ኤስቶኒያ
Eesti Vabariik |
||||||
---|---|---|---|---|---|---|
|
||||||
ብሔራዊ መዝሙር: Mu isamaa, mu õnn ja rõõm |
||||||
![]() |
||||||
ዋና ከተማ | ታሊን | |||||
ብሔራዊ ቋንቋዎች | ኤስቶንኛ | |||||
መንግሥት ፕሬዚዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር |
ፓርለሜንታዊ ሪፐብሊክ ቱማስ ሄንድሪክ ኢልቭስ አንድረስ አንሲፕ |
|||||
ዋና ቀናት ነሐሴ 14 ቀን 1983 (August 20, 1991 እ.ኤ.አ.) |
ነፃነት ተመለሰ |
|||||
የመሬት ስፋት አጠቃላይ (ካሬ ኪ.ሜ.) |
45,336 (129ኛ) |
|||||
የሕዝብ ብዛት የ2017 እ.ኤ.አ. ግምት |
1,315,635 (151ኛ) |
|||||
ገንዘብ | ዩሮ (€) | |||||
የሰዓት ክልል | UTC +2 | |||||
የስልክ መግቢያ | +372 | |||||
ከፍተኛ ደረጃ ከባቢ | .ee |
ኤስቶኒያ በባልቲክ ባሕር ላይ የተገኘ አገር ሲሆን 1.4 ሚሊዮን ያህል ሕዝብ ይኖሩበታል። መደበኛ ቋንቋቸው ኤስቶንኛ የፊንላንድኛ ዘመድ ነው። የኤስቶኒያ ብሔር ከጥንት ጀምሮ በአገሩ ኑረዋል። እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ አረመኔ አገር ነበረ፤ ያንጊዜ ክርስቲያን መስቀለኞች ያዙት። በ16ኛው ክፍለ ዘመን ከፕሮቴስታንት እንቅስቃሴና ከጦርነቶች በኋላ ኤስቶኒያ ለስዊድን ሥልጣን ወጣ፣ በ1713 ዓ.ም. ወደ ሩስያ ተዛወረ። በዚህ ዘመን ሁሉ ግን እስከ 1808 ዓ.ም. ድረስ የኤስቶኒያ ሕዝብ ገበሬዎች ሆነው የጀርመን ገዢዎች ነበሩዋቸው። ጀርመኖች በ1ኛው ዓለማዊ ጦርነት ወርረው የሶቭየት ኅብረት በተነሣ ጊዜ ኤስቶኒያ ነጻ መንግሥት ሆነ። በ1932 ዓ.ም. ግን የሶቭየት ኅብረት በግፍ ጨመረው። ዩናይትድ ስቴትስ ይህንን አድራጎት መቸም አልተቀበለም። የሶቭየት ህብረት በ1983 ዓ.ም. በወደቀበት ዘመን ኤስቶኒያ ዳግመኛ ነጻ ሪፐብሊክ ሆነ። ፓርላማውና ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዲሞክራስያዊ ምርጫ ይመረጣሉ። በ1996 ዓ.ም. የአውሮፓ ኅብረት እንዲሁም የናቶ አባል ሆነ። ከ2003 ዓ.ም. ጀምሮ መደበኛ ገንዘቡ ዩሮ ሆኗል።
ብዙ ኗሪዎች ከአገሩ በመውጣታቸው፣ የልደትም ቁጥር በቂ ባለመሆኑ የኤስቶኒያ ሕዝብ ቁጥር ከ1983 ዓ.ም. ጀምሮ በየዓመቱ እየተቀነሰ ሆኗል። ኤስቶኒያ በዘመናዊው መረጃ ኅብረተሠብ ከፍተኛ ሚና ወስዷል፤ የተደረጀ ኢንተርነት መንግሥት አገልግሎት አለው። ለመሆኑ አሁን ትኩስ የሆነ መስሪያ ስካይፕን የፈጠረው ድርጅት ከኤስቶኒያ ነው። ይህም ድርጅት ከ10 አመት በፊት ትኩስ የነበረውን ካዛዓ ፈጠረ።
|