ሚያዝያ ፭

ከውክፔዲያ
(ከሚያዝያ 5 የተዛወረ)

ሚያዝያ ፭፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፲፭ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፲ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፶፩ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፶ ቀናት ይቀራሉ።

በዚህ ዕለት ኢትዮጵያዊው ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ስለተወለደ ከድጓው ድርሰቱ የተወሰደ ቅንጣቢ፦

መፀው/መከር

"በጊዜሁ ኀለፈ ክረምት ቆመ በረከት ናሁ ጸገዩ ጽጌያት" (ሲተረጐም) ክረምቱ በጊዜው አለፈ አሁን የበረከት ጊዜ ይሆናል አበባዎችም ያብባሉ፡፡

ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • ፲፭፻፳፬ ዓ/ም - አይፈርስ አምባ በተባለ ስፍራ ከግራኝ መሀመድ ጋር በተደረገ ጦርነት ራስ እስላም ሰገድ፣ ተክለ ኢየሱስ እና ብዙ መኳንንት ሞቱ።
  • ፲፱፻፵፫ ዓ.ም. ፦ ፪ ሺህ ፻፷፰ ወታደር የያዘው የኢትዮጵያ የክቡር ዘበኛ ሠራዊት የሻለቃ ጦር ወደ ኮርያ ዘመተ፡፡ ከዘማቾቹ ማህል አንዱ የነበረው ‘የክራሩ ጌታ’ የ፶ ዐለቃ ካሣ ተሰማ "እልም አለ ባቡሩ" በሚለው ዘፈኑ ይሄንን ዕለት አወድሶታል።
  • ፲፱፻፶፮ ዓ/ም - አንጋፋው የፊልም ተዋናይ ሲድኒ ፗቲዬር ‘ሊሊስ ኦፍ ዘ ፊልድ’ (Lilies of the Field) በተባለው ፊልሙ የ’ኦስካር’ ሽልማት ሲቀበል የመጀመሪያው ጥቁር አሜሪካዊ ነው።

ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • (እንግሊዝኛ) P.R.O., FCO 371/1660 ANNUAL REVIEW FOR ETHIOPIA FOR 1973


የኢትዮጵያ ወራት
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ