ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/መስከረም 11
- ፲፮፻፳፭ ዓ/ም - በዙፋን ስማቸው "መልአክ ሰገድ" የሚባሉት ዓፄ ሱስኒዩስ በጽኑ ደዌ ታመው በዕለተ ዐርብ ሞቱ፤ አዘዞ ላይ ተቀበሩ።
- ፲፯፻፹፭ ዓ/ም በፈረንሲስ የዘውድ ስርዓት ተሽሮ አገሪቱ ሪፑብሊክ ሆነች።
- ፲፱፻፪ ዓ/ም - የጋናው የመጀመሪያው ጠቅላይ ሚኒስትር እና የመጀመሪያው ፕሬዚደንት ክዋሜ ንክሩማ በዚህ ዕለት ተወለዱ።
- ፲፱፻፵ ዓ.ም - የክቡር ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ አጽም በስደት ዘመን አርፈው ከተቀበሩበት ከእንግሊዝ አገር ወደ ውድ አገራቸው ኢትዮጵያ ተመልሶ በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ተቀበረ።
- ፲፱፻፶፫ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት የሥራ ሚኒስትር ከአሜሪካ ጉዟቸው ሲመለሱ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁለት ቦይንግ ፯መቶ፳-ቢ (Boeing 720B) ጄት አውሮፕላኖች መግዣ እና ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የሚውል ብድር ከ ኤክሲም ባንክ (Export Import Bank) ጋር የስምምነት ውል መፈራረማቸውን ይፋ አደርጉ።
- ፳፻፪ ዓ/ም በምዕራብ ጐጃም የአንድነት ቅርንጫፍ ቢሮ አስተባባሪዎች ላይ ድብደባ ተፈጸመ