ማርክሲስም-ሌኒኒስም

ከውክፔዲያ

ማርክሲስም-ሌኒኒስም በተለይ በካርል ማርክስና በቭላዲሚር ሌኒን ትምህርት የተመሠረተ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለም ነው።

ማርክሲስም-ሌኒኒስም የአንዳንድ መንግሥት ፍልስፍና በመሆኑ፣ በሃይማኖት ፈንታ እንደ የመንግሥት ሃይማኖት ያህል ያለ ሚና አጫውቷል።

በአሁኑ ሰዓት (2010 ዓም) ማርክሲስት ወይም ኰሙኒስት የሆኑት አገራት

በአሁኑ ሰዓት በይፋ የማርክሲስት-ሌኒኒስት መንግሥት ያላቸው አገራት የሚከተሉ ናቸው፦

ርስት ሁሉ የመንግሥት መሆኑ እንጂ የግል ርስት አለመኖሩ የሚገኝበት ሁናቴ የጀርመን ፋላስፋ የካርል ማርክስ ፍልስፍና ውጤት ነው። በተጨማሪ ማርክስ የሃይማኖት ወዳጅ ባለመሆኑ መጠን፣ ባለፈው ጊዜ በማርክሲስም-ሌኒኒስም በተገዙት አያሌ አገራት ውስጥ የሃይማኖት ወይም የኅሊና ነጻነት አልተገኘም።

በካርል ማርክስም ፍልስፍና ዘንድ ማንም ሕዝብ እንዳይበልጽጉ መቆጣጠር የመንግሥት ኃላፊነት ነው፣ ስለዚህ «ለሴ ፈር» ከ«ካፒታሊዝም» ጽንሰ ሀሣብ ጋር ይዘመዳል።

በቬትናም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በቻይና[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቻይና ከ1941 ዓም ጀምሮ ማርክሲስት ሲሆን ርዕዮተ አለሙ በይፋ «የማው ፀ-ቶንግ ሃሣብ» (ማዊስም) ነበር። በ1970 ዓም ወደ «ሶሻሊዝም ከቻይናዊ ጸባይ ጋር» ተቀየረ። በተጨማሪ «ሕዝብ እንዳይበልጽጉ» የሚለውን የማርክስ ጽንሰ ሀሣብ ትተዋል። የቻይና መሪ ደንግ ሥያውፒንግ በ1976 ዓም እንዳለ፣ «ሶሻሊስም ማለት ደህነትን ማጥፋት ማለት ነው።»

በኩባ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በላዎስ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ስሜን ኮርያ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ባለፈው ጊዜ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በኰሙኒስም ጫፍ (1971-1976 ዓም) ማርክሲስት የነበሩት አገራት

የካርል ማርክስና የሌኒን ርዕዮተ ዓለም ቀድሞ ባለፈው ክፍለ ዘመን በበርካታ አገራት ተስፋፍቶ ነበር። ይህም ሁልጊዜ በአብዮትና በብሔራዊ ጦርነት ነበር።

በኢትዮጵያ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የኢትዮጵያ መንግሥት በደርግ ዘመን (1966-1983 ዓም) በይፋ ማርክሲስት-ሌኒኒስት / ኰሙኒስት ነበረ።

ኢሕአዴግ መንግሥት (1983-2012 ዓም) ይፋዊ ርዕዮተ ዓለም «አብዮታዊ ዴሞክራሲ» ደግሞ በከፊል ከማርክሲስም-ሌኒኒስም የተደረጀ ሲሆን አንዳንድ የማርክስና በተለይም የሌኒን ተጽእኖዎች ቀርተው ነበር፤ ነገር ግን ከ1983 ዓም ጀምሮ በይፋ ርዕዮተ አለሙ ማርክሲስም / ኰሙኒስም አልነበረም። ከ2012 ዓም ጀምሮ ግን የአሁኑ መንግሥት ርዕዮተ አለም ለብልጽግና መደመር ነው።

[[መደብ:ሶሺያሊዝም