መጥምቁ ዮሐንስ

ከውክፔዲያ
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ

እየሱስ ክርስቶስን ሲያጠምቅ
ለክርስቶስ መንገድ አዘጋጅ
ስም ዮሐንስ
የተወለደው ፮ ወር ከክርስቶስ ልደት በፊት በገሊላ ናዝሬት
የአባት ስም ዘካሪያስ
የእናት ስም ኤልሳቤት
የሚታወቀው በበርሀ መኖሩ፣ከክርስቶስ በፊት መንግሥተ ሰማይ ቀርባለች ንስሀ ግቡ እያለ የአይሁድን ሕዝብ በማስተማሩ
ያረፈው በእስር ቤት እያለ በንጉሥ ትዕዛዝ አንገቱን ተከልቶ
የሚከበረው በክርስትና እምነት ተከታይዎች በሙሉ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
ንግሥ ያረፈበት መስከረም ፪ የተወለደበት ነሐሴ ፴


ዮሐንስ በ1500 ዓም ያህል በጀርመን እንደ ተሳለ

መጥምቁ ዮሐንስወንጌላት እንደ ተገለጸ በኢየሱስ ወቅት በይሁዳ የተመላለሰ ሰባኪና ክርስቶስን "የዓለምን ኃጢያት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ " እያለ ያጠመቀ ፣ ክርስቶስ "ሴቶች ከወለድዋቸው እሱን የሚስተካከለው የለም" ብሎ የተናገረለት ፃድቅ ሰው ነው ። በክርስትና፣ እንዲሁም በእስልምና፣ በባኃኢ እምነት እና በማንዳይስም እንደ ነቢይ ይቆጠራል።

አባቱ ዘካርያስና እናቱ ኤልሳቤት ነበሩ። በአዲስ ኪዳን መሠረት፣ ዮሐንስ በይሁዳ ምድረ በዳ ሲዛወር የግመል ጽጉር ልብስና የቆዳ ቀብቶ ለብሶ መብሉ አንበጣማር ነበረ። ንስሐ መግባት እና ለመሲኅ መንግሥት መዘጋጀት ይሰብክ ነበር። ብዙ ሕዝብ ከኢየሩሳሌምና ከይሁዳ ሄደው ሰምተው በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቁ። የፈሪሳውያንሰዱቃውያን ወገኖች ግን ገሰጻቸው። የአይሁድ ዘር መሆን ወይም ከአብርሃም መወለድ ብቻ ለእግዚአብሔር መንግሥት ለመዳን በቂ እንዳልነበረ ነገራቸው (ማቴ.፫፣ ሉቃ ፫)።

በተለይ የሉቃስ ወንጌል ላይ ፫ ከተዘረዘሩት ትምህርቶቹ፦

  • ለሕዝቡ፦ «ሁለት ልብስ ያለው ለሌለው ያካፍል፣ ምግብም ያለው እንዲህ ያድርግ»
  • ለቀራጮች፦ «ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ»
  • ለጭፍሮች (ለወታደሮች)፦ «በማንም ግፍ አትሥሩ፣ ማንንም በሐሰት አትክሰሱ፣ ደመወዛችሁም ይብቃችሁ።»

ስለ ዮሐንስ ቅድስና አንዳንድ ሰዎች መሲህ እራሱ እንደ ነበር ያስቡ ነበር፤ ዮሐንስ ግን ከኔ ይልቅ የሆነ ሊመጣ ነው ብሎ ነበየ።

ኢየሱስ ደግሞ ወደ ዮሐንስ ለጥምቀት ሲቀርብ፣ የእግዚአብሔር ድምጽና መንፈስ እንደ ዋኖስ ወርዶ ይህ ልጄ ነው አለ። ዮሐንስ በመንፈሱ ኢየሱስ መሲኅ እንደ ነበር ዓወቀ።

በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት እየሠራ ዮሐንስ ተከታዮቹን ወደ ኢየሱስ ልኮ የምንጠብቀው መሲኅ ይህ ነው ወይ ብለው ጠየቁት። ተዓምራት መሥራቴን ንገረው ብሎ መለሳቸው። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ ስለ ዮሐንስ ገልጾ በትንቢተ ሚልክያስ እንደ ተነበየ የሚመጣው ኤልያስ ነው በማለት አስተማረ (ማቴ. ፲፩)። ሆኖም ዮሐንስ እራሱ ኤልያስ አይደለሁም ስላለ (ዮሐ ፩)፣ ሉቃስ ፩ እንደ ጻፈው በኤልያስ ኃይልና መንፈስ እንደ ተወለደ እንጂ የኤልያስ ነፍስ ትስብዕት ተመልሶ መሆኑ አይታመንም።

ዮሐንስ ደግሞ የሮሜ መንግሥት ደንበኛ-ንጉሥ ሄሮድያስን ገሰጸው። ሄሮድያስ የወንድሙን ሚስት ማግባቱ በሕገ ሙሴ ዘንድ ሕገ ወጥ መሆኑን አሳወቀው። ስለዚህ መቀያየም ሄሮድያስ ዮሐንስን በወህኒ አሠረው በኋላም በሴት ልጁ በሄሮድያዳ ምክር ራሱን አስቆረጠው።

ከዚያ ትንሽ ጊዜም በኋላ ኢየሱስ ተዓምራት ስለ መሥራቱ ዝነኛ ሲሆን፣ ሄሮድያስ እንደ መሰለው ዮሐንስ በትንሳኤ ተመልሷል ብሎ ገመተ። ሌሎችም ኢየሱስ እንደ ኤልያስ በትንሳኤ ተመልሷል ብለው ያስቡ ነበር (ማር. ፮፣ ማቴ. ፲፬)።

የዮሐንስ ተከታዮች ብዙ ጊዜ ይጾሙ ነበር (ሉቃ. ፭)፤ ብዙዎቹም በኋላ ከአፖሎስ ጋር የኢየሱስ ተከታዮች ሆኑ (የሐዋርያት ሥራ ፲፰፣ ፲፱)። ኤብዮናውያን የተባለው ወገን አትክልት ብቻ ሲበሉ ዮሐንስ ስንኳ አንበጣ አልበላም ብለው ያምኑ ነበር፤ የኤብዮናውያን ወንጌል እንዳለው የበላው «የማር እንጐቻ» ነበር።

የቅሌምንጦስ ስነ ጽሑፍ እንደሚተርከው፣ ከዮሐንስ ተከታዮች ሌሎች ግን ወደ ስምዖን ጠንቋዩ ወገን ተዛወሩ።

ከድረገጾቹ አንዱን ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ

ዮሴፉስ[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

የአይሁድ ታሪክ ጸሐፊ ፍላቪዩስ ዮሴፉስ (70 ዓም ግ.) እንዳለን፣ ሄሮድያስ የተከታዮቹን ብዛት ፈርቶ ዮሐንስን በወህኒ ስላስገደለው፣ ከዚህ እርጉም የተነሣ ከ፮ ዓመታት በኋላ በ28 ዓም የሄሮድያስ ሥራዊት በውግያ ተሸነፈ።

ማንዳይስም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ማንዳይስም በኢራቅ የተገኘ አነስተኛ የኖስቲሲስም አይነት እምነት ሲሆን፣ ዮሐንስ እንደ ዋና ነቢያቸው እና መሲኃቸው ይቆጥሩታል፤ ኢየሱስን ግን አይቀበሉም።

እስልምና[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ቁራን ዘንድ ስሙ በአረብኛ «የህየ» ሲባል ጽድቅ ነቢይና የኢየሱስ ደቀ መዝሙር ይባላል። በሃዲስ ልማዶች መሠረት ደግሞ በ613 ዓም ነቢዩ ሙሐመድ ወደ ሰማይ ተጉዞ በዚያ የህየንና ኢየሱስን እንዳገኛቸው ይታመናል።

ሞርሞኒስም[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ሞርሞኒስም ዘንድ ዮሐንስ በትንሳኤ ለመሥራቹ ለጆሰፍ ስሚስ1821 ዓም በፔንስልቫኒያ ታየው።

ባኃኢ እምነት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በባኃኢ እምነት የእምነቱ መሥራች የባኃኡላህ ቀዳሚ ባብ (1812-1842 ዓም.) በነቢዩ ዮሐንስ እንዲሁም በኤልያስ መንፈስ እንደ ተላከ ይታመናል።

: