ኅዳር ፳፩

ከውክፔዲያ
(ከኅዳር 21 የተዛወረ)

ኅዳር ፳፩ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የዓመቱ ፹፩ኛው ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፪፻፹፭ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፪፻፹፬ ቀናት ይቀራሉ።

ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

፲፱፻፵፮ ዓ.ም. በኡጋንዳቡጋንዳ ንጉሥ ዳግማዊ ኤድዋርድ ሙቴሳ በአገሪቱ የብሪታንያ አስተዳደሪ ‘ሰር አንድሩው ኮሄን’ ተሽረው በስደት ወደለንደን ሄዱ።

፲፱፻፶፫ ዓ/ም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴጋናላይቤሪያቶጎብራዚልናይጄሪያ እና ካሜሩን የሚያካሂዱትን ጉብኝት ለመፈጸም ከአዲስ አበባተነሱ። ዳሩ ግን ዕቅዳቸውን ሳያጠናቅቁ በኢትዮጵያ የታኅሣሥ ግርግር መነሳት ምክንያት ጉዟቸውን አቋርጠው ይመለሳሉ።

፲፱፻፶፭ ዓ.ም. ዩ ታንት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በዋና ጸሐፊነት ተመረጡ። በዋና ጸሐፊነት ኮንጎ በአየር አደጋ የሞቱትን ዳግ ሃመርሾልድን ይተካሉ።

፲፱፻፶፱ ዓ.ም. የባርባዶስ ደሴት ከብሪታንያ ነጻነቷን ተቀዳጀች።

፲፱፻፷ ዓ.ም. የየመን ሕዝባዊ ሪፑብሊክብሪታንያ ነጻነቷን ተቀዳጀች።

፲፱፻፷ ዓ.ም. በፓኪስታን በኋላ የአገሪቱ መሪ የሆኑት እና በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን ወርደው በስቅለት ሞት የተቀጡት ዙልፊቃር አሊ ቡቶፓኪስታን ሕዝባዊ ፓርቲን መሠረቱ።

፲፱፻፷፯ ዓ/ም - በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የነዳጅ ክምችቱን ለማፈንዳት የተደረገው ሙከራ ከሽፏል

፲፱፻፺፰ ዓ.ም. በካምፓላ ኡጋንዳ የተወለዱት ጆን ታከር ሙጋቢ ሴንታሙ ዘጠና ሰባተኛው የዮርክ ሊቀ ጳጳስ ሆኑ። በዚህ ቤተ ክርስቲያን ይሄንን ታላቅ ሥልጣን የተቀበሉት የመጀመሪያው ጥቁር ጳጳስ ናቸው።

ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

፲፰፻፳፰ ዓ.ም. ሳሙኤል ላንግሆርን ክሌመንስ የተባለው አሜሪካዊ እና በብዕር ስሙ ማርክ ትዌይን የሚባለው ታዋቂ ደራሲ

፲፰፻፷፯ ዓ.ም. ታላቁ የሁለተኛው ዓለም ጦርነት መሪ እና የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዊንስተን ቸርቺል

ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

፲፰፻፺፫ ዓ.ም. የጽሑፍ፣ የቅኔ እና የተውኔት ጠቢብ የአየርላንድ ተወላጁ ኦስካር ዋይልድ

ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • (እንግሊዝኛ) P.R.O., FO 371/154836 - Annual Report from Ethiopia for 1960
  • {{en]] P.R.O., FCO 371/1829 - ANNUAL REVIEW FOR ETHIOPIA FOR 1974


የኢትዮጵያ ወራት
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ