ርእስ

ከውክፔዲያ

ረ ሩ ሪ ራ ሬ ር ሮ ሯ



አቡጊዳ ታሪክ

ርእስ በጥንታዊ አቡጊዳ ተራ 20ኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥ ፊደሎች በሶርያም 20ኛው ፊደል «ሬስ» ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል «ራእ» ተብሎ በ«አብጃድ» ተራ 20ኛ ነው።

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ተመሳሳይ ግብፃዊ ስዕል ቅድመ-ሴማዊ ሣባ ግዕዝ
D1


የርእስ መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ የራስ ስዕል መስለ። ለዚህም ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ ነበር። አጠራሩ ግን «ተፕ» ነበር። በግብፅ የሠሩት ሴማውያን ግን በቋንቋቸው «ሬስ» ስላሉት፣ ይህ ስዕል "ር» ሆኖ እንዲሰማ መጣ።

ከነዓን አራማያ ዕብራይስጥ ሶርያ ዓረብኛ
ሬስ ሬስ ר ሬስ


የከነዓን «ሬስ» እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ «ሬስ» የአረብኛም «ራእ» ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት ፊደል «ሮ» (Ρ, ρ) አባት ሆነ። እሱም የላቲን አልፋቤት (R r) እና የቂርሎስ አልፋቤት (Р р) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ«ርእስ» ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል። በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥር (መቶ) ከግሪኩ ρ በመወሰዱ እሱም የ«ረ» ዘመድ ነው።