ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/የካቲት 16

ከውክፔዲያ

የካቲት ፲፮

  • ፲፱፻፳፱ ዓ/ም - በግራዚያኒ የሚመራ የፋሺስት ኢጣልያ ሠራዊት በዝዋይ አካባቢ የጦር አዝማቾቹን የራስ ደስታ ዳምጠውን እና የደጃዝማች በየነ መርዕድን አርበኞት ድል አደረጉ። ሁለቱም ኢትዮጵያውያን አዝማቾች ሕይወታቸውን በዚህ ዕለት ሰዉ። ኢጣሊያውያኑ ራስ ደስታን ከያዟቸው በኋላ በጥይት ደበደቧቸው፡፡
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም ኢትዮጵያ ላይ በፈነዳው አብዮት አስገዳጅነት የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት የሕዝቡን ሸክም ለማቃለል የነዳጅ ዋጋ ቅነሳን የሚያካትት ኤኮኖሚያዊ እርምጃዎችን እንደሚወስድ ይፋ አደረገ።