ሶማሊላንድ
Appearance
|
Somaliland |
||||||
|---|---|---|---|---|---|---|
|
||||||
| ዋና ከተማ | Hargeisa | |||||
| ብሔራዊ ቋንቋዎች | ሶማልኛ | |||||
| መንግሥት {{{ፕሬዚዳንት |
አህመድ ሞሐመድ ሞሐሙድ |
|||||
| የመሬት ስፋት አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.) |
137,600 km2 |
|||||
| ገንዘብ | ሶማሊላንድ ሺሊንግ | |||||
| የሰዓት ክልል | UTC -+3 | |||||
| የስልክ መግቢያ | +252 | |||||
ሶማሊላንድ እውቅና ያልተሰጠው በስራው ግን እንደ አንድ ልዑላዊ ሃገር የሚንቀሳቀስ በአፍሪካ ቀንድ በሰሜን ምስራቅ ሶማሌ የሚገኝ አካል ነው። ግንቦት ፲ ቀን ፲፱፻፹፫ ዓ/ም፥ የሶማሊላንድ ሕዝብ ነጻነቱን አውጆ ከሶማሌ ፲፰ ክፍለ ሀገራት ፭ቱን አካቶ ይዟል። ይህም በጅቡቲ፣ በኢትዮጵያ፣ በቀድሞው የጣልያን ሶማሊላንድና በአደን ባሕረሰላጤ የሚካለለውን ፻፴፯ ሺ ፮መቶ ካሬ ኪሎሜትር የሚሸፍነውን ቦታ ከሞላ ጎደል ይሸፍናል። የሶማሊላንድ ዋና ከተማ ሃርጌሳ ነው።

እውቅና ባያገኝም አካሉ ሳይዋዥቅ እንደ መንግሥት እየሠራ ይገኛል። በመስከረም ፲፰ ቀን ፲፱፻፺፰ ዓ/ም በተደረገው የከተሞች የሊቀመንበርና የሕዝብ ተወካዮች ምርጫ ኡዱብ ፓርቲ ሲያሸንፍ በተለያዩ ታዛቢዋ ትክክለኛና ነጻ ምርጫ እንደ ነበር ዘገባ ቀርቧል። ይህም ሶማሊላንድ ላቀረበችው የእውቅናው ጥያቄ ድጋፍ ይሰጣል የሚሉ ወገኖች አሉ።
| ||||||||||||||||||||||||||
| ጅምር! ይህ አጭር ጽሑፍ መሠረት ወይም መዋቅር ነው። አሁን ሊያስፋፉት ይችላሉ! |
