ኦሪት

ከውክፔዲያ

ኦሪት ማለት በተለይ የብሉይ ኪዳን መጀመርያ ፭ መጻሕፍት ወይም የሙሴ መጻሕፍት ማለት ነው፣ ወይም በእብራይስጥ «ቶራህ» የተባለው ክፍል። ኤነዚህም ፭ መጻሕፍት፦

«የኦሪት ሕግ» ማለት በነዚህ መጻሕፍት ውስጥ የተጻፈው አስርቱ ቃላትሕገ ሙሴ ነው።

በዘመናዊ አማርኛ «ኦሪት» ለዕብራይስጥ «ጦራህ» ወይም ለግሪክኛ «ፔንታቲውክ» ይወክላል፣ ልዩ ልዩ ትርጓሜዎች ኦሪተ ሳምራውያንኦሪተ አይሁድኦሪተ ሊቃውንት ተብለዋል።

ግዕዝ ግን ተጨማሪ ሦስት መጻሕፍት በ«ኦሪት» ይቆጠራሉ፦

«ኦሪት» ደግሞ ጥንታዊ ዘመን ወይም በተለይ እነዚህ መጻሕፍት የሚተርኩት ዘመን (ከ1000 ዓክልበ. በፊት) ማለት ነው፤ ከማየ አይኅ አስቀድሞ የነበረውም ክፉ ዘመን ያጠቅልላል። «ኦሪታውያን» ማለት ደግሞ በጥፋት ውሃ የሰመጠው ክፉ ነገድ ሊሆን ይችላል፣ የዚህም አጠራር ከግብጽ ጣኦት ሔሩ ጋር እንደ ተዛመደ ይመስላል።

:

"ኦሪት" የሚለው ቃል የተገኘው "ኦር" ከሚለው የዕብራይስጥኛ ቃል ነው። በዕብራይስጥኛ "ኦር፡אוֹר"ማለት "ብርሃን" ማለት ነው። ይህም በአምስቱ የሕግ/ቶራህ መጽሐፍት የተዘገቡት የእግዚአብሔር ቃላት ብርሃን ሁነው የሰውን ልጅ መንገድ ስለሚመራ ነው። ይሄንንም በመዝሙረ ዳዊት እንዲህ ተብሎ እናገኘዋለን፡ “ሕግህ ለእግሬ መብራት፥ ለመንገዴ ብርሃን ነው።” መዝሙር 119፥105 ሲል ያስረግጥልናል።