የ1970 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ

ከውክፔዲያ

የ1970 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ

ይፋዊ ምልክት
ይፋዊ ምልክት
ይፋዊ ምልክት
የውድድሩ ዝርዝር
አስተናጋጅ  ሜክሲኮ
ቀናት ከግንቦት ፳፫ እስከ ሰኔ ፲፬ ቀን
ቡድኖች ፲፮ (ከ፭ ኮንፌዴሬሽኖች)
ቦታ(ዎች) ፭ ስታዲየሞች (በ፭ ከተማዎች)
ውጤት
አሸናፊ  ብራዚል (፫ኛው ድል)
ሁለተኛ  ኢጣልያ
ሦስተኛ  ምዕራብ ጀርመን
አራተኛ  ኡራጓይ
እስታቲስቲክስ
የጨዋታዎች ብዛት ፴፪
የጎሎች ብዛት ፺፭
የተመልካች ቁጥር 1,603,975
ኮከብ ግብ አግቢ(ዎች) ምዕራብ ጀርመን ጀርድ ሙለር
፲ ጎሎች
እንግሊዝ 1966 እ.ኤ.አ. ምዕራብ ጀርመን 1974 እ.ኤ.አ.

የ1970 እ.ኤ.አ. ፊፋ የዓለም ዋንጫ ፱ኛው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሲሆን ከግንቦት ፳፫ እስከ ሰኔ ፲፬ ቀን ፲፱፻፷፪ ዓ.ም. በሜክሲኮ ተካሄዷል። ይህ ውድድር ለመጀመሪያ ጊዜ በሰሜን አሜሪካ የቀረበው የዓለም ዋንጫ ነው። ብራዚል ጣሊያንን ፬ ለ ፩ በመርታት ለ፫ኛ ጊዜ ውድድሩን አሸንፏል። የጁልስ ሪሜት ዋንጫ ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ውድድር የተሸለመ ሲሆን ተሸላሚው የብራዚል ቡድን እስከ መጨረሻው ዋንጫውን እንዲይዝ ተፈቅዶለታል።