ፀደይ

ከውክፔዲያ

ጸደይ በአማርኛው በልግ፣ የበጋን ወራት ተከትሎ መጋቢት ፳፮ ቀን ይብትና እስከ ሰኔ ፳፭ ቀን ድረስ ከቀላል ዝናብ ጋር ይዘልቃል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕግና ሥርዓት ወይም በኢትዮጵያ ባሕረ ሐሳብ (የዘመን አቆጣጠር) መሠረት አንድ ዓመት በአራት ንዑሳን ክፍሎች ይከፈላል። ከነኚህ አንዱ ክፍል ወርኀ ጸደይ ነው።


ታላቁ ኢትዮጵያዊ ሊቅ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ጸደይ የሚለውን ቃል ሲያብራሩ «ዐጨዳ፤ ያጨዳ ወራት፤ ዘመነ በልግ፤ በወዲያ መከር፣ በወዲህ በልግ የሚደርስበት የሚታጨድበት፣ ወዲያውም የሚዘራበት ወርኀ ዘርዕ። ክፍለ ዓመት፤ ያመት ርቦ ፺፩ ቀን ወይም ፫ ወር በሐጋይና በክረምት መካከል ያለ ክፍል።[1]

የወቅት ስም የመግቢያው ቀን የማለቂያው ቀን
መፀው (አበባ/መኸር) መስከረም ፳፮ ታኅሣሥ ፳፭
በጋ ታኅሣሥ ፳፮ መጋቢት ፳፭
ፀደይ (በልግ) መጋቢት ፳፮ ሰኔ ፳፭
ክረምት ሰኔ ፳፮ መስከረም ፳፭

ማጣቀሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤"መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ።" (፲፱፻፵፰ ዓ/ም); ገጽ ፯፻፵፬ [1]

ምንጭ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]