ጥቅምት ፳፬

ከውክፔዲያ

ጥቅምት ፳፬ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፶፬ኛ ቀን ነው። ከዚህ ቀን በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፫፻፲፪ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፫፻፲፩ ቀናት ይቀራሉ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዕለት በየወሩ በ እቲሳ ቡልጋ የተወለዱት የኢትዮጵያዊው የቅዱስ አቡነ ተክለ ኃይማኖት መታሰቢያ ቀን አድርጋ ታከብረዋለች።

ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

፲፬፻፹፮ ዓ.ም የጄኖአው ተወላጅ ክሪስቶፎሮ ኮሎምቦ (Christopher Colombus) የአትላንቲክ ውቅያኖስን ከአውሮፓ ወደምዕራብ የማቋረጥ ሁለተኛው ጉዞው፤ ለመጀመሪያ ጊዜ የዶሚኒካ ደሴትን አገኘ።

፲፰፻፹፮ ዓ.ም. ፓናማአሜሪካ ማበረታታት ተነስታ ከኮሎምቢያ ቅኝ ግዛትነት ነጻነቷን አወጀች። የአሜሪካው ፕሬዚደንት ቴዎድሮስ ሩዝቬልትፓናማ ቦይን ለመቅደድ ፈልገው ኮሎምቢያ ለዚሁ ሥራ መከፈል የፈለገችውን ዋጋ ስላልተስማሙበት ፓናማ ነጻ አገር እንድትሆን ጥረታቸው ተሳካ።

፲፱፻፶ሶቪዬት ሕብረት በጠፈር የመጀመሪያውን እንስሳ፤ ላይካ የተባለውን ውሻ፤ በስፑትኒክ ሁለተኛ መንኲራኩር ወደጠፈር ተኮሰች።

፲፱፻፷፫ ዓ/ም ሰባ ከመቶውን የአዲስ አበባ ውሐ የሚያስተናግደው የለገዳዲ የውሐ ግድብ ተመርቆ አገልግሎቱን ጀመረ።

፲፱፻፺፯ ዓ.ም. የአሜሪካው ፕሬዚደንት ጆርጅ ወከር ቡሽ ለሁለተኛና ለመጨረሻ ጊዜ ተመረጡ።

ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

፲፱፻፹፱ ዓ.ም የመካከለኛው አፍሪካ ሪፑብሊክ አገርን በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከያዙ በኋላ ራሳቸውን በዘውድ ያነገሡት ዣን ቢዴል ቦካሳ በተወለዱ በሰባ አምስት ዓመታቸው አረፉ።

ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]


የኢትዮጵያ ወራት
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ