እፃዊ ተዋልዶ

ከውክፔዲያ

እፃዊ ተዋልዶ ለአትክልት የኢሩካቤያዊ መራቦ ዘዴ ነው። በዚህ ተፈጥሮአዊ ሂደት ያለ ምንም ዘር ወይም ዱኬ አዲስ ተክሎች ሊገኙ ይቻላል። ስለዚህ ለምጣኔ ሀብት ዋጋ ላላቸው ዛፎች ለማስፋፋት በተለይ በግብርና ሰፊ ጠቀሜታ አለው።

በተፈጥሮ ሲታይ፣ በልዩ ልዩ ዘዴዎች ሊሆን ይችላል። ለአንዳንድ አትክልት፣ ተቀብሮ (ውስጠ ዘመት) ግንድ ከምድር በታች አዲስ ሥር ወይም ቡቃያ ያስወጣል። በሌሎች ዝርያ፣ ከምድር በላይ ተባዥ ሐረጎች አዲስ ሥር ወይም ቡቃያ ያስወጣል። ስሁት የሚባለው ሥር አለ። ደግሞ በእኩራች ወይም በድንቼ ስረግንድ የሚበዛ አትክልት (ለምሳሌ ነጭ ሽንኩርት) አለ።

በገነት ወይም በእርሻ ተግባር እፃዊ ተዋልዶ ማለት ከዛፍ አንድ ቅርንጫፍ አገዳ ከመሃል አንጓ በታች ተቈርጦ፣ በሌላ መሬት ውስጥ ተክሎ፣ አዲስ ሥር ሲያስገኝ ነው። በዚሁ ዘዴ ብዙ ጠቃሚ የአትክልት አይነቶች ያለ ምንም ዘሮች በቀላሉ ለማብዛት ይቻላል፤ ለምሳሌ፦