በጋ

ከውክፔዲያ

በጋ ፀሐይ የሚበረታበት፣ ደረቅና ሐሩር የሐጋይ ወራት ተብሎ ይታወቃል። በኢትዮጵያ ባሕረ ሐሳብ (ቁጥር ያለው ዘመን) መሠረት ከክረምት በኋላ መስከረም ፳፮ ቀን የሚጀምረው የመፀው (አበባ) ወቅት፣ ጊዜውን ታኅሣሥ ፳፭ ቀን ፈጽሞ ለበጋ ያቀብላል። በጋ የሚያበቃው መጋቢት ፳፭ ቀን ሲሆን ተረካቢው ወቅት ደግሞ ፀደይ (በልግ) ይሆናል።

የወቅት ስም የመግቢያው ቀን የማለቂያው ቀን
መፀው (አበባ) መስከረም ፳፮ ታኅሣሥ ፳፭
በጋ ታኅሣሥ ፳፮ መጋቢት ፳፭
ፀደይ (በልግ) መጋቢት ፳፮ ሰኔ ፳፭
ክረምት ሰኔ ፳፮ መስከረም ፳፭