ጥር ፲
ከውክፔዲያ
ጥር ፲ ቀን፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፻፴ ኛው ዕለት ሲሆን ፲፭ ኛው የበጋ ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በዘመነ ዮሐንስ ፪፻፴፮ ዕለታት ሲቀሩ፤ በዘመነ ማቴዎስ፤ ማርቆስ እና ሉቃስ ደግሞ ፪፻፴፭ ዕለታት ይቀራሉ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች በዚህ፣ የትልቁ የጥምቀት በዓል ሥነ ሥርዓት መጀመሪያ ዕለት የአጥቢያቸውን ታቦተ ሕግ በማጀብ ወደከተራው ተጉዘው እዚያው ያድራሉ።
ማውጫ |
[ለማስተካከል] ታሪካዊ ማስታወሻዎች
- ፲፱፻፹፭ ዓ/ም በ አምሳዎቹም የአሜሪካ ሕብረት ግዛቶች አሁን በየዓመቱ በልደቱ አካባቢ የሚከበረው የጥቁር አሜሪካዊው መሪ የማርቲን ሉተር ኪንግ ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ ተከበረ።
- ፲፱፻፺፯ ዓ/ም እስከ ፭ መቶ ፳፭ መንገዶኞችን የሚያስተናግደው፣ ወደረ ቢሱ ኤየርባስ ኤ፫፻፹ (Airbus A380) የተሰኘው አየር ዠበብ በቱሉስ የፈረንሳይ ከተማ ለዓለም ተገለጸ።
- ፲፱፻፺፱ ዓ/ም በምዕራብ አውሮፓ አገሮች የተነሳ ኃይለኛ አውሎ ንፋስ፣ በብሪታኒያ አሥራ አራት፤ በአለማኝ አሥራ ሦስት ሰዎችን ሲገል በሀያ አገራት ውስጥ አርባ አራት ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል።
[ለማስተካከል] ልደት
[ለማስተካከል] ዕለተ ሞት
[ለማስተካከል] ዋቢ ምንጮች
(እንግሊዝኛ) http://en.wikipedia.org/wiki/January_18
| የኢትዮጵያ ወራት | |
|---|---|
| መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ | |