ንፋስ ስልክ ላፍቶ በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ካሉት ዐሥሩ ክፍለ ከተሞች ውስጥ አንዱ ነው። እስከ እ.ኤ.አ 2011 ባለው መረጃ መሠረት የሕዝብ ብዛቱ 335,740 ነው።
ንፋስ ስልክ ላፍቶ የሚገኘው በአዲስ አበባ ደቡብ አቅጣጫ ላይ ሲሆን ልደታን፣ ቦሌን፣ አቃቂ ቃሊቲን፣ ኮልፌ ቀራንዮን እና ቂርቆስን ያዋስናል።