ኃይለማሪያም ደሳለኝ
| ይህ መጣጥፍ የውክፔዲያ የአቀማመጥ ልምዶችን እንዲከተል መስተካከል ይፈልጋል። |
አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በወላይታ አውራጃ በቦሎሶ ወረዳ ዱቦ በተባለ የገጠር መንደር ተወለዱ። የ1ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በአከባቢያቸው የአየርላንድ ካቶሊክ ሚሺን ባቋቋመው ት/ቤት እንደፈጸሙ የ2ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በወላይታ ሶዶ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ፈጽመው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢንጂነሪንግ ከተመረቁ በኋላ በአርባምንችህ ውኃ ተቋም አስተማሪ ሆነው እያገለገሉ ሳሉ የማስትሬት ዲግሪያቸውን በፊንላንድ ተምፔ ዩኒቨርስቲ አጠናቀው አገር ቤት በመመለስ በአርባምንጭ በአርባ ምንጭ ውኃ ቴክኖሎጂ ዲን ሆነው አገልግለዋል። ከዚያም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በም/ፕሬዚዳንት ፡ በፕሬዚዳንትና የኢሕአዴግ ጸሃፊ ሆነው አገልግለዋል።
አቶ ኃ/ማሪያም ታማኝ የኢሕአዴግ አገልጋይና እውቅ ፖለቲከኛ ከመሆናቸው በፊት በፕሮቴስታንት እምነት በጥብቅ ሃይማኖተኛነት የሚታወቁ እንዲሁም ለመናገር የማይቸኩሉ ጥሩ አዳማጭ እንደሆኑ በግል ባህሪያቸውም በጣም ዝምተኛ ባሕሪ እንደነበራቸው ይታወቃሉ። አቶ ኃ/ማሪያም በከፍተኛ ስልጣን ላይ ሆነውም በከባድ ጥበቃ ታጅበው ጎፋ ሰፈር በሚገኘው የኢትዮጵያ ሃዋሪያዊት ቤተክርስትያን እየተባለ በሚጠራው ቤ/ክርስቲያን እሑድ እሁድ አልፎ አልፎ እንደሚካፈሉና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ለመገኘት ደከመኝ ሰለቸኝ የማይሉ እንደሆኑ በቅርቡ የሚያውቆአቸው ይመሰክርሉቸዋል።
ባለቤታቸው ወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ የአከባቢያቸው የወላይታ ዞን ሲሆኑ በኢኮኖሚክስና በሥራ ሃላፊነት ሁለት የማስተርስ ዲግሪ ምሩቅ ሲሆኑ ባለቤታቸው ወደ አዲስ አበባ እስከመጡበት ድረስ የደቡብ ኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ቢሮ /የባለቤታቸው/ ልዩ አማካሪና የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ ሆነው አገልግለዋል። ወ/ሮ ሮማን ከሃይስኩል እስከ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ድሕረ ምረቃ ድረስ ከባለቤታቸው ጋር አብረዋቸው በከፍተኛ ትምሕርት የዘለቁ ከመሆናቸውም በላይ በባህሪያቸው ትሑት ሰው አክባሪና ግልጽ ተናጋሪ ናቸው። ወ/ሮ ሮማን ተስፋዬ ባሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ሰባዊ መብቶች ድርጅት በኃላፊነት ከሰሩ በህዋላ በዩ ኤን ዲ ፒ ዓለም አቀፍ መሥሪያ ቤት የሚሰሩ ሲሆን ፈጣን አሳቢና የመሰላቸውን ከመናገር ወደ ኋላ የማይሉ በመሆናቸው የባለቤታቸው የአቶ ኃይለማሪያም ድብቅ መሳሪያ እንደሆኑ ይታመናል። ወ/ሮዋ እንደ ባለቤታቸው ሁሉ ከቤተክርስቲያን አከባቢ የማይጠፉ መደበኛ የሃዋሪያት እምነት ተከታይ /ጴንጤ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል።
በጥቁር ገጽታ ደግሞ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ የሚፈረጁት የኢሕአዴግ መንግስትና የወላይታ ሕዝብ በቋንቋ ምክንያት በተፈጠረው ውዝግብ ጊዜ የ"ወጋጎዳ" ቋንቋ የወላይታ ልጆች ተገደው እንዲማሩ ጫና አርገዋል ተብለው በሌሎች የአከባቢያቸው ጎሳዎች ዘንድ አለመወደዳቸው ይነገራል። እንዲሁም በደቡብ ክልል የክልል ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩ ጊዜ በጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ትዕዛዝ የበላይ አለቃቸውና የክልሉን ፕሬዚዳንት የነበሩትን አቶ አባተ ኪሾን ከስልጣን የሚያስወግድ ደብዳቤ በገዛ እጃቸው የጻፉና በምትካቸው ራሳቸውን ተክተዋል እየተባሉ ይተቻሉ። ይሁን እንጂ በመንግሥት ሚዲያ በህዋላ እንደተነገረው አቶ አባተ ኪሾ በኢሕአዴግ ግምገማ ከስልጣን መወገዳቸው ተዘግቦአል።
በዚህም የተነሳ በጊዜው በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መስተዳድር አስተዳደራቸውና እውቅናቸው እይደበዘዘ ስለመጣ የአካ\ከባቢው ተወላጆች በተደጋጋሚ በሚያስነዋስቸው ተቃውሞች ከሥልጣናቸው ተነስተው ወዲያውኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ አማካሪ ሆነው በታላቁ ቤተመንግሥት አከባቢ ቆይተው በ2003 በ8ኛው የኢሕአዴግ ጠቅላላ ስብሰባ ላይ የቀድሞውን የአማራ ብሄራዊ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ መሪ አቶ አዲሱ አበበን በመተካት የኢሕአዴግ ምክትል ሊቀመንበር ለመሆን በቅተዋል። በተጨማሪም የደቡብ ክልላዊ መንግሥት የኢሕአዴግ ሊቀመንበር በመሆናቸው በኢሕአዴግ ታሪክ የመጀመሪያው በትጥቅ ትግል ያልተሳተፉ ሰው ያደርጋቸዋል።
በመሆኑም አቶ ኃይለማሪያም በጣም አጭር ጊዜ ውስጥ ከመለስ ዜናዊ ቀጥሎ ያለውን 2ኛውን ትልቅ ቦታ ባጭር ጊዜ ውስጥ ከመቆናጠጣቸውም በላይ የኢትዮጵያ 24ኛው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነዋል።
እንዲሁም፡ ከሶስት ትላልቅ ብሄሮች ውጪ ማለትም አማራ፡ ትግሬ ፡ ኦሮሞ፡ ብሄር አባል ያልሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የደቡብ ተወላጅና ከኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ውጪ ፕሮተስታንት የሆነ ግለሰብ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው እ.ኤ.አ ኦገስት 22 /2012 ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ አቶ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ወደ ተጠባባቂ ጠ/ሚኒስትርነት ማዕረግ ከፍ ብለው ለአንድ ወር ያህል ከቆዩ በኋላ የገዢው ፓርቲ ኢሕአዴግ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ የፓርቲው ሊቀመንበርና ባለሙሉ ስም ጠ/ሚኒስትር እንዲሆኑ በመምረጣቸው እስከ 2015 ምርጫ ቀጣዩ የኢትዮጵያ መሪ በመሆን በኢትዮጵያ ታሪክ መዝገብ ላይ ስማቸውን አኑረዋል።
|
|
|
|---|---|
| ንጉሠ ነገሥት መንግሥት (1934-1966) | መኮንን እንዳልካቸው · አክሊሉ ሀብተ-ወልድ · እንዳልካቸው መኮንን · ሚካኤል እምሩ |
| ደርግ (1966-1979) | (ማዕረጉ ተሠረዘ) |
| የኢት. ሕዝባዊ ዲሞ. ሪፐብሊክ (1979-1983) | ፍቅረ ሥላሴ ወግደረስ · ሃይሉ ይመኑ* · ተስፋዬ ድንካ* |
| የኢት. ፌዴራላዊ ዲሞ. ሪፐብሊክ (1983-አሁን) | ታምራት ላይኔ* · መለስ ዜናዊ · ኃይለማርያም ደሳለኝ |
|
*ተግባራዊ
|
|
የሚከተለው አስረጅ ከአይጋ ፎረም የተወሰደ ነው
የ47 ዓመቱ አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን ቦሎሶ ሶሬ ወረዳ በአረካ ከተማ ነው የተወለዱት ። የወጣትነት ዘመናቸውንም በዚህ በተወለዱበት ሰፍራ ያሳለፉ ሲሆን ፥ በ1980 ዓመተ ምህረት የባችለር ድግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በምህንድስና አግኝተዋል ። ገና በወጣትነት ዘመናቸው የያኔውን የአርባምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የዛሬውን አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲን በመምህርነት አገልግለዋል ። በተቋሙ ቆይታቸው ባገኙት ነፃ የትምህርት እድልም ወደ ፊንላንድ በማቅናት ከታምፔሬ የቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በስነ ንፅህና ምህንድስና የማስተርስ ድግሪያቸውን ተከታትለዋል ። ከተመለሱም በኋላ የአርባ ምንጭ ውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ዲን በመሆን ለ13 ዓመታት ያገለገሉ ሲሆን ፥ በነዚህ ጊዜያት ውስጥም ከአሜሪካው አዙሳ ፓስፊክ ዩኒቨርሲቲ በድርጅት አመራር የማስተርስ ድግሪ አግኝተዋል ። አቶ ሀይለማሪያመ ደሳለኝ በ1990ዎቹ መግቢያ ላይ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ አባል በመሆን በአገሪቱ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ መሳተፍ ጀምረዋል ። የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስትን በምክትል ርእሰ መስተዳደርነት ሲያገለግሉ የነበሩት አቶ ሀይለማሪያም በ1998 ለአራት ዓመታት የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ሆነው ሰርተዋል ። በመቀጠልም አቶ ሀይለማሪያም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል በመሆን የተንቀሳቀሱ ሲሆን ፥ በምክር ቤቱ የመንግስት ጉዳዮች ተጠሪ ሚኒስትርም ነበሩ ። ከዚህ በተጓዳኝም በጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ አማካሪም ሆነው የሰሩ ሲሆን ፥ የጠቅላይ ሚኒሰትሩ የማህበራዊ ጉዳዮች ፣ የህዝብ አደረጃጀትና ተሳትፎ ልዩ አማካሪም ሆነው የሰሩባቸው ጊዜያቶች ነበሩ ።ከ2002 አገር አቀፍ መርጫ በኋላም በድጋሚ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ሆነው የተመረጡ ሲሆን ፥ በጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ካቢኒ ውስጥም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነትና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ተሹመው በማገልገል ላይ ይግኛሉ ። በፓርቲያቸው ውስጥ ባላቸው እንቀስቃሴም የኢህአዴግ አባል በሆነው ድርጅታቸው በደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ንቅናቄ / ደኢህዴን/ ሊቀመንበር በመሆን ከ10 ዓመት ለሚበልጥ ጊዜ እየሰሩ ይገኛሉ ። የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልም ሲሆኑ ፥ ከሁለት ዓመት በፊት የድርጅቱ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ምክትል ሊቀመንበር ሆነውም ተመርጠዋል ። ከወይዘሮ ሮማን ተስፋዬ ጋር ትዳር መስርተውና ሶሳት ልጆች አፈርተው እየኖሩ የሚገኙት አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ዛሬ የኢህአዴግ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል ። በፓርቲው አሰራርም መሰረት የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ያገለግላሉ