አቡጊዳ

ከውክፔዲያ
ለፊልሙ፣ አቡጊዳ (ፊልም) ይዩ።
አቡጊዳ ታሪክ

አቡጊዳ (Ebugida) ማለት ፊደል ነው። ከልሳነ ግዕዝ የተነሣ ነው። ቢሆንም በቅርብ ጊዜ አንዳንድ የፈረንጅ አገር ሊቅ ይህን አባባል ለቋንቋዎች ጥናት ተበድሯል። በዚሁ አነጋገር "አቡጊዳ" ማለት በዓለም የሚገኙ ልዩ ልዩ አይነት ጽሕፈቶች ሊያመልከት ይችላል። በየአገሮቹ ፊደላቸው "አቡጊዳ" የሚባለው እያንዳንዱ ፊደል ለክፍለ-ቃል ለመወከል ሲሆን ነው እንጂ እንደ እንግሊዝኛ "አልፋቤት" ፊደሉ ለ1 ተነባቢ ወይም ለ1 አናባቢ ብቻ ሲሆን አይደለም። ስለዚህ የግዕዙ ፊደል ይሁንና ሌሎችም ለምሳሌ ብዙ የህንድ አገር አጻጻፎች ጨምረው አቡጊዳ በሚግድጅቭጅለው ስም ይታወቃሉ።

ብራህሚክ ወይም ደቫናጋሪ በተባሉት የህንድ አጻጻፎች በኩል እያንዳንዱ ክፍለ-ቃል በተለየ ፊደል ሲወከል የአናባቢዎች መጠን የሚታየው የፊደሉን መልክ (እንደ ግዕዝ ወይም እንደ አማርኛ) ትንሽ በመቀየሩ ነው። ስለዚህ በቋንቋ ሊቃውንት ዘንድ 'አቡጊዳዎች' ይባላሉ። በተጨማሪ፣ በካናዳ አገር ለጥንታዊ ኗሪ (ቀይ ኢንዲያን የተባሉ) ጐሣዎች ያላቸው አጻጻፍ እንደዚህ አይነት ነው፤ አናባቢው በቅርጹ የሚታየው ፊደሉን በመዞር ወይም በመገልበጥ ነውና።

በግእዝ አቡጊዳ ለሚለው የቃሉ መነሻ ከጥንታዊ የሴም ፊደል ተራ የሚለቀመው ነበር። በግሪክም ይህ ፊደል ተራ በ A, Β, Γ, Δ ጀመረ፤ ወይም በስም አልፋ፣ ቤታ፣ ጋማ፣ ዴልታ ናቸው። ይህ ፊደል ተራ በ ሀ ሁ ሂ ሃ በሚል ቅርጽ ማለት በግእዝ፣ በካዕብ፣ በሣልስ፣ በራብእ ውስጥ ገብቶ ሲሰካ፣ አ፣ ቡ፣ ጊ፣ ዳ የሚለውን ፊደል ተራ አስገኘ። ሁሉ በሙሉ የግእዝ አቡጊዳ እንግዲህ እንደሚከተለው ሰንጠረዥ ነው።


አ ቡ ጊ ዳ ሄ ው ዞ
በ ጉ ዲ ሃ ዌ ዝ ዦ
ገ ዱ ሂ ዋ ዜ ዥ ሖ
ደ ሁ ዊ ዛ ዤ ሕ ጦ
ሀ ዉ ዚ ዣ ሔ ጥ ጮ
ወ ዙ ዢ ሓ ጤ ጭ ዮ
ዘ ዡ ሒ ጣ ጬ ይ ኮ
ዠ ሑ ጢ ጫ ዬ ክ ኾ
ሐ ጡ ጪ ያ ኬ ኽ ሎ
ጠ ጩ ዪ ካ ኼ ል ሞ
ጨ ዩ ኪ ኻ ሌ ም ኖ
የ ኩ ኺ ላ ሜ ን ኞ
ከ ኹ ሊ ማ ኔ ኝ ሶ
ኸ ሉ ሚ ና ኜ ስ ሾ
ለ ሙ ኒ ኛ ሴ ሽ ዖ
መ ኑ ኚ ሳ ሼ ዕ ፎ
ነ ኙ ሲ ሻ ዔ ፍ ጾ
ኘ ሱ ሺ ዓ ፌ ጽ ቆ
ሰ ሹ ዒ ፋ ጼ ቅ ሮ
ሸ ዑ ፊ ጻ ቄ ር ሦ
ዐ ፉ ጺ ቃ ሬ ሥ ቶ
ፈ ጹ ቂ ራ ሤ ት ቾ
ጸ ቁ ሪ ሣ ቴ ች ኆ
ቀ ሩ ሢ ታ ቼ ኅ ጶ
ረ ሡ ቲ ቻ ኄ ጵ ፆ
ሠ ቱ ቺ ኃ ጴ ፅ ፖ
ተ ቹ ኂ ጳ ፄ ፕ ጆ
ቸ ኁ ጲ ፃ ፔ ጅ ኦ
ኀ ጱ ፂ ፓ ጄ እ ቦ
ጰ ፁ ፒ ጃ ኤ ብ ጎ
ፀ ፑ ጂ ኣ ቤ ግ ዶ
ፐ ጁ ኢ ባ ጌ ድ ሆ
ጀ ኡ ቢ ጋ ዴ ህ ዎ
አቡጊዳ ፲፱፻፹፫ ዓ.ም. (Ebugida Sorting Order) Ethiopian Review, 1991

ኣበራ ሞላ