የ፳፻፫ ዓ.ም. የሊቢያ ሕዝባዊ አብዮት

ከውክፔዲያ
አረንጓዴ በጋዳፊ ሃይሎች እጅ የሚገኙ ከተሞች፣ ቡናማ በፀረ-ጋዳፊ ሃይሎች እጅ የሚገኙ ከተሞች እና ቢጫ በየትኛው እጅ እንደሚገኙ ያልታወቁ ከተሞች

የ፳፻፫ ዓ.ም. የሊቢያ ሕዝባዊ አብዮትሊቢያ ውስጥ የተከሰተ እና በሰሜን አፍሪቃ በተከታታይ ከተደረጉ የተለያዩ ሀገራት ፀረ መንግስታዊ አብዮቶች አንዱ ነው። ይህ አብዮት የተጀመረው በእ.አ.አ. 15 ፌብሩዋሪ 2011 ሲሆን በዚሁ ወር መጨረሻ አካባቢ በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች ተባብሶ ታይቷል። አብዮቱ በዋናነት የኮለኔል ሞአመር ጋዳፊን የ42 ዓመታት የስልጣን ላይ ቆይታ በመቃወም ነው። ፀረ መንግስታዊ አገዛዙን በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰቱ አብዮቶች ጋር እንዲያያዝ የሚያደርገው ዋናው ነገር በቱኒዚያ እና ግብፅ የተደረጉ ሕዝባዊ አብዮቶች ተከትሎ መደረጉ ነው። [1]

የኋላ ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ታሪክ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሞአማር ጋዳፊ ቀድሞ የነበረውን አሃዳዊ አገዛዝ በመገርሰስ የስልጣን መንበሩን የተቆናጠጠው እ.አ.አ. በ1969 ነበር።[2]ኡመር ቦንጎን በእ.አ.አ. 2009 መሞት እና የፊደል ካስትሮን በእ.አ.አ. 2008 ከስልጣን መውረድ ተከትሎ የሊቢያው ሞአማር ጋዳፊ በህይወት የሚገኝ እና ለረዥም ጊዜ ሥልጣን ላይ የቆየ ኢ-ንጉሳዊ መሪ ነው።[3]

የህትመት ነፃነት ሥርዓት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እንደ የህትመት ነፃነት ማውጫ መሰረት ሊቢያ በህትመት ነፃነት በኩል ከመካከለኛው ምስራቅ እና ሰሜን አፍሪካ በከፍተኛ ሁኔታ የከበደ ቁጥጥር የሚደረግባት ሀገር ናት።[4] በአብዛኸኛው የሀገሪቱ ፍርድ ከውጭ ሀገር ዜጋ ጋር ስለፖለቲካ ጉዳዮች መነጋገር እስከ ሶስት ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት ሲያስጥል ቆይቷል። ጋዳፊ በሀገሪቱ ውስጥ የውጭ ቋንቋዎች እንዲጠፉ አድርጓል። ከነዚህም እ.አ.አ. 1986 ከአሜሪካ እና እንግሊዝ ጋር ዲፕሎማሲያዊ እንዲሁም ሌሎች ግንኙነቶች ሲቋረጡ እንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት እንዳይሰጥ ከልክሎ ነበር። [5]

ቅድመ አነሳስ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

አቡ ሳሊም ፕሪሰን የተባለው የሊቢያ ከፍተኛ የጠበቃ ባለስልጣን በሀገሪቱ ለተደረጉ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ተጠያቂ መሆን አንዱ ለአብዮቱ መነሳት እንደዋነኛ ምክንያትነት ይጠቀሳል።[6] ይህ ግለሰብ በከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በአለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ለ1,270 ያህል እስረኞች መገደል እንደዋነኛ ተኘያቂ ነው።[7]

የክስተቶች ቅደምተከተል[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ከፌብሩዋሪ 15-21[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ፌብሩዋሪ 15 ቀን መጀመሪያ ወደ 200 የሚጠጉ ሰልፈኞች የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ የሆነውን የፋትሂ ተርቢልን መታሰር በመቃወም በተለያዩ የቤንጋዚ ፖሊስ ጣቢያዎች ፊት አደረጉ።[8] በኋላም ከ500 እስከ 600 የሚጠጉ ሌሎች ሰልፈኞች ጋር በመቀላቀል ተቃውሞ ሲያደርጉ ፖሊስ ሰልፉን ለመበተን ባደረገው ጥረት ከሰልፈኞቹ መካከል 40 የሚሆኑት ጉዳት ደረሰባቸው።[9]

ከፌብሩዋሪ 22-28[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የቤንጋዚ ሴት ልጅ ወረቀት ይዛ
ተቃዋሚዎች በፋዲል ቅጥር ግቢ ውስጥ

የዓይን እማኞች ፌብሩዋሪ 22 ጋዳፊ ከአሜሪካ ወደ ሀገሪቱ በአውሮፕላን ቅጥር ነብሰ-ገዳዮችን አስመጥቷል ሲሉ ተናገሩ።[10] ጋዳፊም ለብጥብጡ መነሳት የውጭ መንግስታትን እና የውጭ ሃይሎችን ተጠያቂ እንደሆኑ በዚህም ተቃውሞ ሰልፈኞቹ እንዲወጡ መገደዳቸውን በዚሁ እለት አስታወቁ።[11]

ከማርች 1-4[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ማርች አንድ የአውስትራልያመከላከያ ሚኒስትር የጋዳፊ መንግስት በፍቃደኝነት ስልጣኑን እንደማይለቅ በማስገንዘብ የኃይል አማራጭ መውሰድ አስፈላጊ መሆኑን አመላክተዋል። [12]

ከማርች 5-8[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ማርች 5 ቀን ከጋዳፊ ሃይሎች ጋር በተደረገ ከባድ ውጊያ ራስ ላኑፍየተባለችዋን የሀገሪቱን ከተማ በተቃዋሚ ሃይሎች እጅ ስር ማስገባት ተችሏል።[13]

የጋዳፊ ሃይሎች ሁኔታ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

እንደ የጋዳፊ ከተማ ሲርት ባሉ ከተሞች የሚኖሩ ሰዎች በጥሩ የኑሮ ደረጃ ያሉ እና ለአገዛዙ ታማኞች ናቸው። ከእንደዚህ ያሉ ከተሞች ሃይሎችን ማስወጣት ለተቃዋሚ ሃይሎች ፈተና ሁኗል።[14]

ሞት እና አካል ጉዳት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በገለልተኛነት እስካሁን የሞቱትን እና የተጎዱትን በትክክል ለማወቅ አልተቻለም። ሆኖም አንዳንድ ምንጮች 1000 አካባቢ ሰዎች እንደሞቱ በመዘገብ አቋርጠዋል። እንደ የአለም የሰብዓዊ መብት ፌዴሬሽን መረጃ ደግሞ ከ3000 የማያንሱ ሰዎች እንደሞቱ ተዘግቧል። ነገር ግን የተቃዋሚ ኃይሎች ይህን አሃዝ በማጣጣል የሟቾች ቁጥር ከ6500 በላይ እንደሆኑ አስታውቀዋል።[15]

የተጎጅዎችንም ብዛት የሚገልፅም ቢሆን ይህ ነው የሚባል ታማኝ መረጃ የለም።

ይዩ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ማጣቀሻ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ http://www.nytimes.com/2011/02/19/world/africa/19libya.html
  2. ^ http://www.bloomberg.com/news/2011-02-23/qaddafi-is-no-mubarak-overthrow-may-mean-descent-to-chaos-.html
  3. ^ http://www.thenational.ae/thenationalconversation/industry-insights/economics/qaddafi-remains-one-of-few-constants-for-troubled-libya
  4. ^ "Archive copy". Archived from the original on 2009-05-20. በ2009-05-20 የተወሰደ.
  5. ^ http://www.guardian.co.uk/education/2007/apr/10/internationaleducationnews.tefl
  6. ^ "Archive copy". Archived from the original on 2011-03-03. በ2011-03-08 የተወሰደ.
  7. ^ http://www.edition.cnn.com/2009/WORLD/africa/11/23/libya.death/index.html
  8. ^ http://www.france24.com/en/20110216-libya-violent-protests-rock-benghazi-anti-government-gaddafi-egypt-tunisia-demonstration
  9. ^ http://www.bbc.co.uk/arabic/middleeast/2011/02/110215_libya_opposition.shtml
  10. ^ http://www.smh.com.au/world/gaddafi-clings-to-power-as-supporters-desert-20110222-1b46r.html
  11. ^ http://english.aljazeera.net/video/africa/2011/02/20112221852864320.html
  12. ^ http://news.theage.com.au/breaking-news-national/nofly-zone-still-an-option-on-libya-rudd-20110301-1bccl.html
  13. ^ http://blogs.aljazeera.net/live/africa/live-blog-libya-march-5
  14. ^ http://www.miamiherald.com/2011/02/28/2090728/a-backwater-no-more-gadhafis-hometown.html
  15. ^ http://www.sify.com/news/at-least-3-000-dead-in-libya-rights-group-news-international-ldcxkhgggdh.html