ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/የካቲት 15

ከውክፔዲያ

የካቲት ፲፭

  • ፲፱፻፶፪ ዓ/ም - ግብጽ እና ሶርያ የአረብ ሪፑብሊ ኅብረትን (United Arab Republic) መሠረቱ። ይሄ የሁለቱ አገሮች ኅብረት ከሦስት ዓመታት በኋላ ቢፈርስም የግብጽ መጠሪያ ስሟ ሆኖ ለብዙ ዓመታት ቆይቷል።.
  • ፲፱፻፷፮ ዓ/ም - በኢትዮጵያአብዮት ፍንዳታ የተፋፋመውን ሽብር ለመቆጣጠር በተወሰደው እርምጃ፣ የንጉሠ ነገሥቱ መንግሥት ወታደሮችን በአዲስ አበባ ከተማ ቀበሌዎችና ‘ቁልፍ’ ቦታዎች ለጥበቃ አሰማራ።
  • ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - ኢትዮጵያ ሕገ ወጥ የአውሮፕላን ጠለፋ ለመከላከል በዓለም ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት የጸደቀውን ስምምነት ፈረመች።
  • ፲፱፻፺፬ ዓ/ም አንጎላዊው የፖለቲካ እና የነጻነት ትግል መሪ የነበሩት ጆናስ ሳቪምቢ በወታደራዊ የደፈጣ ስልት ተገደሉ።