የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መሣሪያዎች
Appearance
ኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ የባህል ሙዚቃ መሣሪያዎች አሉ። እነዚህም መሣሪያዎች የጅማት፣ የትንፋሽና የምት ተብለው ወደ ሶስት ይከፈላሉ።
እነዚህ መሣሪያዎች ድምጽ የሚሰጡት በንዝረት ነው።
እነዚህ መሣሪያዎች ድምጽ የሚሰጡት በትንፋሽ ኃይል ነው።
- ዋሽንት፡ አብዛኛውን ጊዜ እረኞች በሀገር ቤት ይገለገሉበታል። በተጨማሪም በመድረክ ላይ ለክራርና ለመሰንቆ ቅኝት በመስጠትና ዜማን በማጀብ ያገለግላል።
- አምቢልታ፡ ሶስት ዓይነት አመቢልታዎች አሉ። ስማቸውም ኡፍን፣ አውራ እና የማ ነው። በኢትዮጵያ ለክብረ በዓልና ወደ ጦር ሜዳ ለሚሄድ ሰልፈኛ የሚነፋ አድማቂ መሣሪያ ነው።
- መለከት፡ ቀደም ባለው ጊዜ ሰዎች ተሰብስበው የመንግሥት አዋጅ እንዲሰሙ ትዕዛዝን መስጫ መሣሪያ ሆኖ ሲያገለግል የቆየ ነው።
- ድንኬ፡ በሲዳሞ ክፍለ ሀገር በወላይታ አካባቢ ለአስከሬን ማጀቢያነት የሚያገለግል መሣሪያ ነው።
- ፖረሬሳ፡ በደቡብ ኢትዮጵያ ለዘፈን ማጀቢያ የሚያገለግል መሣሪያ ነው።
- ሁራ፡ በከፋ ክፍለ ሀገር ያሉ ጎሳዎች የሚጠቀሙበት የሙዚቃ መሣሪያ ነው።
- ሁልዱዱዋ፡ በሲዳሞ ክፍለ ሀገር የቀብር ሥነ ሥርዓት ለመግለጽ የሚነፋ መሣሪያ ነው።
- ጨቻ ዝዬ፡ በደቡብ ኢትዮጵያ ውዝዋዜ ለማድመቅ የሚያገለግል የሙዚቃ መሣሪያ ነው።
- ዛክ፡ በከፋ ክፍለ ሀገር የሚገኝ የሙዚቃ መሣሪያ ነው።
- ሸመቶ፡ በከፋ ክፍለ ሀገር የሚገኝ የሙዚቃ መሣሪያ ነው።
- ፋንፋ፡ በከፋ ክፍለ ሀገርና በጋሞጎፋ /ኮንሶ/ የሚገኝ የሙዚቃ መሣሪያ ነው።
- አዋዛ፡ በወለጋ ክፍለ ሀገር በአሶሳ አካባቢ የሚገኝ የሙዚቃ መሣሪያ ነው።
- ከበሮ፡ ለዘፈን ማድመቂያና ለሠርግ እንዲሁም ለቤተ ክርስቲያን ዝማሬ ቀሳውስት በሽብሸባ ጊዜ የሚጠቀሙበት መሣሪያ ነው።
- አታሞ፡ ለሙዚቃና ለጭፈራ የሚያገለግል መሣሪያ ነው።
- ነጋሪት፡ በሰልፍ ጊዜ የሚጎሰም የሙዚቃ መሣሪያ ነው።
- መቋሚያ፡ ለመንፈሳዊ ዝማሬ ከከበሮው ስልት ጋር በተዛመደ ሁኔታ በመንቀሳቀስ ቀሳውስት የሚጠቀሙበት መሣሪያ ነው።
- ፀናፅል፡ ለመንፈሳዊ ዝማሬ ቀሳውስት የሚጠቀሙበት መሣሪያ ነው።
- ቅል፡ ቅል በውስጡ ጠጠሮች ወይም ፍሬዎች ተጨምረውበት ለዘፈን ማድመቂያ ያገለግላል።
- ቻንቻ፡ በጋሞጎፋ ክፍለ ሀገር በጭፈራ ጊዜ በወገብ ላይ የሚታሰር አዳማቂ መሣሪያ ነው።
- ካመባ፡ ከሸክላ የተሠራ በደቡብና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኝ መሣሪያ ነው።
- ቃጭል፡ አብዛኛውን ጊዜ ለመንፈሳዊ ዜማ የሚያገለግል መሣሪያ ነው።
- ቶሞ፡ በጋምቤላ ብሔረሰብ ውስጥ እውቅና ተወዳጅ የሆነ የሙዚቃ መሣሪያ ነው። በተጨማሪም በኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛኒያ፣ ናይጄሪያ፣ ሱዳንና ዛየርም በዚህ መሣሪያ እንደሚጠቀሙ ታውቋል።
- ጋሬ፡ በጋምቤላ ብሔረሰብ ውስጥ በእግር ላይ ታስሮ ጭፈራን የሚያደምቅ የሙዚቃ መሣሪያ ነው።
- የግመል ቃጭል፡ ይህ መሣሪያ በተለይ ከእንጨት የሚሠራ ሆኖ ሙዚቃን ለማጀብ የሚጠቅም መሣሪያ ነው።
1ኛ ፊፊ_የጃዊ፣የዳንጉ እና የቋራ ወረዳ አገዎች የመስቀል ክብረ በአል እለት ቤተክርስትያን በመሄድ የሚጫወቱት የትንፋሽ መሳሪያ 2ኛ እንዲልቤል_የጃዊ፣የዳንጉር እና የቋራ ወረዳ አገዎች ከብርቱካ መሰል ከዛፍ ፍሬ የምትሰራ አንድ አፍ እና መገቡ ላይ ሁለት ቀዳዳ ያላት የትንፋሽ መሳሪያ ናት 3ኛ እምቢልታ_የጃዊ፣የዳንጉር፣የቋራ ወረዳ አገዎች የሰርግ ማጀብያነት ይጠቀማሉ
- ናሽናል ቢብሊዮግራፊ ቡድን፣ የአንጋፋ አርቲስቶች መዝገበ የሕይወት ታሪክ፣ መጋቢት ፳፻፣ ገጽ 32-35 Archived ሴፕቴምበር 29, 2011 at the Wayback Machine