ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ግንቦት 25

ከውክፔዲያ

ግንቦት ፳፭

  • ፲፱፻፳፩ ዓ/ም - የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የመጀመሪያዎቹን አራት ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት (አቡነ አብርሓም - የጎንደር እና የጎጃም፤ አቡነ ይስሐቅ - የትግሬ እና የስሜን፤ አቡነ ጴጥሮስ የወሎ እና የላስታ፤ አቡነ ሚካኤል - የኢሉባቡር እና የምዕራብ ኢትዮጵያ) ከግብጻዊው ሊቀ ጳጳሳት (አቡነ ቄርሎስ)ጋር ካይሮ ላይ ተቀብተው ተሾሙ።
  • ፲፱፻፵፭ ዓ/ም - የታላቋ ብሪታኒያ ንግሥት ዳግማዊት ኤልሳቤጥ በዚህ ዕለት ቅብዐ ቅዱስ ተቀብተው ከአባታቸው ከንጉሥ ጊዮርጊስ ሳድሳዊ የወረሱትን ዘውድ ጫኑ። የዘውዱ ሥነ ሥርዓት በመቶ ሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ የራዲዮ አድማጮች የተሠራጨ ሲሆን በታሪክ ለመጀመሪያም ጊዜ በአዲሱ የትዕይንተ መሳታዋት (television) ታይቷል።
  • ፲፱፻፴፰ ዓ/ም - የኢጣልያ ሕዝብ በጣለው የድምጽ ምርጫ የንጉዛታዊ ሥርዓትን ትቶ አገሪቱ የሪፑብሊካዊ አስተዳደር እንድትከተል አደረገ። የቀድሞው ንጉሥ ዳግማዊ ኡምቤርቶ አገር ለቅቀው ተሰደዱ።