ከ«የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
አንድ ለውጥ 363044 ከ196.188.241.66 (ውይይት) ገለበጠ Tag: Undo |
No edit summary Tags: Reverted በንፋስ ስልክ -የሞባይል ድረገፅ |
||
መስመር፡ 2፦ | መስመር፡ 2፦ | ||
| ጦርነት_ስም = የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት |
| ጦርነት_ስም = የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት |
||
| ክፍል = |
| ክፍል = |
||
| ስዕል = World War |
| ስዕል = World War gidmcn1.gif |
||
| የስዕል_መግለጫ = የጦርነቱ ታሪክ በካርታ |
| የስዕል_መግለጫ = የጦርነቱ ታሪክ በካርታ |
||
| ቀን = ከሐምሌ ፳፩ ቀን ፲፱፻፮ እስከ ኅዳር ፪ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓ.ም. <br /> የ[[ቬርሳይ ውል]] የተፈረመው ሰኔ ፳፩ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓ.ም. |
| ቀን = ከሐምሌ ፳፩ ቀን ፲፱፻፮ እስከ ኅዳር ፪ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓ.ም. <br /> የ[[ቬርሳይ ውል]] የተፈረመው ሰኔ ፳፩ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓ.ም. |
እትም በ04:16, 9 ኦገስት 2023
የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት | |||||||
---|---|---|---|---|---|---|---|
ስዕል:World War gidmcn1.gif የጦርነቱ ታሪክ በካርታ | |||||||
| |||||||
ወገኖች | |||||||
አላይድ ሀገራት ፈረንሣይ |
መካከለኛው ኃያላት /central powers/
የጀርመን መንግሥት | ||||||
መሪዎች | |||||||
ሬይመንድ ፑዋንካሬ ጊዮርጊስ ክሌሜንኮ |
ዊልሄልም ፪ኛ ፖል ቮን ሂንደንበርግ | ||||||
አቅም | |||||||
12,000,000 8,841,541[1] |
13,250,000 | ||||||
የደረሰው ጉዳት | |||||||
የሞቱ፦ 5,525,000 የቆሰሉ፦ 12,831,500 የጠፉ፦ 4,121,000 ጠቅላላ፦ 22,477,500 |
የሞቱ፦ 4,386,000 የቆሰሉ፦ 8,388,000 የጠፉ፦ 3,629,000 ጠቅላላ፦ 16,403,000 |
የመጀመሪያው የዓለም ጦርነት በአውሮፓ አገሮች መኻል ከ ፲፱፻፮ ዓ/ም እስከ ፲፱፻፲፩ ዓ/ም መግቢያ፣ ለአራት ዓመታት የተካሄደ ጦርነት ነው። ይኼ ግጭት የዘመኑ ኃያላን አገራት በሁለት ተቃራኒ ወገን ተሰልፈው ያካሄዱት ግብግብ ሲሆን እስከ ሰባ ሚሊዮን ታጣቂዎች የተካፈሉበትና እስከ አስራ አምስት ሚሊዮን አውሮፓውያን ሕይወታቸውን ያጡበት ትልቅ ጦርነት ነው።
መነሻ
ለጦርነቱ ቅስቀሳ ብዙ ምክንያቶች በታሪክ ምሑራን ይጠቀሳሉ። ዓቢይ ከሚባሉት ነገሮች ግን የወቅቱ ኃያላን መንግሥታት የውጭ ጉዳይ ተልዕኮዎች ሲሆኑ የክብሪቱ መጫሪያ ምክንያት ግን የ አውስትሪያ እና ሁንጋሪያው ዘውድ አልጋወራሽ፣ አውስትሪያዊው አርች ዱክ ፍራንዝ ፈርዲናንድ በዩጎዝላቪያዊ ነፍሰ ገዳይ እጅ ሰኔ ፳፩ ቀን ፲፱፻፮ ዓ/ም መገደል ነው። የሳቸውን መገደል ምክንያት በማድረግ የ አውስትሪያ እና ሁንጋሪያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥት ለ ሰርቢያ ንጉዛት ሊያሟሉት የማይችሉትን፣ አስር ነጥብ ያዘለ የእላፊ ገደብ (ultimatum) ማስጠንቀቂያ ይሰጡና ገደቡ ሲያልፍ ቅድሚያውን እንደወጠኑት በሰርቢያ ላይ የጦር አዋጅ አወጁ። ይሄም የታቀደ ትንኮሳ ከአስር ዓመታት በፊት ተመሥርተው የነበሩትን ብዙ የትብብር ውሎችን የሚያንቀሳቅስ ሁኔታ ስለነበረ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ሁሉንም ኃያላን መንግሥታት ጦርነቱ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ አስገደዳቸው። እያንዳንዳቸው ደግሞ በዓለም ዙሪያ የሚያስተዳድሯቸው ቅኝ ግዛቶች ስለነበሯቸው እነዚህንም ቅኝ ግዛቶች በዚሁ ግብግብ ተሳታፊ አደረጋቸው።
የጦርነቱ መግቢያ
የጦርነቱ ትርዒት የተከፈተው የአውስትሪያ እና ሁንጋሪያ ሠራዊት ሰርቢያን ሲወሩ አጋራቸው የአለማኛ መንግሥት ደግሞ ቤልጂግን፣ ሉክሳምቡርግን እና ፈረንሳይን ወረረ። በተቃራኒው ደግሞ የሩሲያ ሠራዊት የምዕራብ አለማኛን ግዛት ይወራሉ። የኦቶማን ንጉሠ ነገሥት ሠራዊት ደግሞ ወዲያው ጦርነቱ ውስጥ ሲገባ በቀጣዩ ዓመት ኢጣልያና ቡልጋሪያ ተከትለው ገቡበት። የሩሲያ ሠራዊት ለሦስት ዓመታት ከተዋጋ በኋላ የጥቅምት አብዮት በ፲፱፻፲ ዓ/ም ሲፈነዳ ከዚህ ታላቅ ጦርነት ወጣ።
መጨረሻው
የአለማኛ ሠራዊት በ፲፱፻፻፲ ዓ/ም የምዕራብ የጦርነቱን ግንባር ማጥቃት ከጀመሩ በኋላ የአሜሪካ ሠራዊት ከአጋሮቹ ጋር ሲሰለፍ፣ የምዕራብ አገሮች ቡድን አለማኞቹን በማጥቃት እያቸነፏቸው መጡ። መጨረሻ ላይ ተሸናፊው የአለማኛ ሠራዊት መሸነፉን አምኖ ኅዳር ፩ ቀን ፲፱፻፲፩ ዓ/ም የእጅ መስጫ ውል ሲፈርም፤ ሰኔ ፲፱ ቀን ፲፱፻፮ ዓ/ም የተለኮሰው ጦርነት አከተመ። አብሮትም የአውስትሪያ እና ሁንጋሪያ ግዛት፣ የኦቶማን ግዛት ሲጠፉ የጀርመን እና የሩሲያ ኃያልነት በፖለቲካም ሆነ በጉልበት ተደምስሰው የአራቱንም ቅኝ ግዛቶች አሸናፊዎቹ እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ተከፋፈሏቸው።
የአንደኛው ዓለም ጦርነት ተስቦ
የቀድሞ ኃያላን መንግሥታትትን ውድመት ያስከተለ ክስተት ከመሆኑም ሌላ፤ በመካከለኛ አውሮፓ የብዙ ትናንሽ ሉዓላዊ አገሮችን መወለድ፤ የዓለም መንግሥታት ማኅበርን መቋቋሚያ መንስዔ፤ ከሁሉም በላይ ግን በአውሮፓ አኅጉር የብሔራዊነትን መንፈስ የቀሰቀሰና የጀርመን ሽንፈትን ያረጋገጠው የቬርሳይ ውል (Treaty of Versailles) በጀርመኖች ላይ ያስከተለው የጭቆና ስሜት አገራችን ኢትዮጵያ በ፲፱፻፳፰ ዓ/ም በፋሽስት ኢጣልያ በግፍ ስትወረር የተለኮሰውን የሁለተኛው የዓለም ጦርነት መነሻ ምክንያት መሆኑ ነው።