ሚያዝያ ፮

ከውክፔዲያ
(ከሚያዝያ 6 የተዛወረ)

ሚያዝያ ፮፣ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፪፻፲፮ኛው ዕለት ሲሆን፤ የፀደይ (በልግ)ወቅት ፲፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ በዘመነ ሉቃስ ፻፶ ዕለታት ሲቀሩ በዘመነ ዮሐንስዘመነ ማቴዎስ እና ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፻፵፱ ቀናት ይቀራሉ።


ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • ፲፰፻፷ ዓ/ም - የፋሲካ ማግሥት ዕለት መቅደላ አምባ ላይ የዓፄ ቴዎድሮስ ሠራዊት እና በሎርድ ኔፒዬር የተመራው የእንግሊዝ ሠራዊት ጦርነት ገጥመው፣ ድሉ የእንግሊዞች ሆነ። ንጉሠ ነገሥቱ ዓፄ ቴዎድሮስ በእንግሊዞች እጅ ከመውደቅ እራሳቸውን ማጥፋትን መርጠው ሽጉጣቸውን ጠጥተው ሞቱ። ቀብራቸው በመቅደላ መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ተከናወነ።
  • ፲፱፻፳፰ ዓ/ም - በሰሜን ኢትዮጵያ በኩል የገባው፤ በማርሻል ፒዬትሮ ባዶሊዮ የሚመራው የፋሺስት ኢጣልያ ሠራዊት በዚህ ዕለት ደሴን በቁጥጥሩ ሥር አዋለ።
  • ፲፱፻፸፩ ዓ/ም - የኡጋንዳው አምባ ገነን ኢዲ አሚን ከተገለበጠ በኋላ ዩሱፍ ሉሌ የአገሪቱ አዲስ ፕሬዚደንት በመኾን ቃለ መሀላቸውን ፈጸሙ።

ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • ፲፰፻፷ ዓ/ም - የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዓፄ ቴዎድሮስእንግሊዝ ሠራዊት ጋር መቅደላ አምባ ላይ ጦርነት ገጥመው ሲሸነፉ በጠላት እጅ ከመውደቅ በገዛ ሽጉጣቸው እራሳቸውን ገደሉ።ቀብራቸውም በመቅደላ መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ተከናወነ።


ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • (እንግሊዝኛ) P.R.O., FCO 371/1829 ANNUAL REVIEW FOR ETHIOPIA FOR 1974


የኢትዮጵያ ወራት
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ