- ፲፱፻፱ ዓ/ም - ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ለራስ ወልደ ጊዮርጊስአቦዬ ዘውድ ጭነውላቸው ንጉሠ ዘቤጌምድርና ስሜን አድርገው ሾሟቸው።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት የመምህራን አድማ ተደረገ። ከዚህም ጋር አብሮ የአዲስ አበባ ታክሲ ነጅዎች አድማ አደረጉ። የታክሲ ነጅዎቹ አድማ ለስድስት ቀናት ቆየ።
- ፲፱፻፷፯ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥትን መስከረም ፪ ቀን የገለበጠውን፣ የኅብረተ ሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር (ደርግ) ለመገርሰስ፣ በቀድሞ አጠራሩ ተጋድሎ ሓርነት ሕዝብ ትግራይ (ተሓሕት"፣ በኋላም ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ተመሠረተ፤ በምዕራባዊ ትግራይ ደደቢት በተባለ ሥፍራም የትጥቅ ትግሉን ጀመረ።
- ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ደራስያን አንድነት ማኅበር (ኢደአማ) ስሙን ወደ ኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር (ኢደማ) የለወጠበት ዕለት።
- ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - ለኢጣሊያ ንጉሣዊ ቤተሰብ አንድ ልዑል በመወለዱ ምክንያት በጄነራል ግራዚያኒ ትዕዛዝ በቀድሞው የገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት (የአሁኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ቅጽር ግቢ ከተሰበሰቡት የአዲስ አበባ ነዋሪዎች፤ ለፋሺስቶቹ ያደሩ ከሀዲ ባንዳዎችና መኳንንት፤ የፋሺስት ባለ ሥልጣናት ወታደሮች በተሰበሰቡበት መኻል፣ አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም የእጅ ቦምብ ወርውረው አደጋ ሲጥሉ ግራዚያኒን ጨምሮ ብዙ ሰዎች ተጎድተዋል። ይኸንን ድርጊት በመበቀል ሰበብ እዚያው ግቢ ውስጥ ከሶስት መቶ በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ተጨፈጨፉ፤ ቀጥሎም የተማሩ ወጣቶች፣ የጦር መኮንኖችና ካህናት፣ የደብረ ሊባኖስ መነኮሳት በሙሉ እየተለቀሙ ተጨፈጨፉ። የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በቤት ውስጥ እያስገቡ ከውጭ ቆልፈው ቤንዚን እያርከፈከፉ አቃጠሉአቸው። በአካፋ፣ በዶማ፣ በመጥረቢያ በተገኙበት ኢትዮጵያውያንን እየቆራረጡ የደም ጎርፍ አወረዱ። ፋሽስቶች የአዲስ አበባንና የአካባቢውን ሕዝብ በጅምላ ጨፈጨፉት። በሶስት ቀናት ፴ሺህ ሕዝብ መስዋዕትነት ተቀበለ።
- ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኢቲ-ኤ-ኤፍ ደብልዩ (ET-AFW) ዲሲ ፫ (Douglas C-47B-10-DK፤ በደቡብ-ምዕራብ ኤርትራ በምትገኘው ባረንቱ ላይ በቦምብ ፍንዳታ ተከስክሶ ሲወድቅ አምስቱም ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል። አየር ዠበቡም ከጥቅም ውጭ ሆኗል።
- ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - የአዲሲቷን ቻይና የሰብዓዊ እና ኤኮኖሚካዊ ገጽታዎች በማነጽ አገሪቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ አሁን የያዘችውን የኤኮኖሚያዊ ኃያልነት ሥፍራ እንድትይዝ ያስቻሏት መሪዋ ዶንግ ዥያው ፒንግ በተወለዱ በ ፺፪ ዓመታቸው አረፉ።
- ፳፻፬ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች የሁዳዴ (ዓቢይ) ጾም ይጀምራሉ።
- ፲፭፻፴፭ ዓ/ም - በዕለተ ረቡዕ አህመድ ግራኝ ወገራ ላይ የንጉሥ ገላውዴዎስን ሠራዊት ገጥሞ በቡርቱጋል ነፍጥ ተመቶ ሲሞት የተረፈው ሠራዊቱ ተሸንፎ ኮበለለ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ በፈነዳው አብዮት፣ የወጥቶ-እብስ ሠራተኞት የሦስት ቀን አድማቸውን ጀመሩ። በ[አዲስ አበባ]] በየቀበሌው እና በየመንገዱ የሚካሄደው ሽብር ቀጥሎ ዋለ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የአፍሪቃ፤ የካሪቢያን እና የሰላማዊ ውቅያኖስ አገሮች የንግድ ሚኒስቴሮች ከአውሮፓ የ ኤኮኖሚክ ኅብረት ጋር የንግድ ግንኙነትን ለማጠንከር አዲስ አበባ ላይ ስብሰባቸውን ጀመሩ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደቻይና የበረራ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በእንግሊዝ አገር ሕክምና ላይ የነበሩትን አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰንን ለመጠየቅ ለአራት ቀን ቆይታ ሎንዶን ገቡ።
- ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ግብጽ እና ሶርያ የአረብ ሪፑብሊ ኅብረትን (United Arab Republic) መሠረቱ። ይሄ የሁለቱ አገሮች ኅብረት ከሦስት ዓመታት በኋላ ቢፈርስም የግብጽ መጠሪያ ስሟ ሆኖ ለብዙ ዓመታት ቆይቷል።.
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ሎንዶን በሕክምና ላይ የነበሩትን የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ፣ መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰንን ለመጠየቅ መጥተው የነበሩት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በዛሬው ዕለት በባኪንግሀም ቤተ መንግሥት ዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ የ’ሻይ’ ግብዣ አደረጉላቸው።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት ፍንዳታ የተፋፋመውን ሽብር ለመቆጣጠር በተወሰደው እርምጃ፣ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ወታደሮችን በአዲስ አበባ ከተማ ቀበሌዎችና ‘ቁልፍ’ ቦታዎች ለጥበቃ አሰማራ።
- ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በግራዚያኒ የሚመራ የፋሺስት ኢጣልያ ሠራዊት በዝዋይ አካባቢ የጦር አዝማቾቹን የራስ ደስታ ዳምጠውን እና የደጃዝማች በየነ መርዕድን አርበኞት ድል አደረጉ። ሁለቱም ኢትዮጵያውያን አዝማቾች ሕይወታቸውን በዚህ ዕለት ሰዉ። ኢጣሊያውያኑ ራስ ደስታን ከያዟቸው በኋላ በጥይት ደበደቧቸው፡፡
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ኢትዮጵያ ላይ በፈነዳው አብዮት አስገዳጅነት የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የሕዝቡን ሸክም ለማቃለል የነዳጅ ዋጋ ቅነሳን የሚያካትት ኤኮኖሚያዊ እርምጃዎችን እንደሚወስድ ይፋ አደረገ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ላይ በፈነዳው አብዮት በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ በልዕልት ፀሐይ ሆስፒታል አካባቢ ተኩስ ተከፈተ። በዚሁ ዕለት የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ለወታደሮች የደሞዝ ጭመራ ለማድረግ መወሰኑን አስታወቀ።
- ፲፭፻፲፱ ዓ/ም - በምድረ አዳል (አሁን አፋር (ክልል)) የባሌው መኮንን ዴገልሃን ሠራዊት ከአህመድ ግራኝ ጋር ጦርነት ገጥሞ የዴገልሃን ሠራዊት በሙሉ ተጨፈጨፈ።
- ፲፱፻፶፭ ዓ/ም - የሉተራውያን ድርጅት በኢትዮጵያ ‘የወንጌል ድምጽ ራዲዮ’ (ብሥራተ ወንጌል ራዲዮ) ጣቢያ አገልግሎቱን ጀመረ።
- ፲፱፻፸፱ ዓ/ም - የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ ሴቶችን የቅስና ሥልጣን ለመቀበል የሚያስችለውን ውሳኔ ከፍ ባለ የድምጽ ብዛት አጸደቀ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት እንቅስቃሴ የወታደሩ ዓመጽ በሐረር፣ ድሬ ዳዋ፣በደብረ ዘይት ዓየር ኃይል እና በምጽዋ የባህር ኃይል ውስጥ ተቀጣጥሎ ተስፋፋ። የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት መላክተኞች ከ፪ተኛ ክፍለ ጦር አባላት ጋር ለመደራደር ወደአስመራ በረሩ።
- ፲፯፻፸፪ ዓ/ም - በኢራን የተከሰተ የመሬት እንቅጥቅጥ ፪ መቶ ሺህ ሰዎችን አጠፋ።
- ፲፱፻፲፬ ዓ/ም - የብሪታኒያ ንጉዛት መንግሥት በራሱ ፈቃድ በግብጽ ላይ የነበረውን ሉዐላዊነት አቁሞ ነጻነትን ለግብጻውያን አሳልፎ ሲሰጥ የውጭ ጉዳይን፤ ግንኙነትን፤ የጦር ሠራዊትንና የግብጽ ሱዳንን አስተዳደር የሚመለከቱ ጉዳዮችን ግን በራሱ አስተዳደር ሥር አስቀረ።
- ፲፱፻፳፯ ዓ/ም - ለዱፖንት ኩባንያ ይሠራ የነበረው ዋላስ ካሮዘርስ ናይሎን (Nylon) ፈጠረ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት ፍንዳታ፣ የወታደሩ አመጽ ተስፋፍቶ አዲስ አበባ የሚገኙ የ፬ተኛ ክፍለ ጦር፤ የጦር ሠራዊት፤ ዓየር ኃይል እና የዋና መሥሪያ ቤት ወታደሮች በከተማው ‘ቁልፍ’ ቦታዎችን በቁጥጥራቸው ሥር አዋሉ። ብዙዎችን የአክሊሉ ሀብተ-ወልድን ሚኒስቴሮች አስረው ያዙ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አቶ እንዳልካቸው መኮንንን ለጠቅላይ ሚኒስትርነት እና ጄኔራል አቢይ አበበን የመከላከያ ሚኒስትር አድርገው ሾሙ። በወቅቱ አዲስ አበባ ላይ ሊካሄድ ተዘጋጅቶ የነበረው የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት ስብሰባ በረብሻው ምክንያት ተሰረዘ።
- ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - የመሬት እንቅጥቅጥ በአርሜኒያ እና አዘርባይጃን አገሮች ፩ ሺህ ፩ መቶ ሰዎች ሲገል፣ በሰሜን ኢራን ደግሞ ፫ ሺህ ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል
- ፲፯፻፴፫ ዓ/ም - የሸዋው መስፍን መርዕድ አዝማች አብዬ አረፉ። ቀብራቸውም በሐር አምባ ሚካኤል ተከናወነ። ልጃቸው መርዕድ አዝማች አምኃ ኢየሱስ ተተክተው ምስፍናውን ያዙ።
- ፲፱፻፷፪ ዓ.ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ከሮማ አየር ዠበብ ጣቢያ ሊነሳ ሲዘጋጅ፣ ሽብርተኞች የጫኑት ቦምብ ተገኝቶ በጥበቃ/ፖሊስ ተወግዷል።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት የሚንስትሮች ምክር ቤት ጉባዔ የኡጋንዳን ልዑካን በጉባዔው ላይ በመሳተፍ ጥያቄ ላይ ስምምነት ባለማግኘቱ ተበታተነ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት የ፬ተኛ ክፍለ ጦር አስሯቸው የነበሩትን ሚኒስቴሮች ፈትተው ለንጉሠ ነገሥቱ አስረከቡ። በዚሁ ዕለት በአዲስ አበባ ተማሪዎች የሰላማዊ ሰልፍ ሲያካሂዱ፣ የክብር ዘበኛ ሠራዊት ደግሞ አመጻቸውን ጀመሩ።
- ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - በብሪታኒያ እና በፈረንሳይ ትብብር የተሰራው ‘ኮንኮርድ’ አየር ዠበብ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፈረንሳይ ከተማ ቱሉዝ ተነስቶ ለ ሃያ ሰባት ደቂቃ የበረራ ሙከራ አደረገ።
- ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - አሁን ዚምባብዌ የምትባለው የቀድሞዋ ሮዴዢያ ነጭ ዜጎች በመሪያቸው ኢያን ስሚዝ ሥልጣን አገሪቱን ከብሪታኒያ ዘውድ ጋር የነበራትን ሰንሰለት በጥሰው በሸፍጥ ሪፑብሊክ አደረጓት።
- ፲፱፻፹፬ ዓ/ም - የቀድሞው የሶቪዬት ኅብረት አባላት የነበሩት አርሜኒያ፤ አዘርባጃን፤ ካዛክስታን፤ ኪሪጂስታን፤ ሞልዶቫ፤ ታጂኪስታን፤ ቱርክሜኒስታን እና ኡዝቤኪስታን እንዲሁም ሳን ማሪኖ በአንድነት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባላት ሆኑ።
- ፲፱፻፪ ዓ/ም - እቴጌ ጣይቱ ብጡል ከሥልጣን ከመውረዳቸው ከሁለት ሣምንት በፊት፣ ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ዕለት ከሰጡት ሹመቶች አንዱ፣ የሐረርጌን ጠቅላይ ገዥነት ለደጃዝማች ተፈሪ መኮንን (በኋላ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ) ነው።
- ፲፱፻፲ ዓ/ም - የቤጌምድር እና የስሜን ንጉሥ ወልደ ጊዮርጊስ ደብረ ታቦር ላይ አርፈው እዚያው ተቀበሩ።
- ፲፱፻፳፯ ዓ/ም - የዐቢይ ጾም ቅበላ ዕለት ዓፄ ኃይለ ሥላሴ መምህር ገብረ ጊዮርጊስን (በኋላ አቡነ ባስልዮስ) እጨጌነት ሾሟቸው።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ፍንዳታ ሑከቱ ወደከርቸሌ እስረኞች ተሸጋግሮ በተከሰተው ረብሻ ፴፮ እስረኞች በጥይት ተገደሉ። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በእንዳልካቸው መኮንን አስተዳደር ውስጥ አዲስ የተሾሙት ሚኒስትሮች ፓትርያርኩ አቡነ ቴዎፍሎስ ፊት ቀርበው ቃለ መኀላቸውን ሰጡ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ በኢትዮጵያእና በሱዳን መንግሥታት መሃል ውይይት ለማድረግ የኢትዮጵያን ልዑካን መርተው ወደካርቱም አመሩ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሕገ መንግሥቱን አጥንቶ የሚያሻሽል ቡድን መሰየማቸውን ይፋ አደረጉ።
- ፲፯፻፹፫ ዓ/ም - ቬርሞንት የአሜሪካ ኅብረት ፲፬ተኛዋ አባል ሆነች።
- ፲፰፻፺፩ ዓ/ም - የባየር መድኀኒት ኩባንያ አስፒሪን የተባለውን መድኀኒት በንግድ-ስም አስመዘገበ።
- ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - ‘ቴሌፎን’ ተብሎ የተሠየመው ፈጠራ የአዕምሯዊ ንብረትነቱ (patent) በአሌክሳንደር ግራሃም ቤል ስም ተመዘገበ።
- ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - ጋና ነጻ በወጣች ማግሥት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አባል ሆነች።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በወለጋ ጠቅላይ ግዛት የቅርፀ ምድር ጥናት ለማካሄድ የሚያስችል የቴክኒክ ስምምነት በኢትዮጵያ እና በጃፓን መሀል ተፈረመ።
- ፲፰፻፹፰ ዓ/ም - ኢጣልያም በአድዋ ጦርነት ድል ከተመታች በኋላ በዚሁ ምክንያት ጠቅላይ ሚኒስትሯ ፍራንቼስኮ ክሪስፒ ሥልጣኑን ለቀቀ።
- ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - የሶቪዬት ሕብረት ባህር ዳር ላይ ፩ ሺህ ተማሪዎችን የሚያስተናገድ የቴክኒክ ትምህርት ቤት እንደምትሠራ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት አስታወቀ
[ለማስተካከል] መጋቢት
- ፲፭፻፺፱ ዓ/ም - በጎጃም ምድር ጎል በተባለ ሥፍራ የንጉሥ አጼ ያዕቆብ እና የአጼ ሱስንዮስ ሠራዊት ጦርነት ገጥመው ድሉ የሱስንዮስ ሆነ። አጼ ያዕቆብ እና ጳጳሱ ዳግማዊ ጴጥሮስ በዚሁ ጦርነት ላይ ሞቱ።
- ፲፰፻፹፩ ዓ/ም - ዮሐንስ ፬ኛ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ በትልቅ ጦርነት ከደርቡሾች ጋር ሲዋጉ መተማ ላይ በእነሱ ውጅ ወደቁ። ሱዳኖቹ አንገታቸውን ቆርጠው እንጨት ላይ ሰክተው ገበያ ለገበያ ለሕዝባቸው አሳዩት።
- ፲፱፻፵፱ ዓ/ም - የአልቃይዳ መሥራችና መሪ ኦሳማ ቢን ላደን በዚኡ ዕለት ተወለደ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ከኢትዮጵያ የሠራተኞች ማኅበራት ድርጅት ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን አስታወቁ።
- ፲፰፻፷፰ ዓ/ም - አሌክሳንደር ግራሃም ቤል ለመጀመሪያ ጊዜ በስልክ ረዳቱን አነጋገረ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - በኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ፣ አራት ኪሎ ላይ በሰላማዊ ሰልፍ የወጡ ተማሪዎችን ፖሊሶች በጢስ ቦምብ እና በዱላ በታተኑ። ተማሪዎቹ የጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድን የአሻንጉልት ምስል አቃጠሉ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ሽብር የአየር በረራ አስተዳደር (Civil Aviation Administration) ሠራተኞች አድማ ተጀመረ። አድማው እስከ መጋቢት ፳፫ ቀን ድረስ ተካሂዷል።
- ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - የኤርትራ ነጻነት ግንባር ቡድን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ ፯መቶ፯ አየር ዠበብ ላይ ፍራንክፈርት አየር ማረፊያ ጣቢያ ላይ ቦምብ አፈነዱ።
መጋቢት ፬
- ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የተመደቡ (ሦስት የሩሲያ ጋዜጠኞችና ሦስት የቼኮዝሎቫኪያ ዲፕሎማቶች)፤ ለተማሪዎች እንቅስቃሴ የገንዘብ እርዳታ አድርገዋል በሚል ወንጀል ከአገር እንዲባረሩ ተደረገ።
- ፲፰፻፲፪ ዓ/ም - የሜይን ግዛት የአሜሪካ ኅብረት ፳፫ተኛዋ ዓባል ሆነች።
- ፳፻፪ ዓ/ም - ታዋቂው የቀድሞ የክብር ዘበኛ ኦርኬስትራ ግጥምና ዜማ ደራሲ/አቀናባሪ ኮሎኔል ሣህሌ ደጋጎ አረፉ።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ እና አልጋ ወራሽ አስፋ ወሰን በደቡብ ኢትዮጵያ የእርሻ ልማት ሊጎበኙ ሄደው፣ የተሳፈሩበት የሩሲያ ኤም ፰ ሄሊኮፕተር ተሽከርካሪው በድንገት ተሰብሮ ሲከሰከስ ሦስት ተመልካቾች ሞተዋል፡ ንጉሠ ነገሥቱ እና አልጋ ወራሹ ግን ምንም ሳይሆኑ ተርፈው ጉዟቸውን በመኪና ቀጥለዋል።
- ፲፸፻፶፭ ዓ/ም - በባሊ ደሴት ላይ የሚገኘው ሦስት ሺ ሜትር ቁመት ያለው የአጉንግ ተራራ በእሳተ ገሞራ ፍንዳታ እስከ አሥራ አንድ ሺ ሰዎችን ፈጅቷል።
- ፲፱፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (UNDP) በእርሻ ልማት መስክ ለአዋሽ ሸለቆ ማልሚያ ሁለት ስምምነቶችን ፈረሙ። በተጨማሪ የዓለም ባንክ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (IDA) በኢትዮጵያ ለከብት እርባታ የሚውል የአምሥት ሚሊዮን ዶላር ዋስትና እንደሚሰጥ አስታወቀ።
- ፲፱፻፹ ዓ/ም - የኤርትራ ነጻነት ግንባር ሠራዊት በአፋበት ግንባር በተሰማራው የ’ናደው እዝ’ ጦር ላይ ከጎንና ከኋላም አስርጎ ሲያጠቃ በኮሎኔል ጌታነህ ኃይሌ የሚመራው የናደው እዝ በከፍተኛ ሽብር ሊሸነፍ ቻለ።
- ፳፻፬ ዓ/ም - በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ፓትርያርክ ሆነው ከ፲፱፻፷፬ ዓ/ም ጀምሮ ለ፵ ዓመታት የእስክንድርያ (ኮፕት) ቤተ ክርስቲያንን የመሩት መንፈሳዊ አባት አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ በዛሬው ዕለት በተወለዱ በ፹፰ ዓመታቸው አረፉ።
- ፲፱፻፯ ዓ/ም - በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት እንግሊዞች በዳርዳኔል ቱርክ ላይ ሲወረሩ አልተከናወንም።
- ፲፱፻፵፭ ዓ/ም - በቱርክ የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ የ ፪መቶ፶ ሰዎችን ሕይወት አጠፋ።
- ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - በምሥራቃዊ ጀርመን ለመጀመርያ ጊዜ የነጻ ምርጫ ተካሄደ።
- ፲፱፻፴፮ ዓ/ም - ስመ ጥሩው አርበኛ ደጃዝማች ዑመር ሰመተር አረፉ፡፡
- ፲፱፻፶፩ ዓ/ም - የናዝሬት ትምህርት ቤት አዲስ አበባ ላይ ተከፈተ፡፡
- ፲፭፻፳፪ ዓ/ም - ከአህመድ ግራኝ ጋር ሽምብራኩሬ በተባለ ቦታ ላይ በተደረገ ጦርነት ራስ ኅዱግ፣ ራስ ማኅፀንቶ፣ ገብረ መድኅን እና ብዙ የኢትዮጵያ ሠራዊት አለቁ።
- ፲፱፻፵፮ ዓ/ም - የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ተመርቆ ተከፈተ፡
- ፳፻፪ ዓ/ም - የአፍሪቃ ኅብረት የሠላምና ጸጥታ ምክር ቤት በማዳጋስካር ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል በለወጡ ግለሰቦችና ተቋማት ላይ የተጣለው ማዕቀብ ተግባራዊ እንዲሆን ወሰነ፡፡
- ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በአፓርታይዳዊ ደቡብ አፍሪቃ፣ በታሪክ ዘገባ ‘የሻርፕቪል ፍጅት’ (Sharpeville Massacre) በሚባለው ክስተት ፖሊሶች በጥቁር ሕዝብ ላይ ተኩስ ሲከፍቱ ፷፱ ጥቁሮች ሲገደሉ ፻፹ ሰዎች በጥይት የቁስል አደጋ ደርሶባቸዋል።
- ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - የደቡብ-ምዕራብ አፍሪቃ ትባል የነበረችው አገር ከሰባ አምሥት ዓመታት የቅኝ ግዛትነት በኋላ ናሚቢያ ተብላ ከአፓርታይዳዊ ደቡብ አፍሪቃ ነጻ ወጣች
- ፲፰፻፵፱ ዓ/ም - በጃፓን የተከሰተ የመሬት እንቅጥቅጥ የ ፻ ሺህ ሰዎችን ነፍስ አጠፋ
- ፲፰፻፺፰ ዓ/ም - ልዑል ራስ መኮንን ቁልቢ ላይ አርፈው ቀብራቸው ሐረር ላይ እሳቸው በተከሉት በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተከናወነ።
- ፲፱፻፲፩ ዓ/ም - በጣልያን ከተማ ሚላኖ፣ ቤኒቶ ሙሶሊኒ የፋሺስት ፓርቲን መሰረተ።
- ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የአለማኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአዶልፍ ሂትለር የሚመራው የሚንስትሮች ሸንጎ በራሱ ሥልጣን ሕግ መደንገግ የሚያስችለውን ሕግ (ሕጋዊ አምባ ገነንነት) ደነገገ።
- ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - በአይሮፍሎት በረራ ቁጥር ፭፻፺፫ ላይ ተሳፍረው የነበሩ ፸፭ ሰዎች፤ የአብራሪው የ ፲፭ ዓመት ልጅ አየር ዠበቡን በ’ስህተት’ ከአውቶ-ፓይለት በመሰረዙ ሳይቤርያ ውስጥ ተከስክሰው አለቁ።
- ፲፰፻፺፪ ዓ/ም - ራስ ዳርጌ ሣህለ ሥላሴ በተወለዱ በ ፸ ዓመታቸው አርፈው በደብረ ሊባኖስ ተቀበሩ። ራስ ዳርገ የዳግማዊ ምኒልክ አጎት ነበሩ።
- ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ የመጀመሪያውና ሦስተኛው ፕሬዚደንት ዴቪድ ዳኮቡሺያ በምትባል መንደር ተወለዱ
- ፲፱፻፲፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ መንግሥት አልጋ ወራሽ እና ባለሙሉ ሥልጣን እንደራሴ ራስ ተፈሪ መኮንን «ስለ ባሮች አስተዳደርና ነፃነት የቆመ ደንብ» በሚል ርእስ የተጻፈ ባለ አሥር ገጽ መመሪያ አሳተሙ። በአገሪቱም “ባሪያ” እንዳይሸጥ፣ እንዳይገዛ የሚከለክል አዋጅ መጋቢት ፳፪ ቀን ታወጀ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት ንቅንቅ፣ በኮሎኔል የዓለም ዘውዴ የተመራ የአየር ወለድ ሠራዊት በደብረ ዘይት የአየር ኃይል ረብሸኞችን በመምታት በቁጥጥር ስር አዋለ። ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የባለ ሥልጣናትን አቋም እና ወንጀል የሚያጠና አጣሪ ሸንጎ እንደመሠረቱ አስታወቁ።
- ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - የግብጽ ፕሬዚደንት አንዋር ሳዳት እና የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ምናኽም ቤጊን በአሜሪካ ርዕሰ ከተማ ዋሺንግተን ዲሲ ላይ የሰላም ውል ተፈራረሙ።
- ፲፰፻፸ ዓ/ም - ዓፄ ዮሐንስ እና የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ወሎ፣ ቦሩ ሜዳ ላይ ተገናኝተው ንጉሥ ምኒልክ የንጉሠ ነገሥቱን የበላይነት መቀበላቸውን እና ዓፄ ዮሐንስ ደግሞ የምኒልክን በሸዋ ላይ ንጉሥነታቸውን በመቀበል በመሐላ ታረቁ። ንጉሠ ነገሥቱ ለንጉሥ ምኒልክም ዘውድ ጫኑላቸው።
- ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - የንግድ እና ኢንዱስትሪ ማዕከል እንዲሁም የቱርክ ርዕሰ ከተማ የሆነችው ‘አንጎራ’ ስሟ ተለውጦ አንካራ ስትባል፤ የአገሪቱ አንደኛ ከተማ እና በሮማይስጡ ቄሳር ቁስጥንጢኖስ የተመሠረተችው ቁስጥንጢንያ ወይም ኮንስታንቲኖፕል (Constantinople) ስሟን ቀይራ ኢስታንቡል ተባለች።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አብዮት ሲፈነዳ ከተሰነዘሩት ዐበያት ሕዝባዊ እሮሮዎች አንዱ በመሳፍንቱ፣ መኳንንቱ፣ ሚኒስትሮችና ባለሥልጣናት ግፈኝነት እና ሙስና ስለነበር ይሄንኑ ጉዳይ እንዲያጠና የተመሠረተው ኮሚሲዮን አባላት ተሠየሙ።
- ፲፱፻፸፮ ዓ/ም - ለ መብራት ኃይል የእግር ኳስ ክለብ፤ የኢትዮጵያ ቡና የእግር ኳስ ክለብ እና የድሬ ዳዋ ባቡር የእግር ኳስ ክለብ እንዲሁም በቅርቡ ደግሞ ለየመን የአል ሳቅር የእግር ኳስ ክለብ ተጫዋቹ ዮርዳኖስ አባይ በዚህ ዕለት ተወለደ
- ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - በደቡብ አፍሪቃ ሪፑብሊክ ፤ በጆሃንስበርግ ከተማ፣ በዙሉዎችና ‘የአፍሪቃ ብሔራዊ ሸንጎ’ (African National Congress) ደጋፊዎች መኻል በተከሰተው ሽብር አሥራ ስምንት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - ክቡር ፀሐፊ ትዕዛዝ አክሊሉ ሀብተ ወልድ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጠቅላይ ሚኒስትር ኾነው ተሾሙ።
- ፲፱፻፬ ዓ/ም የሞሮኮ መሪ ሱልጣን አብደልሃፊድ አገሪቱን በፈረንሳይ ጥላ ሥር ያደረገውን ስምምነት ፈረሙ። ሞሮኮ ከ ፵፬ ዓመት በኋላ መጋቢት ፳፱ ቀን ፲፱፻፵፰ ዓ/ም በ ግርማዊ ዳግማዊ ሀሰን መሪነት ነጻነቷን ተቀዳጀች።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም የታኅሣሥ ግርግር በመባል በታሪክ መዝገብ የሚታወቀውን የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ በግንባር ቀደምነት ያካሄዱት የክብር ዘበኛ አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ ነዋይ በተቀበሉት ፍርድ መሠረት በስቅላት ተቀጡ።
- ፲፱፻፲፮ ዓ.ም፣ ልዑል አልጋወራሽ ተፈሪ መኰንን የባርያ ነፃነትን ደንብ አቆሙ/ደነገጉ።
- ፲፱፻፳፰ ዓ.ም.፣ ኢትዮጵያ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አዝማችነት ከኢጣሊያን ሠራዊት ጋር በማይጨው ጦርነት ገጠመች
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም የዓፄ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት፣ የታኅሣሥ ግርግር መሪ የነበሩት ሜጀር ጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ በተሰቀሉ ማግሥት በተደረገው ሹም ሽር ጸሐፌ ትእዛዝ አክሊሉ ሀብተ ወልድ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ሲሾሙ፣ በጊዜው በሎንዶን አምባሳዶር የነበሩት ልጅ እንዳልካቸው መኮንን ደግሞ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚንስትር ሆነው ተሾሙ። ልጅ እንዳልካቸው የ ስድሳ ስድስቱ አብዮት ሲፈነዳ ጸሐፌ ትእዛዝ አክሊሉን በመተካት ከ ሠላሳ ሦስቱ ድል በኋላ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ሦስተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል። ሁለቱም ጠቅላይ ሚኒስቶች በዚሁ አብዮት ተገድለዋል።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ፓሪስ የመንገደኛ መሥመር፣ የመጀመሪያውን በረራ አከናወነ።
- ፲፱፻፺፪ ዓ/ም በኢትዮጵያ በሆቴሎች እና በቱሪዝም የሥራ ዘርፍ ፋና ወጊ በመሆን ሀገራቸውን ለበርካታ ዓመታት ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ በቀለ ሞላ በተወለዱ በ፹፯ ዓመታቸው ቀን ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
- ፲፮፻፩ ዓ/ም – አጼ ሱስንዮስ የደብረ ዘይት ዕለት በአክሱም ጽዮን (ርዕሰ አድባራት ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ፅዮን) ቤተ ክርስቲያን፣ በስመ መንግሥት ሥልጣን ሰገድ ተሰይመው ነገሡ።
- ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በንጉሠ ነገሥት ዙፋን ተቀመጡ፡፡
- ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ በነገሡ በአሥራ ሦሥት ዓመት ተኩል በ፶፬ ዓመት ዕድሜያቸው ዐረፉ። አባታቸው ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ በተቀበሩበት በታዕካ ነገሥት በዓታ ቤተ ክርስቲያን ተቀበሩ።
- ፲፱፻፺፯ ዓ/ም - የካቶሊኩ ሊቀ ጳጳስ ዳግማዊ አቡነ ዮሐንስ-ጳውሎስ በ፹፬ ዓመት ዕድሜያቸው አለፉ።
- ፳፻፫ ዓ/ም - ታላቁ የኢትዮጵያ የህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ተቀመጠ።
- ፲፰፻፷ ዓ/ም - የዓፄ ቴዎድሮስ ትልቁ መድፍ፣ 'ሴባስቶፖል' ከስድስት ወራት ጉዞ በኋላ በዚህ ዕለት መቅደላ ምሽግ ስር ሰላምጌ ደረሰ።
- ፲፰፻፹፫ ዓ/ም - የግርማዊት እቴጌ መነን አስፋው ልደት።
- ፲፰፻፺፯ ዓ/ም - ‘የካንግራ ሸለቆ’ በሚባለው የሕንድ ግዛት ውስጥ የተከሰተው እሳተ ገሞራ የ ፳ ሺ ሰዎችን ሕይወት ሲያጠፋ የአካባቢውን ከተማዎችና ሠፈሮች አውድሟል።
- ፲፱፻፵፩ ዓ/ም - አሥራ ሁለት ምዕራባውያን አገሮች፤ የአሜሪካ ኅብረት፣ ታላቋ ብሪታንያ፣ ፈረንሲስ፣ ቤልጂግ፣ ሆላንድ፣ ዴንማርክ፣ ኢጣልያ፣ ሉክሳምቡርግ፣ ኖርዌይ፣ አይስላንድ፣ ካናዳ እና ብርቱጋል በስምምነት የሰሜን አትለንቲስ የውል ድርጅት (North Atlantic Treaty Organization (NATO) ) መሠረቱ
- ፲፱፻፷ ዓ/ም - በአሜሪካ የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና የጥቁር አሜሪካውያን መሪ የነበረው ታናሹ ማርቲን ሉተር ኪንግ ጄምስ ኧርል ሬይ በተባል ነፍሰ ገዳይ እጅ በሜምፊስ ከተማ ተገደለ። የኪንግ ሞት ዜና ሲሰማ በ መቶ የአሜሪካ ከተሞች ከፍ ያለ የሕዝብ ሽብር ተከተለ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኒው ዮርክ መንታ ሰማይ-ጠቀስ ፎቆች (‘የዓለም የንግድ ማዕከል’ World Trade Center ) ሕንፃ ግንባታ ተጠናቀቀ። እነዚህ መንታ ፎቆች መስከረም ፩ ቀን ፲፱፻፺፬ ዓ/ም በአመጽ የአየር ዠበብ ግጭት ወድመዋል።
- ፲፭፻፶፩ ዓ/ም - የስቅለት ዓርብ ዕለት በአዋሽ አካባቢ ከአዳሉ አሚር ኑር ጋር በተደረገ ጦርነት ላይ ዓፄ ገላውዴዎስ እና የደብረ ሊባኖስ እጨጌ ዮሐንስ ተገደሉ። በሐረሩ ዘእና መዋዕል ዘገባ አሚር ኑር የንጉሠ ነገሥቱን ጭንቅላት ወደይፋቱ ሡልጣን ሳዳዲን ልኮ ዘመቻውን ቀጠለ። ወንድማቸው ዓፄ ሚናስ በስመ መንግሥት አድማስ ሰገድ ተብለው በኢትዮጵያ አልጋ ተክተዋቸው ነገሡ።
- ፲፱፻፳፪ ዓ/ም - የብሪታንያ ቅኝ ገዚዎች በሕንድ ሕዝብ ላይ ጭነውት የነበረውን የ’ጨው ቀረጥ’ ሕዝቡ በማህተማ ጋንዲ መሪነት በሠላማዊ ሰልፎች መቃወሙን ቢያሳይም ትግሉ አልተሳካለትም ነበር። ነገር ግን ጋንዲ ወደ ጨው-ባሕር ወርደው ከባሕር ውሐ ጨው በነጻ ማውጣት በመቻላቸው ቅኝ ገዥዎቹ እስከዚያ ጊዜ ድረስ በሕዝቡ ላይ አውጀውት የነበረውን የጨው ፍብረካ ባለቤትነት የግዳጅ ቀንበር ሰብሮታል።
- ፲፱፻፴፫ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከስደት ዘመን በኋላ በኢትዮጵያ አርበኞች ትግል እና በብሪታኒያ ሠራዊት እርዳታ የጣሊያንን ሠራዊት ድል እየመቱ ደብረ ማርቆስ ከተማ ገቡ፡፡ በምሥራቅ ኢትዮጵያ የተንቀሳቀሱ አርበኞችም አዲስ አበባን በዚሁ ዕለት ያዙ፡፡
- ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - የርዋንዳ እና የቡሩንዲ ፕሬዚዳንቶች አብረው የተሳፈሩበት አየር ዠበብ በርዋንዳዋ ርዕሰ ከተማ ኪጋሊ አካባቢ ላይ በደረሰበት አደጋ ሁለቱም ፕሬዚናንቶች ሞተዋል።
- ፲፱፻፵ ዓ/ም - የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሥሩ የሚተዳደር ዓለም አቀፍ የሕዝብ ጤንነት ባለ ሥልጣን ድርጅት - ‘የዓለም ጤንነት ድርጅት’ን ( The World Health Organization (WHO)) መሠረተ።
- ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - በርዋንዳ በጎሳ ልዩነት ላይ የተመሠረተው የእርስ በእርስ ፍጅት፣ የሁቱ ጎሠኞች እስከ ፰ መቶ ሺ የሚሆኑ የቱትሲ ብሔር ተወላጆችን ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ ታይቶም ተሰምቶም በማያውቅ ሁኔታ ፈጇቸው። የውጭ መንግሥታትን በጉዳዩ ጣልቃ እንዳይገቡ በተጤነ ዕቅድ፣ የርዋንዳ ሠራዊት በዚሁ ዕለት አሥር የቤልጂግ ጸጥታ አስከባሪ ወታደሮችን ገድለዋል።
- ፲፱፻፴፰ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመጀሜሪያ ጊዜ የዓለም አቀፍ በረራውን ከአዲስ አበባ ተነሥቶ በአስመራ በኩል በምስር ርዕሰ ከተማ ካይሮ ላይ አከናወነ።
- ፲፱፻፵፭ ዓ/ም - በኬንያ ‘የአፍሪቃ ኅብረት እንቅስቃሴ’ መሪ የነበሩት ጆሞ ኬንያታ ድርጅቱ በቅኝ ገዝዎቻቸው ላይ የ’ማው ማው’ ሽብርን አካሂዷል በሚል በተሰነዘርበት ክስ ኃላፊነት አለብዎ ተብለው ለሰባት ዓመት የጽኑ እሥራት ቅጣት ተፈረደባቸው።
- ፲፱፻፺፯ ዓ/ም - የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ጳጳስ አቡነ ዳግማዊ ዮሐንስ-ጳውሎስ የቀብር ሥነ ሥርዓት በቫቲካን የቅዱስ ጴጥሮስ ‘ባዚሊካ’ የዓለም መሪዎችና ምዕመናን በተገኙበት ተከናወነ።
[ለማስተካከል] ሚያዝያ
- ፲፱፻፶፩ ዓ/ም - የአሜሪካ የጠፈር በረራና ምርመራ ባለሥልጣን (NASA the National Aeronautics and Space Administration) ’መርኩሪ’ በሚባለው የአገሪቱ የመጀመሪያ የሰው አሳፋሪ መንኮራኩር መርሐ-ግብር የሚሳተፉትን ጠፈርተኞች ለዓለም አስተዋወቀ። እነርሱም፦ ስኮት ካርፔንተር፣ ጎርደን ኩፐር፣ ጆን ግሌን፣ ቨርጅል ግሪሰም፣ ዎልተር ስኪራ፣ አላን ሼፈርድ እና ዶናልድ ስሌይተን ነበሩ።
- ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ሁለት የብሪታንያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፤ ብራያን ሃሪሶን (Brian Harrison) እና ጄምስ ስሌተር (James Slater) ለጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ። ከንጉሠ ነገሥቱም ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል።
- ፲፱፻፷ ዓ/ም - የጥቁር አሜሪካዊው የሰብዓዊ መብት መሪ የዶክቶር ማርቲን ሉተር ኪንግ የቀብር ሥነ-ሥርዓት በተወለዱበት ከተማ በአትላንታ ተከናወነ። የጆርጂያ ክፍለ-ሀገር ገዥ ሌስተር ማደክስ ዶክቶር ኪንግ የ’ሀገር ጠላት’ ነበሩ በሚል አቋም እቀብሩ ላይ አልሳተፍም ብለው መቅረታቸው ሳይበቃ ለሟቹም ክብር የክፍለ ሀገሩን መንግሥታዊ ቢሮዎች እንደማይዘጉ አስታወቁ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የቡልጋሪያ ባለ ሥልጣናት ከኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ጋር በሁለቱ አገሮች መኻል የባህላዊ ግንኙነት እና ልውውጥ ለመወያየት አዲስ አበባ ገቡ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በጠቅላይ ሚኒስትር እንዳልካቸው መኮንን የሚመራው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ሕገ መንግሥታዊ የዘውድ ሥርዓትን ለመመሥረት የታዘዘውን አጥኒ ሸንጎ በማንኛውም ጉዳይ እንደሚተባበረውና እንደሚረዳው አረጋገጠ። አያይዞም መሬትን በተመለከተ በአገሪቱ ውስጥ ማንም ሰው ለማልማት ከሚችለው በላይ መሬት መያዝ እንዳይችልና ለወደፊት ከአርሶ አደሮች በስተቀር የእርሻ መሬት ለማንም እንደማይሰጥ ለማድረግ የሚያስችል ሕግ እንደሚወጣ አስታወቀ።
- ፲፱፻፳፰ ዓ/ም - የፋሺስት ኢጣልያ ሠራዊት ኢትዮጵያን አጥቅቶ ወረራ በመጀመሩ የብሪታኒያ መንግሥት በኢጣልያ ላይ ቅጣት እንዲጣል በመገፋፋትና እና በራሱ በኩልም በአውሮፓ ጦርነት የሚያቀጣጥል ቢሆንም እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ።
- ፲፱፻፷፪ ዓ/ም - ‘ቢትልስ’ (Beatles) የሚባለው የሙዚቃ ቡድን አባላት እርስ በእርስ ባለመስማማታቸው እንደተበተኑ የቡድኑ አባል የነበረው ፖል መካርትኒ ይፋ አደረገ።
- ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - በደቡብ ኢራቅ የተከሰተው የመሬት እንቅጥቅጥ እስከ ፭ ሺህ ፫ መቶ ሰዎችን ነፍስ አጥፍቷል።
- ፲፰፻፷ ዓ/ም - የስቅለት ዓርብ ዕለት በ ሎርድ ናፒዬር የሚመራው የእንግሊዝ ሠራዊት እና የዓፄ ቴዎድሮስ ሠራዊት በመቅደላ ተራራ ሥር በምትገኘው እሮጌ በምትባል ሥፍራ ላይ ጦርነት ገጥመው የዓፄ ቴዎድሮስ የጦር አዛዥ የነበሩት ፊታውራሪ ገብርዬ ሞቱ።
- ፲፱፻፫ ዓ/ም - የልጅ ኢያሱ ሞግዚት የነበሩትራስ ቢትወደድ ተሰማ ናደው አልፈው በደብረ ሊባኖስ ተቀበሩ።
- ፲፱፻፵፬ ዓ/ም - የአዲስ አበባው ሊሴ ገብረ ማርያም ትምሕርት ቤት ተመረቀ፡፡
- ፲፱፻፷ ዓ/ም - የአሜሪካ ፕሬዚደንት ሊንደን ጆንሰን ጥቁር አሜሪካውያን ላይ የነበረውን የመኖሪያ ቤት ጭቆና ሕገ-ወጥ የሚያደርግ የሰብዓዊ መብት ሕግ አጽድቀው ፈረሙ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ ስለ ጋራ ጉዳዮች ለመወያየት የሰሜን አፍሪቃ አገሮችን መጎብኘት ጀመሩ።
- ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - በታንዛኒያ መንግሥት ድጋፍ የተንቀሳቀሱ የኡጋንዳ ታጋዮች የአገሪቱን በትረ-ሥልጣን ከአምባ ገነኑ ኢዲ አሚን እጅ ፈልቅቀው ጨበጡ። አሚን ሸሽቶ ወደሊቢያ ኮበለለ።
- ፲፱፻፴፯ ዓ/ም ለአሥራ ሁለት ዓመታት አገራቸውን በፕሬዚደንትነት የመሩት አሜሪካዊው ፍራንክሊን ዴላኖ ሩዝቬልት በዛሬው ዕለት አለፉ። ሩዝቬልት የአሜሪካ ፴፪ኛው ፕሬዚደንት ነበሩ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የሶቪዬት ሕብረት የመጀመሪያውን ጠፈርተኛ፣ የ፳፯ ዓመት የአየር ኃይል አባል ዩሪ ጋጋሪንን በመኖራኩር ተኮሰች። ጋጋሪን በጠፈር በረራ ምድርን ለአንድ ሰዓት ከአርባ ደቂቃ ያህል ከዞረ በኋላ ወደመሬት ተመልሷል።
- ፲፱፻፸፫ ዓ/ም - የአሜሪካ የበረራ እና የጠፈር አስተዳደር ድርጅት (NASA) ‘ስፔስ ሻትል’ በመባል የሚታወቀውን አየር ዠበብ/የጠፈር መንኮራኩር ለመጀመሪያ ጊዜ ወደጠፈር ተኮሰ። ይኽ የመጀመሪያው አየር ዠበበ/መንኮራኩር ‘ኮለምቢያ’ (Columbia) የተባለው ሲሆን ሃያ ሰባት ጊዜ ወደጠፈር ተተኩሶ ከተመለሰ በኋላ ጥር ፳፬ ቀን ፲፱፻፺፭ ዓ/ም ተመልሶ ወደምድር ሲገባ ተቃጥሎ ተሰባበረ።
- ፭፻፭ ዓ.ም.፣ ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ተወለደ።
- ፲፱፻፲፰ ዓ.ም.፦ ቤተ ሳይዳ (በኋላ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሆስፒታል ፣ አሁን የካቲት ፲፪ የተባለው) ሆስፒታል ተቋቋመ፡፡
- ፲፱፻፵፫ ዓ.ም. ፦ ፪ ሺህ ፻፷፰ ወታደር ያሰለፈው የኢትዮጵያ የክቡር ዘበኛ ሠራዊት፣ ቃኘው የሻለቃ ጦር ወደ ኮርያ ዘመተ። ከዘማቾቹ ማህል አንዱ የነበረው ‘የክራሩ ጌታ’ የ፶ ዐለቃ ካሣ ተሰማ "እልም አለ ባቡሩ" በሚለው ዘፈኑ ይሄንን ዕለት አወድሶታል።
- ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - አንጋፋው የፊልም ተዋናይ ሲድኒ ፗቲዬር ‘ሊሊስ ኦፍ ዘ ፊልድ’ (Lilies of the Field) በተባለው ፊልሙ የ’ኦስካር’ ሽልማት ሲቀበል የመጀመሪያው ጥቁር አሜሪካዊ ነው።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የአፍሪቃ አንድነት ድርጅት (አ. አ.ድ) ((እንግሊዝኛ)፡ Organisation of African Unity (OAU)) የአፍሪቃ የሠራተኞች ማኅበራት የአንድነት ውል አዲስ አበባ ላይ ተፈረመ።
- ፲፰፻፷ ዓ/ም - የፋሲካ ማግሥት ዕለት መቅደላ አምባ ላይ የዓፄ ቴዎድሮስ ሠራዊት እና በሎርድ ኔፒዬር የተመራው የእንግሊዝ ሠራዊት ጦርነት ገጥመው፣ ድሉ የእንግሊዞች ሆነ። ንጉሠ ነገሥቱ ዓፄ ቴዎድሮስ በእንግሊዞች እጅ ከመውደቅ እራሳቸውን ማጥፋትን መርጠው ሽጉጣቸውን ጠጥተው ሞቱ። ቀብራቸው በመቅደላ መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ተከናወነ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አብዮት ከተጀመረ በኋላ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴየልጅ ልጃቸው ልዑል ዘርዓ ያዕቆብ በወቅቱ በሕክምነ ላይ ለነበሩት መርዕድ አዝማች አስፋ ወሰን ተጠባባቂ አልጋ ወራሽ እንደሆኑ በይፋ አስታወቁ። ይሄም ማብራሪያ የንጉሠ ነገሥቱ የሁለተኛ ወንድ ልጅ የነበሩት የሟቹ የልዑል መኮንን ወንዶች ልጆች በዕድሜ የዘርዓ ያዕቆብ ታላላቆች ቢሆኑም ለዘውዱ ውርስ ቅደም ተከተል ግን ከአስፋ ወሰን ወንድ ልጅ ተከታይ እንደሆኑ አረጋግጧል።
- ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - የኡጋንዳው አምባ ገነን ኢዲ አሚን በታንዛኒያ ሠራዊት እርዳታ ከተገለበጠ በኋላ ዩሱፍ ሉሌ የአገሪቱ አዲስ ፕሬዚደንት በመኾን ቃለ መሀላቸውን ፈጸሙ።
- ፲፰፻፶፯ ዓ/ም - አሥራ ስድስተኛው የአሜሪካው ፕሬዚደንት አብርሀም ሊንከን የመድረክ ትርዒት በሚያዩበት የፎርድ ቴአትር ውስጥ ነፍሰ ገዳዩ ጆን ዊልክስ ቡዝ በጥይት መታቸው። ሕይወታቸው በማግሥቱ አለፈች።
- ፲፱፻፶ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለአፍሪቃ ተማሪዎች የነጻ ትምህርት ዕድል እንደምትሰጥ በጋና ከተማ አክራ ጉባኤ ላይ የተገኙት ክቡር አቶ አበበ ረታ አስታወቁ፡፡
- ፲፰፻፶፯ ዓ/ም ፲፮ኛው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት አብርሀም ሊንከን በነፍሰ ገዳይ ጥይት በተመቱ በማግሥቱ አረፉ።
- ፲፱፻፵፫ ዓ/ም - አንድ ሺ አንድ መቶ ሃምሣ ሦስት (፩ሺ ፻፶፫) መኮንኖችና ወታደሮች ያካተተው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የሻለቃ ጦር በተ.መ.ድ. ሥር ተሰማርቶ በኮሪያጦርነት ለመሳተፍ በዚህ ዕለት ከጂቡቲወደብ ተሣፈረ።
- ፲፭፻፴፬ ዓ/ም - በግራኝ መሀመድ እና በብርቱጋል ሠራዊት መኻል ብርቱ ጦርነት ተካሄደ። ብዙ ሰዎች በጥይት ቀኦሰሉ፣ ሞቱ።
- ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ለሚቀጥለው ዓመት የወጪ እቅድ (Budget) ፮ መቶ ፴፫ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር እንደሚሆን ይፋ አደረገ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት ትግል ድሬ ዳዋ ላይ ፖሊሶች በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ ተኩስ ከፍተው ስድስት ሰዎችን አቆሰሉ። በምጽዋ እና አስመራ የባሕር ወደብ እና የምድር ባቡር ሠራተኞች አድማቸውን ጀመሩ።
- ፲፱፻፵፮ ዓ/ም - በግብጽ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ኮሎኔል ጋማል አብደል ናስር ሥልጣን ጨበጡ።
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - ስመጥሩው ኢትዮጵያው አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በአርሲ፣ አሰላ ከተማ ተወለደ።
- ፲፱፻፵፯ ዓ/ም - የጀርመን ተወላጁ የተፈጥሮ ሕግጋት ጥናት ሊቅ አልበርት አይንስታይን በተወለደ በሰባ ስድስት አመቱ አረፈ።
- ፲፭፻፶፫ ዓ/ም የ፲፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ታላቅ ደራሲ የደብረ ሊባኖስ እጨጌ ዕንባቆም አረፉ።
- ፲፮፻፹፰ ዓ/ም - የሆሣዕና በዓል ማግሥት የኢትዮጵያ ርዕሰ ከተማ በነበረችው በጎንደር ከተማ በአንዲት ሴት-አዳሪ ቤት የተነሳ እሳት በ’ግራ ቤት’ አካባቢ ያሉትን ቤቶች በሙሉ ከመፍጀቱም ባሻገር፤ የቅዱስ ጊዮርጊስ፣ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት እና የኢየሱስ አብያተ ክርስቲያናትም ተቃጥለዋል።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት እንቅስቃሴ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ልጅ እንዳልካቸው መኮንን የፖሊስ ሠራዊት አባላትን አነጋገሩ። በዚሁ ዕለት የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር አክሊሉ ኃብቴ ሥራቸውን ለቀቁ።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የቡሩንዲን ንጉዛት የሁለት ቀን ጉብኝት ጀመሩ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የአብዮት ቃጠሎ ወደ ፴ሺ የሚጠጉ የእስልምና ተከታዮች አዲስ አበባ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ።
- ፲፰፻፹፩ ዓ/ም - የጀርመን የናዚ ፖለቲካ ቡድን መሥራችና መሪ የነበረው አዶልፍ ሂትለር በዚህ ዕለት ተወለደ።
- ፲፱፻፲፰ ዓ/ም - የታላቋ ብሪታኒያ ንግሥት ዳግማዊት ኤልሳቤጥ በሎንዶን ተወለዱ።
- ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ጃማይካን ለመጎብኘት ኪንግስተን ሲገቡ ከመቶ ሺ የማያንሱ ሰዎች የደመቀ አቀባበል አደረጉላቸው። ይሄን ዕለት የ’ራስ ተፈሪያን’ ተከታዮች በየዓመቱ የዚያን የጉብኝት ማስታወሻ አድርገው ያከብሩታል።
- ፲፱፻፹፩ ዓ/ም - መቶ ሺ ተማሪዎች በቤይጂንግ ከተማ ‘ቲያናንመን’ አደባባይ ላይ የቻይናን የፖለቲካ ሥርዓት በመቃወም የሰላማዊ ሰልፍ አካሄዱ።
- ፲፱፻፳ ዓ/ም በመካከለኛው የግሪክ ግዛት ውስጥ የተከሰተው የመሬት እንቅጥቅጥ አደጋ የቆሮንጦስን ከተማ አወደመ።
- ፲፱፻፸፪ ዓ/ም - በላይቤሪያ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የጨበጠው የሃምሣ ዓለቃ ዶ ተከታዮች፣ የቀድሞውን ፕሬዚደንት የዊሊያም ቶልበርትን ታላቅ ወንድም ጨምሮ ብዙ የቀድሞ ባለሥልጣናትንና ሚኒስቴሮች ረሸኗቸው።
- ፳፻፫ ዓ/ም - በመላው ዓለም የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች በዛሬው ዕለት የኢየሱስ ክርስቶስን ስቅለተ ዓርብ በማስታወስ ይዘክራሉ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት በአብዮቱ ፍንዳታ እይተካሄዱ ያሉትን አድማዎችና ሰላማዊ ሰልፎችን ለመግታት የሚወስዳቸውን እርምጃዎች አስታወቀ። የፖስታ ሠራተኞች የአራት ቀን አድማቸውን ጀመሩ።
- ፲፱፻፹፪ ዓ/ም - ናሚቢያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት መቶ ስልሳኛ አባል ሆነች።
- ፲፱፻፺፱ ዓ/ም - የሩሲያ ኅብረት መንግሥት (Russian Federation) የመጀመሪያው ፕሬዚደንት የነበሩት ቦሪስ የልስቲን በተወለዱ በሰባ ስድስት ዓመታቸው አረፉ
- ፲፱፻፷፭ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዶክቶር ምናሴ ኃይሌ በሀገራቸውና በጎረቤት አገር ሶማሊያ ጋር ያለውን ጸብ በሰላም ለመፍታት ተልከው ሞቃዲሹ ገቡ።
- ፳፻፫ ዓ/ም - በመላው ዓለም የክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች የእምነታቸው ዋና ምሠሶ የሆነውን የኢየሱስ ክርስቶስን ከሙታን መነሳት መታሰቢያ - የትንሳዔ በዓል አከበሩ።
- ፲፱፻፯ ዓ/ም - በመጀመሪያው የዓለም ጦርነት የአውስትራልያ፤ ብሪታኒያ፤ ፈረንሳይና የኒው ዚላንድ ሠራዊት በጋሊፖሊ በኩል ቱርክን ወረሩ።
- ፲፱፻፲፯ ዓ/ም - በአዲስ አበባ አዲሱ የተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት ተመርቆ ተከፈተ።
- ፲፱፻፹፯ ዓ/ም - በአሜሪካ የኦክላሆማ ከተማ ውስጥ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ላይ የተለቀቀ፣ በፈንጂ የተሞላ ተሽከርካሪ ሲፈነዳ በጥቂቱ ሰማንያ ሰዎች ሞተዋል። ከመቶ የማያንሱ ሰዎችም የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።
- ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - በምሥራቅ አፍሪቃ የሚገኙት ታንጋኒካ እና የዛንዚባር ደሴት ተዋሕደው አንድ አገር መሠረቱ። ይሄም የተዋሕዶ አገር ከሁለቱም ስም በተውጣጣው አዲሱ ስም ታንዛኒያ ተብሎ ተሰየመ።
- ፲፱፻፶፰ ዓ/ም - የኡዝቤኪስታን ርዕሰ ከተማ ታሽኬንት በትልቅ የመሬት እንቅጥቅጥ ክስተት ስትወድም ሰብ ስምንት ሺ መኖሪያ ቤቶች በመጥፋታቸው ከሦስት መቶ ሺ በላይ የሚሆኑ ነዋሪዎቿ መኖሪያ ቢስ ሆነዋል።
- ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በሶቪዬት ሕብረት ውስጥ የቸርኖቢል የኑክሊዬር መብራት ኃይል ማምረቻ ክፉ አደጋ ተከሰተ። የዚህን አደጋ ክስተት የስካንዲናቪያ አገሮች ይፋ እስካደረጉት ድረስ የሶቪዬት ሕብረት ባለ ሥልጣናት ደፋፍነውት ነበር።
- ፲፱፻፶፯ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የካቶሊክ ዕምነት ተከታዮች ሃይማኖታዊ በዓላትን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር መሠረት ለማክበር መወሰናቸው ተገለጠ።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በእስፓኝ የሁለት ቀን ጉብኝታቸውን ጀመሩ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በብሪታኒያ በሚገኘው የሊቢያ ቋሚ ልዑካን መሥሪያ ቤት ደጅ ላይ አንዲት እንግላዚዊት የፖሊስ ባልደረባ በመገደሏ ምክንያት የብሪታኒያ መንግሥት ከሊቢያ ጋር የዲፕሎማቲክ ግንኙነቱን ከማቋረጡም ባሻገር፣ በዛሬው ዕለት የሊቢያን ልዑካን ካገር አስወጡ።
- ፲፱፻፹፮ ዓ/ም - በደቡብ አፍሪቃ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቁር ዜጎችን አሳትፎ በተካሄደው ምርጫ ኔልሰን ማንዴላ ፕሬዚደንት ሆነው ተመረጡ
- ፲፱፻፲፮ ዓ/ም - የዛምቢያ የመጀመሪያ ፕሬዚደንት የነበሩት ኬኔዝ ካውንዳ ተወለዱ።
- ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - የኢጣልያ የፋሺስት መሪ የነበረው ቤኒቶ ሙሶሊኒ ከነውሽማው ክላራ ፔታቺ ጋር በቀበሌ ታጣቂዎች ተይዞ በኮሎኔል ካሌሪዶ ከተረሸነ በኋላ አደባባይ ላይ ቁልቁል ተሰቀለ።
- ፲፱፻፶፱ ዓ/ም - ጥቁር አሜሪካዊው ቡጢኛ ሙሐመድ አሊ ወደአገሪቱ ጦር ሠራዊት ገብቶ በቪየትናምጦርነት ላይ የማገልገል ግዴታውን እንዲወጣ ቢጠየቅም አሻፈረኝ አለ። የዚያኑ ዕለት የዓለም ቻምፒዮናነቱን ማዕረግ በኒው ዮርክ የአትሌቲክ ባለ ሥልጣን ተገፈፈ።
- ፲፱፻፷፩ ዓ/ም - በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጊዜ የአገራቸውን አርበኞች የመሩትና ከነጻነት በኋላም የፈረንሳይ ፕሬዚደንት ሆነው ለ አሥራ አንድ ዓመታት ያገለገሉት ሻርል ደጎል በፈቃድቸው ሥልጣናቸውን ለቀቁ።
- ፲፱፻፸፰ ዓ/ም - በስዊድን፤ ፊንላንድ እና ኖርዌይ የሚገኙ የኑክሊዬር ምርመራ ማዕከላት ያልተለመደ የጨረር ጉዳት በከላ በምድር ጠፈር ላይ እንዳገኙ ባስታወቁ በሁለተኛው ቀን የሶቪዬት ኅብረት ባለ ሥልጣናት ቸርኖቢል የሚባለው የኑክሊዬር የመብራት ኃይል ማምረቻ አደጋ እንደደረሰበት ይፋ አደረጉ።
- ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - አዶልፍ ሂትለር እና የብዙ ዘመን ውሽማው ኤቫ ብሮን በበርሊን ምሽግ ውስጥ ተጋቡ። ሂትለር አድሚራል ካርል ዶኒትዝን የሥልጣን ተተኪው እንደሆነ አስታወቀ።
- ፲፱፻፹፫ ዓ/ም - ‘ቺታጎንግ’ በተባለ የደቡብ-ምሥራቅ የባንግላዴሽ ግዛት ላይ የተነሳ አውሎ-ነፋስ መቶ ሰላሳ ስምንት ሺ ሰዎችን ሲገድል እስከ አሥር ሚሊዮን የሚጠጉ ዜጎች የመኖሪያ ቤታቸው ወድሞባቸዋል።
- ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በጄኔራል መንግሥቱ ንዋይ የሚመራው የክብር ዘበኛ ሠራዊት በሱሉልታ አካባቢ የጦር ታክቲክ ልምምድ አካሄደ። ይሄንን ልምምድ ብዙዎች የታኅሣሥ ግርግር ዝግጅት እና ትልቅ የማስጠንቀቂያ ደውል መሆኑን ይገምታሉ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ እንቅስቃሴ የ፪ተኛ ክፍለ ጦር ሰራዊት የአስመራ ከተማን በቁጥጥሩ ስር አዋለ። የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የፖስታ እና ቴሌኮሙኒኬሽን ሚኒስትሩ ሌተና ጄኔራል አሰፋ አየነ በአብዮታዊ ወታደሮች በዚህ ዕለት እስር ላይ ሲውሉ፤ የመከላከያ ሚኒስቴር ደግሞ የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማኅበርን ሕገ-ወጥ አድማ ማካሄዱን ካላቆመ እንደሚዘጋ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።
- ፲፯፻፺፭ ዓ/ም - የአሜሪካ ኅብረት መንግሥት የኦርሊአንስ ግዛት የተባለውን ክፍል ከፈረንሳይ ላይ በ አሥራ አምስት ሚሊዮን ዶላር ገዛ።
- ፲፱፻፷፰ ዓ/ም ፥ የኅብረተ ሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ዴሞክራሲያዊ አብዮት ፕሮግራምን አወጣ።
- ፲፱፻፵፬ ዓ/ም - ‘ደ ሀቪላንድ-ኮሜት’ የተባለው የዓለም የመጀመሪያው የተሳፋሪ ጄት አየር-ዠበብ የመጀመሪያ በረራውን ከሎንዶን እስከ ጆሃንስበርግ ድረስ አከናወነ።
በአገራችን ታሪክ ሁለት የሐዘንና የደስታ ቀኖችን ትዘክራለች። ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ/ም የፋሽሽት ኢጣልያ ጄነራል ባዶሊዮ በጊዚያዊ ድል አድራጊነት አዲስ አበባን ከቁጥጥሩ ሥር ያደረገበትና ነጻነታችንን ያጣንበት ዕለት ሲሆን ልክ በአምስት ዓመቱ በ ፲፱፻፴፫ ዓ/ም ደግሞ ንጉሠ ነገሥቱ በአርበኞች አባት እናቶቻችን ትግል፣ በእንግሊዝ እና ግብረአበሮቿ ዕርዳታ በድል አድራጊነት አዲስ አበባ የገቡበት ዕለት ነው።
- ፲፱፻፴፫ ዓ/ም ዓፄ ኃይለ ሥላሴ በድል አድራጊነት መናገሻ ከተማችን አዲስ አበባ ገቡ።
- ፲፱፻፴፰ ዓ/ም - የጄኔራል ዊንጌት ፪ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትየፋሺስት ኢጣልያ የራዲዮ ጣቢያ በነበሩ በተበታተኑ አሮጌ ቤቶች ውስጥ፣ ከመላው አገሪቱ ጠቅላይ ግዛቶች ለመጡ ፳፰ የመጀመሪያ ተማሪዎች የትምህርት አገልግሎት መስጠቱን ጀመረ።
- ፲፱፻፶፮ ዓ/ም የአውሮፓ ሸንጎ (The Council of Europe) ይሄንን ዕለት “የአውሮፓ ቀን” ብሎ ሰይሞታል
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በብሔራዊ የድል በዐል ላይ ባደረጉት ንግግር፣ በአገሪቱ የተለኮሰውን የአብዮት እሳት በተመለከተ ከውጭ የሚራገብ ነቀርሳ እንደሆነና ኢትዮጵያውያን በሙሉ በሕብረት እንዲቃወሙት ጥሪያቸውን አሰሙ።
- ፲፱፻፷፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፳፭ኛ የልደት በዐሉን አከበረ።
- ፲፰፻፸፬ ዓ/ም - እምባቦ በሚባል ሥፍራ የሸዋው ንጉሥ ምኒልክ ሠራዊት እና የጎጃም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ውጊያ ገጥሞ ድሉ የንጉሥ ምኒልክ ሲሆን፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ተማረኩ።
- ፲፱፻፳፭ ዓ/ም - የሕንድ አባት በሚል ቅጽል ስም የሚታወቀው ሞሃንድራስ ካራምቻንድ ጋንዲበአገሩ ላይ የእንግሊዝን ቅኝ አስተዳደር በመቃወም የሃያ አንድ ቀን የ'ረሀብ አድማ' ጀመረ።
- ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - በአውሮፓ የሁለተኛው የዓለም ጦርነትን ማክተም ምክንያት በማድረግ 'ሴቲፍ' በተባለች የአልጄሪያ ከተማ በተካሄደ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፻፫ አውሮፓውያን በመሞታቸው፣ የገዢው የፈረንሳይ መንግሥት ፖሊሶች እና ወታደሮች ባካሄዱት ጨካኝ በቀላ እስከ ስድስት ሺ አልጄሪያውያን ተጨፍጭፈዋል። የዚህ አረመኔያዊ ድርጊት ሳቢያ በመላው የሰሜን አፍሪቃ የፈረንሳይን ቅኝ ገዢነት ማክተሚያ አብሳሪ እንደሆነ ታሪካውያን ይዘግባሉ።
...
| ጅምር! (ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። እርስዎ ሊያስፋፉት ይችላሉ!) |
[ለማስተካከል] ነሐሴ
፲፱፻፫ ዓ/ም አንድ ሚሊዮንኛው የአዕምሯዊ ንብረት (patent) በዩናይትድ ስቴትስ የአዕምሯዊ ንብረት ጽ/ቤት ተመዘገበ። ይኼም የፍራንሲስ ሆልተን ውስጣዊ ቱቦ አልባ ጎማ ነው።
፲፱፻፷፮ ዓ/ም የአሜሪካ ፕሬዚደንት ሪቻርድ ኒክሰን የ“ወተርጌት ቅሌት” (watergate scandal) ተብሎ በሚታወቀው ጉዳይ ምክንያት የፕሬዚደንት ስልጣናቸውን በማግሥቱ እንደሚለቁ ይፋ አደረጉ።
፲፱፻፹፪ ዓ/ም ኢራቅ ጎረቤቷን ኩዌትን በመውረር የኢራቅ አካል አደርገች። ይኼም ድርጊት የመጀመሪያውን የባህረ ሰላጤ ጦርነት የጫረው ድርጊት ነው ፲፩፻፷፭ ዓ/ም - ሁለት ምዕተ ዓመት የፈጀው የፒሳ ግንብ ሥራ ተጀመረ።
፲፱፻፳፰ ዓ/ም -ጄሲ ኦዌን የተባለው ጥቁር አሜሪካዊ በበርሊን የናዚ ጀርመን ከተማ በሚካሄደው አሥራ አንደኛው ኦሊምፒክ ውድድር ላይ አራተኛ የወርቅ ኒሻን አሸነፈ።
፲፱፻፴፯ ዓ/ም -ናጋሳኪ የተባለችው የጃፓን ከተማ ላይ የአሜሪካ የቦንብ አውሮፕላን የጫነውን አቶሚክ ቦንብ ሲጥል ሰላሳ ዘጠኝ ሺህ ሰዎች ወዲያው ሲሞቱ ከተማዋ ወድማለች።
፱፻፷፮ ዓ/ም - የአሜሪካ ፕሬዚደንት ሪቻርድ ኒክሰን የወተርጌት ቅሌት በተሰኘው ጉዳይ ምክንያት ስልጣናቸውን ሲለቁ፣ ምክትል ፕሬዚደንቱ ጄራልድ ፎርድሥልጣኑን ተረክበው ፴፰ኛው ፕሬዚደንት ሆኑ። ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ነሐሴ 3
- ፲፭፻፲፩ ዓ/ም ፈርዲናንድ ማጄላን ከአምስት የእስፓኝ መርከቦች ጋር ዓለምን በባሕር ለመዞር ሴቪል ከሚባል ሥፍራ ጉዟቸውን ጀመሩ። ማጄላን በመሃል ላይ ፊሊፒን ደሴቶች ላይ ሲሞት ጉዞውን ምክትሉ ሴባስቲያን እልካኖ ጨረሰ።
- ፲፪፻፷፪ ዓ/ም ዓፄ ይኩኖ አምላክ የዛግዌ ሥርወ መንግስትን ተክተው ነገሡ።
- ፲፱፻፵፬ ዓ/ም - በዮርዳኖስ ሐሺሚ ንጉዛት ንጉሡ ታላል በአዕምሮ ሕመምተኛነት ምክንያት በአገሪቱ ምክር ቤት ሸንጎ “ለሥልጣን ብቃት የላቸውም" ተብለው ሲሻሩ ገና አሥራ ስምንት ዓመት ያልሞላቸው ልጃቸው አልጋወራሹ በንጉሥነት እንደተኳቸው ይፋ ተደረገ። ንጉሥ ሁሴን የልደታቸው ዕለት ኅዳር ፯ ቀን ፲፱፻፵፮ ዓ/ም የንግሥ ስርዓታቸው ተከናወነ።
- ፲፱፻፺፩ ዓ/ም - በአውሮፓ እና በእስያ አኅጉራት እስከ ፫፻፶ ሚሊዮን የሚቆጠሩ በአውሮፓውያን አቆጣጠር የምዕተ ዓመቱን የመጨረሻ ድፍን የፀሐይ ግርዶሽ ተመልክተዋል።
ነሐሴ ፮ የዓለም ዓቀፍ የግራኞች ቀን በመባል ከዓለም ጠቅላላ ሕዝብ ቁጥር ከሰባት እስከ አስር በመቶ ይሆናሉ ተብለው የሚገመቱት ግራኞች የሚገጥሟቸውን ዕለታዊ ችግሮችን ለማስታወስ በ፲፱፻፷፰ ዓ/ም ተጀምሮ በየዓመቱ ይከበራል።
- ፲፰፻፹ ዓ/ም - የመጀመሪያውን መስታዮተ-ትርዒት(television) የፈጠረው የስኮትላንድ ተወላጅ ጆን ሎጊ ቤርድ ተወለደ።
- ፲፱፻፪ ዓ/ም - በክራይሚያ ጦርነት “የኩራዟ ዕመቤት” በሚል ቅጽል ስም የታወቀችው እንግሊዛዊቷ የመጀመሪያ ዘመናዊት አስታማሚ ፍሎሬንስ ናይቲንጌይል አረፈች።
- ፲፱፻፶፪ ዓ/ም -የመካከለኛው አፍሪቃ ሪፑብሊክ ከፈረንሳይ ነጻነቷን ተቀዳጀች።
- ፲፱፻፮ ዓ/ም - የአትላንቲክ ውቅያኖስንና ሰላማዊ ውቅያኖስ ለማገናኘት የተቆፈረው የፓናማ ቦይ ሥራው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ።
- ፲፱፻፴፯ ዓ/ም - ጃፓን በቃል ኪዳን አገሮች ተሸንፋ እጇን ስትሰጥ የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ሆነ። በዚህ ዕለት ኮሪያም ነጻ ወጣች።
- ፲፱፻፴፱ ዓ/ም - ለ፫ መቶ ፴፬ ዓመታት በብሪታኒያንጉዛት ሥር በቅኝ ግዛትነት የኖረችው ሕንድ በዚህ ዕለት ነጻነቷን ተቀዳጀች። እስላማዊው የሰሜን-ምዕራብ አካልም በዚሁ ዕለት ተገንጥሎ ፓኪስታን በሚል ስም አዲስ አገር ተፈጠረ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮት የሥልጣን ሽግግር፤ ደርግ የንጉሠ ነገሥቱን መንግሥት የጡረታ ሚኒስቴር በቁጥጥሩ ሥር አደረገ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር ደርግ የንጉሠ ነገሥቱን ችሎት እና የዘውድ ምክር ቤት በመሻር ሕገ-ወጥ ከማድረጉም ባሻገር በዚሁ ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ታጣቂ ወታደሮችን እና ታንክ ጭምር በማሠማራት የመሣሪያ ኃይሉን አሳየ። በተያያዘ ሁኔታ ኤርትራውያንን የሚወክሉ የፓርላማ አባላት ሥራቸውን እንደሚለቁ አስታወቁ።
- ፲፱፻፺፭ ዓ/ም - የኡጋንዳ አምባ-ገነን ፕሬዚደንት የነበረው ኢዲ አሚን በስደት በሚኖርበት ሳዑዲ አረቢያ ላይ በተወለደ በ፸፰ ዓመቱ አረፈ።
- ፲፰፻፶ ዓ/ም - በብሪታኒያ ንጉዛት እና በአሜሪካ ኅብረት መኻል በአትላንቲክ ውቅያኖስ ውስጥ የተዘረጋውን አዲሱን የቴሌግራፍ መስመር በመመረቅ ንግሥት ቪክቶሪያ እና የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጄምስ ቡካነን የሰላምታ መልእክት ተለዋወጡ።
- ፲፱፻፴፬ ዓ/ም - የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ልጅ ልዕልት ፀሐይ በዚህ ዕለት አረፉ።
- ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - በኢትዮጵያ የብሪታኒያ ዋና መላክተኛ (Ambassador) ዳግላስ ራይት (Douglas A. H. Wright) በኢትዮጵያ እና በኬንያ መኻል ያለውን ድንበር ለመስማማት የተዘጋጀውን የውል ረቂቅ ለኢትዮጵያ መንግሥት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አክሊሉ ሀብተ-ወልድ አስረከበ።
- ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያ አብዮታዊ ሽግግር የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የክብር ዘበኛ ሠራዊት አዛዥ የነበሩት ማዮር ጄነራል ታፈሰ ለማ በደርግ ተይዘው ታሠሩ። በዚሁ ዕለት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የነብሩት አቡነ ቴዎፍሎስ አዲስ በተዘጋጀው ረቂቅ ሕገ-መንግሥት ውስጥ በተካተቱ አንዳንድ አንቀጾች ላይ ቅዋሜ እንዳላቸው አስታወቁ።
- ፲፰፻፴፮ ዓ/ም - ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ላይ ተወለዱ።
- ፲፱፻፱ ዓ/ም - በግሪክ ሁለተኛ ከተማ በተሰሎንቄ (Thessaloniki) የተከሰተ የእሳት አደጋ የከተማዋን ቤቶች በቁጥር ከሦስት እጅ አንድ በማውደሙ እስከ ፸ሺ ነዋሪዎችን ውጭ አዳሪ ቤት አልባ አድርጓቸዋል።
- ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ኮሚቴ(International Olympic Committee - IOC) ዘረኛውን የደቡብ አፍሪቃ መንግሥት ‘አፓርታይድ’ በሚል መርሆ የሚያካሂደውን የግፍ አስተዳደር እንዲያወግዝ ያቀረበለትን ጥሪ ባለመቀበሉ በዚህ ዓመት ቶክዮ ከተማ ላይ በተዘጋጀው ፲፰ኛው የኦሊምፒክ ውድድር ላይ እንዳይሳተፍ አገደው።
- ፲፱፻፸፱ ዓ/ም - ረቡዕ ዕለት፣ ታላቁ የስፖርት ሰው፣ የኦሊምፒኩ አውራ ይድነቃቸው ተሰማ ያረፉበት ቀን ነው።
- ፲፱፻፹፱ ዓ/ም - በደብረ ዳሞ ገዳም ብዙ ታሪካዊ ፤ ሃይማኖታዊ እና ምሥጢራዊ የመጽሐፍ ቅርሶችን ያካተተው ቤተ መጻሕፍትና ሃይማኖታዊ 'ንዋየ ቅድሳት' የተከተቱበት ግምጃ ቤት ባልታወቀ ምክንያት በእሳት አደጋ ቃጠሎ ወደሙ
ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ነሐሴ 14 ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ነሐሴ 15 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች በዛሬው ዕለት በየዓመቱ ነሐሴ ፩ ቀን የሚጀመረውን ጾመ ፍልሰታ የሚፈቱበት ቀን ነው።
- ፲፰፻፶፮ ዓ/ም - በጦርነት የተማረኩ ሰዎችን መብት ስለማስጠበቅና ስለማክበር የተዘጋጀው የጋራ ድንጋጌ (የጀኒቫ ኮንቬንሽን) በአሥራ ሁለት መሥራች አገሮች ተፈረመ። የቀይ መስቀል ማኅበርም አብሮ ተመሠረተ።
- ፲፰፻፺፮ ዓ/ም - በ፺፫ ዓመታቸው እስከሞቱ ድረስ ለ፳፯ ዓመታት ቻይናን የመሩት ዶንግ ዢያው ፒንግ ተወለዱ።
- ፲፱፻፷፬ ዓ/ም - የዓለም አቀፍ ኦሊምፒክ ሸንጎ (International Olympic Committee) ሮዴዚያን (አሁን ዚምባብዌ) በዘረኛነቷ ምክንያት አባልነቷን ሠረዘ።
ነሐሴ 17 ቀን: ነጻነት ቀን በሮማንያ፤ ኡምህላንጋ (የሸምበቆ) በዓል በስዋዚላንድ...
- 1931 - ሂትለርና ስታሊን በሥውር ፊርማ ፖሎኝን አካፈሉ።
- 1954 - መጀመርያ ቴሌቪዥን ግንኙነት በአሜሪካና በአውሮጳ መካከል
- 1958 - መጀመርያ የምድር ፎቶ በጨረቃ ምኋር ካለ ሰው ሰራሽ መንኮራኩር ተነሣ።
ነሐሴ 19 ቀን: ብሔራዊ በዓል በዩሩጓይና በፊልፒንስ...
- 1791 - ስልጣን ለመያዝ ናፖሌዎን ከግብፅ ወደ ፈረንሳይ ወጣ።
- 1806 - የእንግሊዝ ጭፍሮች በጦርነት ዋሺንግቶን ዲሲ ገብተው ዋይት ሃውስን አቃጠሉ።
- 1850 - በሪችሞንድ ቪርጂኒያ 90 ጥቁሮች ትምህርት ስለተማሩ ታሰሩ።
- 1912 - ፖሎኝ በዋርሳው ውጊያ በሩሲያ ቀይ ጭፍሮች ላይ ያሸነፋል።
- 1936 - ፓሪስ ከተማ በጓደኞች አርበኞች ከጀርመን ነጻ ወጣች።
- 1981 - ቮየጀር የተባለ ሰው ሰራሽ መንኮራኩር በኔፕቱን ፈልክ አለፈ።
ነሐሴ 20 ቀን: ዓመት በአል በናሚቢያ፤ የሱልጣን ልደት በዓል በዛንዚባር...
- 1822 - ቤልጅክ በኔዘርላንድ ላይ አመጸ።
- 1912 - ሴቶች በአሜሪካ ዩናይትድ እስቴት የምርጫ መብት አገኙ።
- 1978 - በመርዝ ጋዝ አደጋ በካሜሩን 1700 ሰዎች ሞቱ።
- 1989 - በእስላም ታጣቂዎች በአልጄሪያ በተገረገ እልቂት 60-100 ሰዎች ተገደሉ።
- 1994 - የምድር ጉባኤ ስብሰባ በጆሃነስበርግ ደቡብ አፍሪቃ ጀመረ።
- 1564 - ካቶሊኮች በፈረንሳይ ፕሮቴስታንቶች ላይ የበርተሎሜዎስ እልቂት ጀምረው መሪያቸውን ደኮልኒን ገደሉ።
- 1831 - አሚስታድ የተባለ በአፍሪቃውያን የተማረከው መርከብ ወደ ኒው ዮርክ ደረሰ።
- 1875 - ክራካቶአ የተባለ እሳተ ገሞራ በእንዶኔዝያ ፈነዳ፤ 3600 ሰዎች ሞቱ።
- 1892 - የእንግሊዝ ሃያላት በአፍሪካነር (ቦር) ጦርነት (ደቡብ አፍሪቃ) በበርገንዳል ውጊያ አሸነፉ።
- 1920 - ጦርነት የሚከላከል የኬሎግ-ብሪያንድ ውል በ60 አገሮች ተፈረመ።
ነሐሴ 22 ቀን: ነጻነት በዓል በሆንግኮንግ...
- 1601 - ጋሊሌኦ ስለመጀመርያ ቴሌስኮፕ ለቬኒስ አማካሪዎች መግለጫ ሰጠ።
- 1805 - ናፖሌዎን በድረስደን ውጊያ ድል አደረገ።
- 1888 - ከዓለሙ ታሪክ አጭሩ ጦርነት - 38 ደቂቃ - የእንግሊዝ-ዛንዚባር ጦርነት።
- 1955 - ዶ/ር ማርቲን ሉጠር ኪንግ «እኔ ሕልም አለኝ» ያለበትን ቃል ለሰላማዊ ሰልፍ ተናገረ።
- 1982 - ሳዳም ሁሰይን ኩወይት የኢራቅ ክፍላገር ነው ይላል።
- 1768 - የእንግሊዝ ሠራዊት በጆርጅ ዋሽንግተን ላይ በሎንግ አይላንድ ውጊያ አሸነፉ።
- 1822 - መጀመርያ የምድር ባቡር አገልግሎት "ዘ ቶም ሳምብ" በዩናይትድ ስቴትስ ጀመረ።
- 1871 - በደቡብ አፍሪቃ መጨረሻ የሆኑት የዙሉ ንጉሥ ከትሿዮ በእንግሊዞች ተማረከ።
- 1941 - የሶቭየት ኅብረት መጀመርያውን ንዩክሌያር መሣሪያ በፈተና አፈነዳ።
- 1987 - ናቶ በቦስኒያ ሰርቦች ላይ ዘመቻ ጀመረ።
ነሐሴ 24 ቀን: የድል ቀን በቱርክ (የ 1922 ዱምሉፒናር ድል ለማስታወስ)፤ የቅዱስ ሮዛ በዓል በፔሩ...
- 1934 - የአላም አል ሓልፋ ውጊያ በጀርመንና እንግሊዝ ታንኮች መኃል በግብፅ በረሃ ጀመረ።
- 1959 - ጡርጉድ ማርሻል መጀመርያ አፍሪቃ-አሜሪካዊ የዋና ብሔራዊ ችሎት ፈራጅ ተሾሙ።
ነሐሴ 25 ቀን: የነጻነት በዓል በማለይዝያ፤ ትሪኒዳድ፤ ኪርግዝስታን...
- 1557 - በዩናይትድ እስቴት ከሁሉ አስቀድሞ በአውሮጳውያን የተሰራ ከተማ ሰይንት ኦገስቲን ፍሎሪዳ ተመሰረተ።
- 1792 - ጌብሪየል ፕሮሰር የባርዮችን ብጥብጥ በሪችሞንድ ቪርጂንያ አሸፈተ።
- 1805 - ክሪክ የተባለው የቀይ ኢንዲያን ጐሣ ወታደሮች በፎርት ሚምስ ምሽግ አላባማ ላይ እልቂት አደረጉ።
- 1854 - በአሜሪካ መነጣጠል ጦርነት ደቡብ ክፍላገሮች (ኮንፌዴራቶች) በ2ኛ መናሠሥ ውጊያ አሸነፉ።
- 1984 - ፓስካል ሊሱባ በኮንጎ ሪፑብሊክ ምርጫ ፕሬዚዳን ሆኑ፤ ይህ ምርጫ የረጅም ዘመን አንድ ፓርቲ ግዛት ጨረሰ።
- 1990 - ስሜን ኮሪያ የራሱን ሰው ሠራሽ መንኮራኩር መጀመርያ ጊዜ ላከ።
ነሐሴ 26 ቀን: የሕገመንግስት ቀን በስሎቫኪያ...
- 1878 - ከምድር መንቀጥቀጥ በሳውስ ካሮላይና 100 ሰዎች ሞቱ።
- 1915 - ታላቅ ምድር መንቀጥቀጥ በጃፓን መቶ ሺህ የሚያህሉ ሰዎች ገደለ።
- 1931 - አዶልፍ ሂትለር ፖሎኝን በመውረሩ ሁለተኛ ዓለማዊ ጦርነት ጀመረ።
- 1961 - መንፈቅለ መንግስት በሊቢያ ሙአማር ጋዳፊን ከፍ አደረገው።
- 1975 - የኮሪያ አየር መንገድ አይሮፕላን በሶቭየት ኅብረት ላይ ሲተኮስ 269 መንገደኞች ሞቱ።
- 1983 - ዑዝበክስታን ነጻነቱን ከሶቭየት ኅብረት አዋጀ።
- 1862 - የፕሩሲያ (ጀርመን) ሠራዊት 3ኛ ናፖሊዎንን ከ100,000 ጭፍሮች ጋር በሰዳን ውግያ አሸነፈ።
- 1890 - በኦምዱርማን ውግያ ሱዳን የእንግሊዝ ሠራዊት ድል በማድረግ ቅኝ አገር አደረጉት።
- 1935 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት ኢጣልያ በጓደኞቹ ሃያላት ተወረረች።
- 1946 - የቻይና ሃያላት የደቡብ ኮርያ ደሴቶችን በቦምብ ደበደቡ።
ነሐሴ 29 ቀን: የአባቶች ቀን በአውስትራሊያ፣ ኒው ዚላንድ...
- 1784 - በፈረንሳይ አብዮት ከ200 በላይ ቄሳውንት ሰማዕትነት አገኙ።
- 1830 - በሜሪላንድ ፍረድሪክ ዳግላስ መርከበኛ በማስመስል ከባርነት አመለጠ።
- 1949 - የአርካንሳው አገረ ገዥ ኦርቪል ፋውበስ ጥቁር ትማሮች ከነጭ ጋራ እንዳይማሩ የክፍላገሩን ወታደሮች በሊተል ሮክ ሰበሰበ።
ነሐሴ 30 ቀን: አስተማሮች ቀን በሕንደኬ (የራዳክሪሽናን ልደት)...
- 402 - ሮማ በቪዚጎቶች ተዘረፈች።
- 1641 - በኢጣልያ ካስትሮ የሚባል ከተማ በሮማ ፓፓ ላይ አመጽ አድርጎ፡ የፓፓ ሃያላት አጠፉት።
- 1658 - በለንደን እንግሊዝ 10 ሺህ ሕንጻዎች ያጠፋ ታላቅ እሳት ጀመረ።
- 1775 - የአሜሪካ ነጻነት አብዮት ከእንግሊዝ በፓሪስ ውል ተጨረሰ።
- 1790 - የአንድ ሳምንት ባሕር ውግያ በእንግሊዝና በእስፓንያ መካከል ከቤሊዝ አጠገብ ጀመረ።
- 1878 - ከ30 አመት ትግል በኋላ፣ የአፓቺ አለቃ ጀሮኒሞ በአሪዞና እጅን ሰጠ።
ጳጉሜ 2 ቀን: ነጻነት ቀን በብራዚል፣ የድል ቀን በሞዛምቢክ...
- 1785 - የፈረንሳይ አብዮታዊ አማካሪዎች "የማስፈራራት መንግስት" ዐዋጁ።
- 1932 - ጀርመኖች በ2ኛ ዓለማዊ ጦርነት ለንደንን በቦምብ ለመደብደብ ጀመሩ።
- 1969 - የአሜሪካ ፕሬዚዳን ጂሚ ካርተር የፓናማ ካናል አስተዳደር ለፓናማ በ1992 ለማዛወር ውል ፈረሙ።
- 1978 - ዴስሞንድ ቱቱ በኤጲስቆፖሳዊ ቤተክርስቲያን በደቡብ አፍሪካ መጀመርያ ጥቁር ኤጲስ ቆጶስ ሆኑ።
- 1988 - የራፕ ሙዚቃ ተጫዋች ቱፓክ ሻኩር በላስ ቬጋስ ተተኲሶ ተገደለ።
- 71 - ደብረ ቬሱቪዩስ እሳተ ገሞራ በኢጣልያ 3 ከተሞችን አጠፋ።
- 1690 - ፃር 1 ፕዮትር በሩሲያ የጺም ቀረጥ አስገበረ።
- 1804 - ናፖሊዎን በሩሲያ ላይ በቦሮዲኖ ውግያ ድል አደረገ።
- 1814 - ብራዚል ነጻነቱን ከፖርቱጋል አዋጀ።
- 1892 - አንድ ታላቅ አውሎ ንፋስ በቴክሳስ 8000 ሰዎች አጠፋ።
- 1935 - የአሜሪካ ጄኔራል አይዘንሃወር የኢጣልያ እጅ መስጠት በጦርነት አዋጀ።
ጳጉሜ 4 ቀን: ሬፑብሊክ ቀን በስሜን ኮርያ፣ ነጻነት ቀን በታጂኪስታን፣ ብሄራዊ ቀን በቡልጋርያ...
- 467 - የጀርመን አለቃ ኦረስቴስ የሮማ ነጉስን አባርሮ መጨረሻውን ንጉስ ሮሙሉስ አውግስጦስን ሾመ።
- 1514 - ቪክቶሪያ የምትባል መርከብ ወደ ስፓንያ በመመለሷ መጀመርያ ዓለምን የከበበችው መርከብ ሆነች።
- 1914 - ቱርኮች በግሪክ-ቱርክ ጦርነት አሸንፈው ስሚርና ከተማ ተቃጠለ።
- 1963 - በአቲካ እስር ቤት ኒው ዮርክ ሁከት ተደረገ።
- 1252 - እጣልያ የንጉስ ወገን በፓፓ ወገን በሞንታፔርቲ ድል አደረገ።
- 1831 - ጆን ኸርሸል መጀመርያ ፎቶ አነሳ።
- 1911 - በሳንዠርመን ውል ዩጎስላቪያ፣ ሃንጋሪና ቸኮስሎቫኪያ ከኦስትሪያ ነጻነታቸውን አገኙ።
- 1934 - በ2ኛ አለማዊ ጦርነት የጓደኞች ሃያላት በማጁንጋ ማዳጋስካር ደረሱ።
- 1966 - ጊኔ-ቢሳው ነጻነቱን ከፖርቱጋል አገኘ።
- 1994 - ገለልተኛ አገር የሆነ ስዊስ በመጨረሻ የተባበሩት መንግስታት አባል ሆነ።
ጳጉሜ 6 ቀን
- 1731 - በቻርልስተን ሳውስ ካሮላይና አካባቢ ስቶኖ የባርዮች አመጽ ሆነ።
- 1979 - የሬጌ ሙዚቃ ዘፋኝ ፒተር ቶሽ ቤቱ በኪንግስተን ጃማይካ በሌቦች ተገደለ።


