ማይ

ከውክፔዲያ

መ ሙ ሚ ማ ሜ ም ሞ ሟ



አቡጊዳ ታሪክ

ማይ በጥንታዊ አቡጊዳ ተራ 13ኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥሶርያም ፊደሎች 13ኛው ፊደል «ሜም» ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል «ሚም» ተብሎ በ«አብጃድ» ተራ 13ኛ ነው።

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ተመሳሳይ ግብፃዊ ስዕል («ነ») ቅድመ-ሴማዊ ሣባ ግዕዝ
N35


የማይ መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ የውሃ ስዕል መስለ። ለዚህም ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ ነበር። አጠራሩ ግን «ነ» ነበር። በግብፅ የሠሩት ሴማውያን ግን በቋንቋቸው «ሜም» ስላሉት፣ ይህ ስዕል «ም» ሆኖ እንዲሰማ መጣ።

ከነዓን አራማያ ዕብራይስጥ ሶርያ ዓረብኛ
ሜም ሜም מ,ם ሜም


የከነዓን «ሜም» እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ «ሜም» የአረብኛም «ሚም» ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት «ሙ» (Μ, μ) አባት ሆነ። እሱም የላቲን አልፋቤት (M m) እና የቂርሎስ አልፋቤት (М м) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ«ማይ» ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል። በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥር (ዓርባ) ከግሪኩ μ በመወሰዱ እሱም የ«መ» ዘመድ ነው።