ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ግንቦት 3

ከውክፔዲያ
  • ፲፱፻፲፮ ዓ/ም - ሁለቱ ጀርመናውያን ተሽከርካሪ አምራቾች፣ ጎትሊብ ዴይምለር እና ካርል ቤንዝ ኩባንያዎቻቸውን አዋሕደው አዲሱን የመርሴዲስ-ቤንዝ (Mercedes-Benz) ኩባንያ መሠረቱ።
  • ፲፱፻፵፰ ዓ/ም- የብሪታኒያ የቅኝ ግዛቶች ሚኒስትር የምዕራብ አፍሪቃዋ ጎልድ ኮስት (በኋላ ጋና) ነጻነቷን እንደምትሰጥ መወሰኑን ለሕዝብ ተወካዮች ሸንጎ አስታወቀ።
  • ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የውጭ ጣልቃ ገቦች በአገሪቱ ጉዳይ ውስጥ እየገቡ አስቸግረዋል በሚል መነሻ የፈረንሳይን፤ አሜሪካን፤ ግብጽን፤ የሶቪዬት ሕብረትን፤ የብሪታኒያን እና የዩጎዝላቪያን የልዑካን አለቆች ሰብስበው አነጋገሩ። በማግሥቱ ይፋ የተደረገው ጽሑፋዊ ቃለ-ጉባኤ አምባሳደሮቹ የተጠሩት «የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት በአፍሪቃ ቀንድ አካባቢ ጉዳዮች ላይ የባዕዳንን ጣልቃ ገብነት በብርቱ እንደሚቃወም እና በኢትዮጵያ ግዛትና ሉዐላዊነት ላይ የሚሰነዘሩትን ማናቸውንም እርምጃዎች ለመከላከል ቆራጥ መሆኑን እንዲገነዘቡ ነው።» ይላል።