ላዊ

ከውክፔዲያ

ለ ሉ ሊ ላ ሌ ል ሎ ሏ



አቡጊዳ ታሪክ

ላዊ (ወይም ላዌ፥ ለው) በጥንታዊ አቡጊዳ ተራ 12ኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥሶርያም ፊደሎች 12ኛው ፊደል «ላሜድ» ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል «ላም» ተብሎ በ«አብጃድ» ተራ 12ኛ ነው።

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ተመሳሳይ ግብፃዊ ስዕል ቅድመ-ሴማዊ ሣባ ግዕዝ
S39


የላዊ መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ የቅዝምዝም ስዕል መስለ። ለዚህም ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ ነበር። አጠራሩ ግን «ዐወት» ነበር። በግብፅ የሠሩት ሴማውያን ግን በቋንቋቸው «ላሜድ» ስላሉት፣ ይህ ስዕል «ል» ሆኖ እንዲሰማ መጣ።

ከነዓን አራማያ ዕብራይስጥ ሶርያ ዓረብኛ
ላሜድ ላሜድ ל ላሜድ


የከነዓን «ላሜድ» እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ «ላሜድ» የአረብኛም «ላም» ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት «ላምብዳ» (Λ, λ) አባት ሆነ። እሱም የላቲን አልፋቤት (L l) እና የቂርሎስ አልፋቤት (Л л) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ«ላዊ» ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል። በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥር (ሠላሳ) ከግሪኩ Λ በመወሰዱ እሱም የ«ለ» ዘመድ ነው።