ጥቅምት ፳፭

ከውክፔዲያ
(ከጥቅምት 25 የተዛወረ)

ጥቅምት ፳፭ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፶፭ኛ ቀን ነው። ከዚህ ቀን በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፫፻፲፩ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፫፻፲ ቀናት ይቀራሉ።

ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • ፲፰፻፹፪ ዓ.ም - ዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ በ እንጦጦ “መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም” ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሊቀ ጳጳሱ በአቡነ ማቴዎስ እጅ ቅብዓ መንግሥት ተቀብተው የንጉሠ ነገሥት ዘውድ ጫኑ። [1]
  • ፲፱፻ ዓ/ም - በነሐሴ ወር ፲፰፻፺፰ ዓ/ም ሥራውን የጀመረው በአዲስ አበባ እቴጌ ሆተል ተብሎ የተሠየመው የመጀመሪያው ሆቴል በዚህ ዕለት በአዲስ አበባ የነበሩ ዲፕሎማቶችና የውጭ አገር ዜጋዎች በተገኙበት በዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ተመርቆ ተከፈተ። የመጀመሪያው ሥራ አስኪያጅም ፍሬደሪክ ሐል ነበር። በኋላ ግን አቶ ዘለቃ አጋርደው ተሾሙ።[2]
  • ፲፱፻፸፪ ዓ.ም. - የኢራን ሻህ ሬዛ ፓህላቪ በሕዝብ ፍንቀላ ከሥልጣን ከወረዱ በኋላ አብዮታዊ ተማሪዎች የአሜሪካን ኤምባሲ በኃይል ደምሥሠው ገብተው ዘጠና የአሜሪካ ዜጎችን በቁጥጥራቸው ስር አዋሉ።

ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • ፲፱፻፹፰ ዓ.ም - የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስቴር ይስሐቅ ራቢን በነፍሰ-ገዳይ እጅ ሕይወታቸውን አጡ።

ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ ኅሩይ ወልደሥላሴ (ብላቴን ጌታ)፣ "የኢትዮጵያ ታሪክ ከንግሥተ ሳባ እስከ ታላቁ የአድዋ ድል"፣ 1999
  2. ^ ጳውሎስ ኞኞ፣ "አጤ ምኒልክ"፣ገጽ ፫፻፳፱ ሦስተኛ ዕትም (፲፱፻፺፱ ዓ/ም)

http://news.bbc.co.uk/onthisday/hi/dates/stories/november/4

http://www.nytimes.com/learning/general/onthisday/20081101.html

http://www.nytimes.com/learning/general/onthisday/20081104.html

http://www.history.co.uk/this-day-in-history/November/04/also.html Archived ኖቬምበር 6, 2009 at the Wayback Machine