ውክፔዲያ:ታሪካዊ ማስታወሻዎች/ጥቅምት 30

ከውክፔዲያ

ጥቅምት ፴

  • ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. - የጀርመን ፖሊሶችና ወታደሮች በሙኒክ ከተማ የቢራ አዳራሽ በናዚዎች ቅስቀሳ የተጀመረውን ያልተሳካ መፈንቅለ መንግሥት ደመሰሱ።
  • ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. - በጀርመን እና በአውስትሪያ አገሮች ናዚዎች የይሁዳውያን መቅደሳትና መደብሮችን በዝብዘው በእሳት አጋዩ። ይሄም ታሪካዊ ምዕራፍ “Kristallnacht” የመስተዋት መስበሪያ ምሽት በመባል ይታወቃል።
  • ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. - በሰሜን ምሥራቅ አሜሪካ ግዛቶችና በካናዳ ለአሥራ ሦስት ሰዐት ተኩል ያህል ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ ስምንት መቶ ሺህ ሰዎች በኒው ዮርክ ውስጠ መሬት ባቡር ላይ ተደንቅረው አመሹ። ችግሩ በግምት የሃያ አምስት ሚሊዮን ሕዝቦችን ኑሮ አዛብቷል።