ጥቅምት ፴

ከውክፔዲያ
(ከጥቅምት 30 የተዛወረ)

ጥቅምት ፴ ቀን በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር የሁለተኛው ወር መጨረሻ፤ የዓመቱ ፷ኛ እና የመፀው ወቅት ፴፭ተኛ ቀን ነው። ከዚህ ዕለት በኋላ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ፣ በ ዘመነ ሉቃስ ፫፻፮ ቀናት በ ዘመነ ዮሐንስ፤ በ ዘመነ ማቴዎስ፤ እና በ ዘመነ ማርቆስ ደግሞ ፫፻፭ ቀናት ይቀራሉ።

ይሄ ዕለት በጀርመን አገር በ፲፰፻፵፩፲፱፻፲፩፲፱፻፲፮፲፱፻፴፩ እና ፲፱፻፹፩ ዓመተ ምሕረታት በተፈጸሙት ብሔራዊ ታሪኮች ምክንያት የአገሪቱ “የጦስ ቀን” (Schicksalstag (day of fate)) ይባላል።

ዓቢይ ታሪካዊ ማስታወሻዎች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  • ፲፱፻፲፮ ዓ.ም. - የጀርመን ፖሊሶችና ወታደሮች በሙኒክ ከተማ የቢራ አዳራሽ በናዚዎች ቅስቀሳ የተጀመረውን ያልተሳካ መፈንቅለ መንግሥት ደመሰሱ።
  • ፲፱፻፴፩ ዓ.ም. - በጀርመን እና በአውስትሪያ አገሮች ናዚዎች የይሁዳውያን መቅደሳትና መደብሮችን በዝብዘው በእሳት አጋዩ። ይሄም ታሪካዊ ምዕራፍ “Kristallnacht” የመስተዋት መስበሪያ ምሽት በመባል ይታወቃል።
  • ፲፱፻፶፰ ዓ.ም. - በሰሜን ምሥራቅ አሜሪካ ግዛቶችና በካናዳ ለአሥራ ሦስት ሰዐት ተኩል ያህል ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጦ ስምንት መቶ ሺህ ሰዎች በኒው ዮርክ ውስጠ መሬት ባቡር ላይ ተደንቅረው አመሹ። ችግሩ በግምት የሃያ አምስት ሚሊዮን ሕዝቦችን ኑሮ አዛብቷል።

ልደት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዕለተ ሞት[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

ዋቢ ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ፤ "ፍሬ ከናፍር። ዘ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ።" ፫ኛ መጽሐፍ (፲፱፻፶፯ ዓ/ም) ገጽ ፩ሺ ፬፻፷፮፮


የኢትዮጵያ ወራት
መስከረም - ጥቅምት - ኅዳር - ታኅሣሥ - ጥር - የካቲት - መጋቢት - ሚያዝያ - ግንቦት - ሰኔ - ሐምሌ - ነሐሴ - ጳጉሜ