ከ«1 እሽመ-ዳጋን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
ጥ r2.7.2+) (ሎሌ መጨመር: zh:伊什麦达干 |
|||
መስመር፡ 38፦ | መስመር፡ 38፦ | ||
[[sh:Išme-Dagan I]] |
[[sh:Išme-Dagan I]] |
||
[[sv:Ishme-Dagan I]] |
[[sv:Ishme-Dagan I]] |
||
[[zh:伊什麦达干]] |
እትም በ09:59, 14 ጁን 2012
1 እሽመ-ዳጋን ከ1688 እስከ 1678 ዓክልበ. ('ኡልትራ አጭሩ' አቆጣጠር[1]) የአሦር ንጉሥ ነበረ። አባቱ 1 ሻምሺ-አዳድ የአሦር ንጉሥ እየሆነ፣ ልጁን እስመ-ዳጋንን በኤካላቱም ዙፋን ላይ አስቀምጦት ነበር። ታናሹ ወንድሙ ያስማሕ-አዳድ ደግሞ የማሪን ዙፋን ተቀበለው። በባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ 17ኛው አመት (በ1688 ዓክልበ.) 1 ሻምሺ-አዳድ እንደ ሞቱ ልጁም እሽመ-ዳጋን የአሦርን መንግሥት እንደ ወረሰው ይታወቃል።
በዘመኑ መጀመርያ፣ የሆራውያን ቱሩኩ ጎሣ አለቃ ሊዳይ ጽኑ አመጽ በሹሻራ አገር አስነሣሣ። ክፍላገሩ በተለይ ተራራማ ስለ ሆነ፣ እሽመ-ዳጋን የአሦርን ሠራዊት ሹሻራን እንዲተው አደረገ። ከዚያ ግን ኡታን አገር አሸነፈ። በተሸነፈው አገር በኡታ ሥልጣኑን ለመጠብቅ፣ ወንድሙን ያስማሕ-አዳድ ከማሪ ወደ ኡታ እንደራሴነት አዛወረው። በስደት የኖረው የማሪ ቀድሞ ንጉስ ዚምሪ-ሊም በዚያ ዕድሉን አገኝቶ ማሪን ከያስማሕ-አዳድ ነጥቆ ወደ ዙፋኑ ተመለሰ።
በእሽመ-ዳጋን ዘመን፣ አሦር ከማሪ፣ ከኤሽኑና እና ከኤላም ጋራ ጦርነት ያደርግ ነበር። ስለዚህ እሽመ-ዳጋን ከበፊቱ ጠላቶች ከቱሩኩ ሕዝብ ጋር የስምምነት ውል አደረገ። የቱሩኩ አለቃ ሴት ልጅ ለእሽመ-ዳጋን ወንድ ልጅ ለሙት-አሽኩር ታጨች። በዚህ ወቅት ደግሞ የባቢሎን ሃይል እየበረታ አሦር ከባቢሎን ወዳጅነት ተጠቀመ። ሆኖም እሽመ-ዳጋን የአባቱን ግዛት በሙሉ ሊጠብቅ አልተቻለውም። በመጨረሻ ግዛቱ የኤካላቱም፣ አሹርና ነነዌ ከተሞች ዙሪያ ብቻ ያጠቅልል ነበር።
በማሪ ጽሑፎች እንደሚዘገብ፣ በዚምሪ-ሊም 9ኛው አመት (በ1679 ዓክልበ.)፣ ኤላማውያን እሽመ-ዳጋንን ከአገሩ አባረሩትና ወደ ባቢሎን ሸሸ። በዚያ በጽናት ታመመ። እሽመ-ዳጋን ማዕረጉን በይፋ ቢጠብቅም የሃሙራቢን ሥልጣን እንዲቀብል ተገደደ። በመሞቱም አሦር በብሔራዊ ሁከት ተያዘ፤ ልጁ ሙት-አሽኩር ይቅርና ብዙ ሌሎች ሰዎች ዙፋኑን ለመያዝ ሞከሩ። ከነዚህም አሹር-ዱጉል አገሩን ለጥቂት አመት እንዲገዛ በቃ።
የአሦር ነገሥታት ዝርዝር እሽመ-ዳጋን ለ40 አመት እንደ ነገሠ ሲል፣ ባለፈው ቅርብ ጊዜ ግን (1995 ዓ.ም.) ተጨማሪ ሰነዶች በካነሽ (በዛሬው ቱርክ) በመገኘታቸው አሁን የአሦር ንጉሥ ለ11 ዓመታት ብቻ እንደ ነበር ይታወቃል።[2]
ዋቢ መጽሐፍት
- ^ http://chronosynchro.net/base.php?page=accueil (ፈረንሳይኛ)
- ^ http://chronosynchro.net/base.php?page=accueil (ፈረንሳይኛ)
- Jean-Marie Durand, Documents Epistolaires du Palais de Mari, Collection « Littérature Ancienne du Proche-Orient » N° 16. (1997); (2002) ISBN 2204056855 (ፈረንሳይኛ)
ቀዳሚው 1 ሻምሺ-አዳድ |
የአሦር ንጉሥ 1688-1678 ዓክልበ. ግድም |
ተከታይ አሹር-ዱጉል፣ ሙት-አሽኩርና 8 ሌሎች ተፎካካሪዎች |