ጎጃም ክፍለ ሀገር

ከውክፔዲያ


ጎጃም በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኝና በአባይ ወንዝ ተከቦ የሚገኝ ባህር ዳርፍኖተ ሰላምን አገው ምድርን መተከልን ፓዊ ቆላ-ደጋዳሞትን፣ አቸፈርን ደብረ ማርቆስን ሞጣና ብቸና አውርጃዎች እና በነዚ ውስጥም ከ 35 በላይ ወረዳዎችን ይዞ የሚገኝ የራሱ ስርዎ መንግሥት የነበረው ከፍለ-ሃገር ነው። ጎጃም ውስጥ ኣሉ ከሚባሉት ከተሞች እንደ ባሕር ዳር ፡ ደብረ ማርቆስ ፡ፍኖተ ሰላም ፡ቡሬ ፡ኮሶበር ፡ ዳንግላ ፡ቻግኒ ፡ ኣዴት ፡ መራዊ ፡ ሞጣ፡ ቢቸና፡ ደጀን ይገኙበታል ፡፡ ጎጃም እንደነ በላይ ዘለቀ ያሉ ጀግኖች መፈጠሪያ እንዲሁም የዓባይ እና የጣና ባለቤት ናት ፡፡

ጎጃም የቅኔ ትምህርት በስፋት የሚሰጥበት ፡እንዲሁም እንደነ የፍቅር እስከ መቃብር ደራሲ ሀዲስ አለማየሁ (ዶ ር) (1902- 1996 )ኣ.ም ኣቤ ጉበኛ (1925 - 1972 )ኣ.ም ዮፍታሄ ንጉሤ(1897-1937 ) ኣ.ም የመሳሰሉ የጥበብ ሰወችን ኣፍርታለች ፡፡ ጎጃም በጤፍ አምራችነት ከታወቁት የኢትዮጵያ ክልሎች ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል። በተለይ የአዴት ጤፍ በባህር ዳር ጎንደር ደሴ እና መቀሌ ነዋሪዎች ዘንድ በስፋት የታወቀ እና ተወዳጅም ነው። እንዲሁም በምስራቅ ጎጃም እነብሴ ሞጣ ዙሪያ ወይንውሀ እና ጎንቻ ሲሶ ግንደወይን ዙሪያ የሚመረተው ጤፍ የአዲስ አበባን ህዝብ ገትሮ እንደያዘ ይነገራል።[[ቡሬ]] ዙሪያ የሚበቅለው በርበሬ በቆሎ ደግሞ የመላው የኢቲዮጵያን ህዝብ ገትሮ እንደያዘም ይነገርለታል፡፡ በነገራችን ላይ ቡሬ ዙሪያ ይህንን ብቻ አይደለም የሚያበቅል እንደ ጤፍ፣ሽንብራ፣ቦለቄ፣ዳጉሳ፣መጥቀስ ሆነብን እንጂ የማይበቅል ነገር የለም፡፡በዋናነትም ከ ቡሬ ዙሪያ ወረዳ [[ገዳም ልጃሞር]] ቀበሌ ይህንን በማምረት ይጠቀሳል፡፡ ጎጃም ሌሎች እንደ ገብስ ስንዴ በቆሎ ባቄላ አተር ወዘተ የሰብል አይነቶችን በማምረትም ይታወቃል። ጎጃም የአባይ እና ሌሎች የበርካታ ወንዞች መነሻ ነው ።ጮቄ ተራራ በዚሁ ክፍለ ሃገር ይገኛል።ጎጃም በኣሁኑ ጊዜ ማለትም ኣገራችን የፌደራሊዝም ስርኣት ከተከተለች ወዲህ ከኣራት ኣስተዳደር ዞን ተከፍሏል ።ሥወስቱ ማለትም አዊ፣ ምዕራብ እና ምስራቅ ጎጃም በአማራ ክልል ሲገኙ መተከል ቤሻንጉል ጉምዝ ክልል ተካቷል ።

ምዕራብ ጐጃም ዞን §የዞኑ ዋና ከተማ፡- ፍኖተ ሰላም

                                            §የወረዳዎች ብዛት፡- 16
                                              §የከተማ አስተዳደሮች ብዛት፡- 6
                                                 oባህር ዳር 
                                                   oፍኖተ ሰላም
                                                    oመርዓዊ
                                                   oቡሬ
                                                   oደንበ ጫ  
                                                        o   አዴት
                                                      
                                                           §የቀበሌዎች ብዛት፡- 370
                                                               oየገጠር፡-328
                                                                    oየከተማ፡-42
                                                     §በዞኑ ውስጥ የሚገኝ ህዝብ ብዛት፡- 2714017
                                                              ወንድ 1 364 143
                                                                                 ሴት 1 349 874


የወረዳው ስም የወረዳው ዋና ከተማ


1 ሜጫ መርዓዊ

2ደምበጫ ደምበጫ

3ቡሬ ዙሪያ ቡሬ

4ወንበርማ ሺንዲ

5ጃቢ ጣህናን ፍኖተ ሠላም

6ባህር ዳር ዙሪያ ባህር ዳር

7ደጋ ዳሞት ፈረስ ቤት

8ሰከላ ግሽ ዓባይ

9ቋሪት ገበዘ ማርያም

10ሰሜን አቸፈር ቢን

11ደቡብ አቸፈር ዱር ቤቴ

12ይልማና ዴንሳ አዴት

13ጐንጅ ቆለላ አዲስ አለም

አዊ  ዞን                §የዞኑ ዋና ከተማ፡- እንጅባራ 
                                                  §የዞኑ ዋና ከተማ ከክልሉ ዋና ከተማ ያለው ርቀት-122 ኪ.ሜ
                                                                                                                              


                                                      §የወረዳዎች ብዛት፡- 7
                                                     §የከተማ አስተዳደሮች ብዛት፡- 3
                                                            oዳንግላ
                                                           oእንጅባራ
                                                           oቻግኒ
                                                      §የቀበሌዎች ብዛት፡- 201
                                                             oየገጠር፡- 180
                                                        oየከተማ፡- 21
                                                 §በዞኑ ውስጥ የሚገኝ ህዝብ ብዛት፡- 1058 289
                                                     oወንድ916015
                                                    oሴት142274
      


የወረዳው ስም የወረዳው ዋና ከተማ

1አንካሻ ጓጉሣ አገው ግምጃ ቤት

2ባንጃ ሽኩዳድ እንጅባራ

3ጓጉሣ ሽኩዳድ ቲሊሊ

4ፋግታ ለኮማ አዲስ ቅዳም

5ዳንግላ ዳንግላ

6ጃዊ ፈንድቃ

7ጓንጓ ቻግኒ


ምስራቅ ጐጃም ዞን

 §የዞኑ ዋና ከተማ፡- ደብረ ማርቆስ
    §የዞኑ ዋና ከተማ ከክልሉ ዋና ከተማ ያለው ርቀት፡-
              249 ኪ.ሜ
       §የወረዳዎች ብዛት፡- 16
      §የከተማ አስተዳደሮች ብዛት ፡- 4
 oደብረ ማርቆ
oሞጣ
   oቢቸና
    oደጀን
 §የቀበሌዎች ብዛት፡- 424
   oየገጠር፡- 388
    oየከተማ፡- 36
  §በዞኑ ውስጥ የሚገኝ ህዝብ ብዛት፡- 2 152 671
ወንድ1 066 09    ሴት1 086 577
የወረዳው ስም                                     የወረዳው ዋና ከተማ

1ባሶሊበን የጁቤ

2ማቻከል አማኑኤል

3እነማይ ቢቸና

4ደባይጥላት ግን ቁይ

5ደጀን ዙሪያ ደጀን

6እናርጅና እናውጋ ደብረ ወርቅ

7ሁለት እጁ እነሴ ሞጣ

8 ቢቡኝ

                                      ድጓፅዮን

9አዋበል ሉማሜ

10እነብሴ ሳር ምድር መርጡ ለማሪያም

11ጐዛምን ደብረ ማርቆስ

12 ስናን ረቡዕ ገበያ

13አነደድ አምበር

14ሸበል በረንታ የዕድ ውኃ

15ጐንቻሲሶ እነብሴ ግንደ ወይን

16ደብረ ኤልያስ ደብረ ኤልያስ

17 ሰዴ

                 ሰዴ 


1.  http://www.amhara.gov.et/web/communcation-affairs-office/information-desk?p_p_id=56_INSTANCE_o5RZ&p_p_lifecycle=0&p_p_state=normal&p_p_mode=view&p_p_col_id=column-2&p_p_col_count=1&page=8

2. «Bibliography of Ethiopian Writers» ከብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻህፍት ኤጀንሲ - ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር (pdf)


#ስዩም ይዘንጋው ድንቁ (talk) 14:27, 23 ጁላይ 2019 (UTC)