ቀይ ተኩላ

ከውክፔዲያ
?ቀይ ተኩላ

ሳይንሳዊ ደረጃ መስጫ
ስፍን: ጉንደ እንስሳ (Animalia)
ክፍለስፍን: አምደስጌ (Chordata)
መደብ: አጥቢ (Mammalia)
ክፍለመደብ: ስጋበል
አስተኔ: የውሻ አስተኔ Canidae
ወገን: የውሻ ወገን Canis
ዝርያ: ቀይ ተኩላ C. simensis
ክሌስም ስያሜ
Canis simensis

ቀይ ተኩላ ወይም ቀይ ቀበሮ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚገኝ አጥቢ እንስሳ ነው። በዘልማድ «ቀበሮ» ይባል እንጂ የተኩላ ዘር (የውሻ ወገን) ነው። የሚኖርበትም ስፍራ ከ3000 ሜትር ከፍታ በላይ ካሉ ቦታውች ብቻ ሲሆን፣ የሚገኘውም በብዛት ባሌ ተራራና ሰሜን ተራራ ነው። ከዚህ በተረፈ በጉና ተራራ፣ በመንዝ እና በወሎ አልፎ አልፎ ይገኛል። ቁጥሩም የተመናመነ ስለሆነ ሊጠፋ የደረሰ እንስሳ ተብሎ ይታወቃል።