ኦሪት
Jump to navigation
Jump to search
:
ኦሪት ማለት በተለይ የብሉይ ኪዳን መጀመርያ ፭ መጻሕፍት ወይም የሙሴ መጻሕፍት ማለት ነው፣ ወይም በእብራይስጥ «ቶራህ» የተባለው ክፍል። ኤነዚህም ፭ መጻሕፍት፦
«የኦሪት ሕግ» ማለት በነዚህ መጻሕፍት ውስጥ የተጻፈው አስርቱ ቃላትና ሕገ ሙሴ ነው።
በዘመናዊ አማርኛ «ኦሪት» ለዕብራይስጥ «ጦራህ» ወይም ለግሪክኛ «ፔንታቲውክ» ይወክላል፣ ልዩ ልዩ ትርጓሜዎች ኦሪተ ሳምራውያን፣ ኦሪተ አይሁድ፣ ኦሪተ ሊቃውንት ተብለዋል።
በግዕዝ ግን ተጨማሪ ሦስት መጻሕፍት በ«ኦሪት» ይቆጠራሉ፦
- መጽሐፈ ኢያሱ (ኦሪት ዘኢየሱስ)
- መጽሐፈ መሳፍንት (ኦሪት ዘመሳፍንት)
- መጽሐፈ ሩት (ኦሪት ዘሩት)
«ኦሪት» ደግሞ ጥንታዊ ዘመን ወይም በተለይ እነዚህ መጻሕፍት የሚተርኩት ዘመን (ከ1000 ዓክልበ. በፊት) ማለት ነው፤ ከማየ አይኅ አስቀድሞ የነበረውም ክፉ ዘመን ያጠቅልላል። «ኦሪታውያን» ማለት ደግሞ በጥፋት ውሃ የሰመጠው ክፉ ነገድ ሊሆን ይችላል፣ የዚህም አጠራር ከግብጽ ጣኦት ሔሩ ጋር እንደ ተዛመደ ይመስላል።