አልፋቤት

ከውክፔዲያ
በ3ቱ ዋና ፊደላት (ግሪክ፣ ላቲን፣ ቂርሎስ) 11ዱ ቅርጾች ለሁሉ የጋራ መሆናቸውን የሚያሳይ ካርታ

አልፋቤት ማለት የዓለም ጽሕፈቶች ከተባሉት አምስት ዋና መደቦች አንዱ ነው። በአልፋቤቶች ውስጥ፣ እያንዳንዱ ምልክት ወይም ፊደል ባጠቃላይ ለተወሰነ ድምጽ ክፍል (እንደ ተነባቢ ወይም አናባቢ) ይወክላል።

ከአልፋቤቶች ቀድሞ በሆነ ዘዴ በ«ሎጎግራም» ጽሕፈት እያንዳንዱ ምልክት ለተለየ ቃል ወይም ክፍለ-ቃል ይወክላል፣ ለምሳሌ የቻይና ጽሕፈት ዛሬም እንዲህ ነው። እንዲሁም «ሲላቢክ» በሚባለው መደብ፣ እያንዳንዱ ምልክት የተለየ ክፍለ-ቃል ድምጽ ያሰማል፣ ለምሳሌ የጻላጊኛ ጽሕፈት፣ ወይም እንደ አቡጊዳ ወይም እንደ ሕንድ ብራሚክ ጽሕፈቶች ቤተሠብ፣ የክፍለ-ቃል ድምጽ ምልክቶች እንደ አነንባቢው ተመሳሳይ ናቸው። ስለዚህ «አልፋቤቶች» እንደ «ሎጎግራም» ወይም «ሲላቢክ» ሳይሆኑ ከነዚህ ሁሉ የተለዩ ናቸው።

ከሁሉ አስቀድሞ የተደረጁት አልፋቤቶች ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት ሲሆኑ ለአናባቢዎቹ የተለዩ ምልክቶች አልነበራቸውም፣ ስለዚህ የነዚህ አልፋቤት አይነት «አብጃድ» ነው። የፊንቄ አብጃድየዕብራይስጥ አብጃድየአረብኛ አብጃድየአረማይስጥ አብጃድ ወዘተ. ሁላቸው በዚህ አይነት ናቸው። ስያሜው «አብጃድ» ከአረብኛ መጀመርያ ፊደል ስሞች መጣ። ከነዚህም ብዙዎች እንደ ዕብራይስጥና አረብኛ አናባቢዎቹን በሌሎች ነጥቦች በኋላ አመለከቱ።

ምናልባት ከ800 ዓክልበ. ግድም ጀምሮ ግሪኮች የፊንቄ አብጃድ ትንሽ ቀይረው የአንዳንድ ድምጽ ጥቅም ከተነባቢ ወደ አናባቢ አዛወሩት። እነዚህ ከመጀመርያ የግሪክ አልፋቤት ፊደሎች ስሞች «አልፋ» እና «ቤታ» የተነሣ እውነተኛ «አልፋቤቶች» ይባላሉ። የአለም ዋና አልፋቤቶች በተለይም የላቲን አልፋቤትየቂርሎስ አልፋቤት ከዚያ ተደረጁ።

ብዙ ቋንቋዎች በአንድ ተመሳሳይ አልፋቤት አይነት ሊጻፉ ይችላሉ፣ እያንዳንዱም ቋንቋ ልዩ ምልክቶችን ለራሱ ጥቅሞች ሊያዘጋጅ ይችላል።

ደግሞ ይዩ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]