Jump to content

ዲምቱ

ከውክፔዲያ
ዲምቱ
ከተማ
አገር  ኢትዮጵያ
ክልል ደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት
ዞን ዎላይታ
ወረዳ ድጉና ፋንጎ
ካንቲባ ኢዩኤል ሞላ
ከፍታ 1,400 ሜ.
ዲምቱ is located in ኢትዮጵያ
{{{alt}}}
ዲምቱ
የዲምቱ ፡ አቀማመጥ ፡ በኢትዮጵያ ፡ ውስጥ

6°55′ ሰሜን ኬክሮስ እና 38°07′ ምሥራቅ ኬንትሮስ


ዲምቱ ወይም ወላይታ ዲምቱ ከተማ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት፣ በዎላይታ የሚትገኝ ከተማ አስተዳደር ናት። ከተማዋ ከዚህ ቀደም በነበረው አወቃቀር በዳሞት ወይዴ ወረዳ ስር የነበረች ቢሆንም፣ አሁን ግን በድጉና ፋንጎ ወረዳ ስር ትገኛለች።[1]

ዴቪድ ቡክሰን የተባለ ጻሓፊ፥ ዲምቱ በብላቴ ወንዝ አካባቢ የሚገኝ የገበያ ስም እንደሆነ ጽፎ ነበር።[2] አንዳንድ አፈታሪኮች እንደምጠቁሙት ከሆነ ገበያው ስያሜውን ያገኘው ከከተማዋ የሚወጣ ትንሽ ንጹህ ወንዝ ከብላቴ ወንዝ ጋር በሚገናኙበት ገበያው ይቆም ስለነበረ ነው። ይህን መገናኘት በወላይትኛ ዳንቷ እያሉ ይጠሩትም ነበር፤ መገናኛ ማለት ነውና። ከጊዜና ከቃሉ አጠራር ዘዬ ጋር ተያይዞ የአሁኑን ስያሜ ይዞ ለከተማውም ስም ሆኖ አረፈው ይባላል። ዲምቱ በወላይታ ውስጥ ከሶዶ ቀጥሎ እጅግ ረጅም ዕድሜ ያስቆጠረች ከተማ ናት። ከተማዋ ከአዲስ አበባ በስተደቡብ ምዕራብ 333 ኪሎ ሜትር ርቃ የሚትገኝ ሲሆን፥ ከዞኑ ዋና ከተማ ሶዶ ደግሞ በ68 ኪሎ ሜትር ርቀት በስተምሥራቅ ትገኛለች። ከተማዋ በስተምሥራቅ በብላቴ ወንዝ የሚትዋሰን ሲሆን ውንዙ ከሲዳማ ክልል እና ከኦሮሚያ ክልል በተመሳሳይ ሁኔታ ያገናኛታል።

  1. ^ "Admirative Map of SNNPR". በ6 October 2020 የተወሰደ.
  2. ^ David, Buxton. David Roden Buxton. David Roden Buxton. pp. 66.