ፎገራ

ከውክፔዲያ


የፎገራ ወረዳ መሬት ይዞታ ባሕርይ[1]

  ሊታረስ እሚችል (44.2%)
  በመስኖ የለማ (20%)
  ግጦሽ (22.9%)
  ደን (1.8%)
  በውሃ የተሸፈነ (3.7%)
  ሊለማ እማይችል (7.4%)

ፎገራ በደቡብ ጎንደር የሚገኝ ወረዳ ሲሆን፣ የወረዳው አስተዳደር ማዕከል ወረታ ይሰኛል። በዚህ ወረዳ ውስጥ ከሚገኙ ታዋቂ ትናንሽ ከተሞች ውስጥ አመድ በር እና አውራአምባ ይገኛሉ።

ጉማራ እና ርብ ወንዝ ይህን ክፍል ሲያካልሉት ለጣና ሐይቅ ያለው ቅርበት ደግሞ የውሃ ሃብቱን ያጎላዋል። 490 ስኩየር ኪ.ሜ. እሚያክለው የዚህ ወረዳ መሬት በየአመቱ በጣና ሐይቅ ሙላት ምክንያት የጎርፍ ተጠቂ ነው። [2] ጤፍማሽላዳጉሳጥጥሰሊጥ ዋናዎቹ የዚህ ወረዳ ምርቶች ናቸው። የፎገራ ላም ለየት ያለ የላም ዝርያ ዓይነት ሲሆን በግዙፍነቱና በከፍተኛ የወተት ምርቱ ይታወቃል። ሆኖም በበጋ ወራት ከከምከም እና ደራ ወረዳዎች ላሞች ወደዚህ ወረዳ ለግጦሽ ስለሚመጡ የዚህ ዝርያ ላም በመዳቀል ኅልውናው አስጊ ሆኗል።

ፎገራ የአለቃ ገብረሃና የትውልድ ቦታ በመሆኑም ይታዎቃል።

የሕዝብ ስብጥር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የከምከም ወረዳ ሕዝብ ቁጥር [3] [4]
ዓ.ም.** የሕዝብ ብዛት
1986
185,280
1999
228,449


ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ Ethiopia-Sudan Power Systems Interconnection Project, ESIA Final Report, p. 55 (Ethiopian Electric Power Corporation website) This was based on information provided by the woreda in 2006.
  2. ^ "Tana & Beles Integrated Water Resources Development: Project Appraisal Document (PAD), Vol.1", World Bank, 2 May 2008 (accessed 5 May 2009)
  3. ^ Census 2007 Tables: Amhara Region, Tables 2.1, 2.4, 2.5, 3.1, 3.2 and 3.4.
  4. ^ 1994 Population and Housing Census of Ethiopia: Results for Amhara Region, Vol. 1, part 1, Tables 2.1, 2.7, 2.10, 2.13, 2.17, Annex II.2 (accessed 9 April 2009)