አርባ ምንጭ

ከውክፔዲያ
አርባ ምንጭ
አርባ ምንጭ is located in ኢትዮጵያ
{{{alt}}}
አርባ ምንጭ

6°2′ ሰሜን ኬክሮስ እና 37°33′ ምሥራቅ ኬንትሮስ


አርባ ምንጭ ከተማ

የሰላም ሰገነት፤ የደቡብ ፈርጥ፤ ትንሿ ኢትዮጵያ ፤ምስለ ገነት

አርባ ምንጭ ከተማ ላለፉት 60 ዓመታት የተለያዩ አስተዳደር መዋቅሮች ማዕከል ሆና በቆየችባቸው ጊዜያት የሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች ወግና ባህል በማክበር በሰላም የኖረች ትንሿ ኢትዮጵያ አርባምንጭ ከተማ  ዛሬ ዘላቂነት ላለው ልማት ሰላማዊና ሁሉን አቀፍ የሆነ ማህበረሰብን ለመፍጠር አስችሏታል።

የአርባ ምንጭ ከተማ የጋሞ ዞን መዲና ስትሆን ከአዲስ አበባ በስተደቡብ በ505 ኪሎ ሜትር ፣ከሀዋሳ ከተማ በስተ ደቡብ ሆና በ275 ኪ. ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።

ለኮንሶ ዞን እና ለደቡብ ኦሞ ዞን ዋና መተላለፍያ ስትሆን በቀደምት ጊዜ የአሁኑን አንጋፋውን የአየር ማረፊያን ጨምሮ የባህር ትራንስፖርት የሚሰጥባት የስልጣኔ አሻራ ያረፈባት ከተማ ናት።

ከባህር ጠለል በላይ ከ1285 ሜትር ከፍታ ላይ ስትገኝ በ6°2′ ሰሜን ኬክሮስ እና 37°33′ ምሥራቅ ኬንትሮስ መጋጠሚያ መስመር ስትሆን በ22 ሺህ 851 ሄክታር  አስተዳደራዊና በ18 ሺህ 375 ፕላን ወሰን ላይ ከትማለች፤ 24 ሰልሸስ ግሬድ የሙቀት መጠን ያላት፤ 900 ሚሊ አመታዊ የዝናብ መጠን አላት።

ፈጣሪ የቸራት ውብ የተፈጥሮ ጸዳል የተጎናጸፈች ህብረ ብሔራዊት ከተማዋ በአባያና ጫሞ የስምጥ ሸለቆ ሃይቆች የተከበበች፤ የብዝሃ ህይወት መገኛ፤ የነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ ብርቅዬ እንስሳት መናኸሪያ፤ የከተማዋ መጠሪያ የሆኑት አርባዎቹ ምንጮች መፍለቂያ፣ ጥቅጥቅ የደን ንጣፍ፣ የእግዜር ድልድይ፣ በኢትዮጵያ ብቸኛው የአዞ ራንች መገኛና አስደማሚው የአዞ ገበያ ውብ የጋሞ የተፈጥሮ መልክአምድር መናገሻ፤ የሰላም ተምሳሌት ከተማ ናት፡፡

በሀገራችን ባለው ምቹ የመሠረተ ልማት፣ የሆቴል፤ የቱሪዝምና የአግሮ ኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት አማራጭ እድሉን ለመጠቀም አርባ ምንጭና የጋሞ ምድርን ማዬትና መጎብኘት በቂ ነው፡፡

በአትክልትና ፍራፍሬ ተክል የተሸፈነው አካባቢው ለሀገራችን በሰፋፊ እርሻዎች የማንጎ፤ የሙዝ፤ የአቮካዶ፤ የአፕልና የሽንኩርት ምርት ማምረቻ ሆነዋል፡፡የአዞ ቆዳ አቅርቦት፤ የዓሳ ምርት ምንጭ፤ የበርካታ ቀንድ ከብት ስጋና የወተት ምርት ፀጋችን ለኢንቨስተሩ ተመራጭና ለሀገር ኢኮኖሚ እድገት ጠቀሜታ ያለው ነው፡፡

በውድ ገንዘብዎ በሥራዎ ደስታዎን እጥፍ ለማድረግ እርግጠኛ ለመሆን አርባ ምንጭ ከተማንና ጋሞ አከባቢን መዳረሻዎ ያድርጉ፤ ለዓለም የሰላም ተምሳሌት የሆነው የጋሞ ህዝብና ውብ የተፈጥሮ ጸጋንና የተትረፈረፈ የኢንቨስትመንት አማራጮችን በአርባ ምንጭ ይመልከታሉና።

ዘውትር ለደንበኞቹ አገልግሎት የሚሰጠው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአርባ ምንጭ ከተማም የሚሰጠውን ዕለታዊ የበረራ አገልግሎት በመጠቀም ቤተኛ እንዲሆኑ ለእርስዎና ለቤተሰብዎ ማረፊያ ሊሆኑ ማራኪ ሎጆች፤ ሆቴሎች፤ ሪዞርቶች እና በውብ የባህል መንደሮች ተዝናንተው እንዲያተርፉ ምንግዜም ዝግጁ ናቸው፡፡

3 መቶ  50 ሺ በላይ የሚሆኑ ህዝቦች በመከባበር በፍቅር የሚኖሩባት የፍቅር ከተማ ስትሆን ከግንቦት፣ ሰኔ፣ መስከረም፣ ጥቅምት ወራት ከፍተኛ ዝናብ የሚዘንብባት፤ ሞቃታማና በአማካኝ ነፋሻማ የአየር ንብረት ያላት በመሆኗ የፍራፍሬና የአትክልት አምራች አድርጓታል፡፡

ከተማዋ አባያና ጫሞ ሐይቅ፤ የነጭ ሣር ብሔራዊ ፖርክን ጨምሮ በርካታ የቱሪስት መስዕቦች ባለቤት መሆኑዋ ለቱሪስት መዳረሻና ለአስተዳደር ማዕከልነት ተመራጭ ያደርጋታል፡፡

አርባ ምንጭ ከ1955 እስከ 1982/83 ዓ/ም ድረስ የጋሞ ጐፋ ጠቅላይ ግዛትና የጋሞ ጐፋ ክ/ሀገር ርዕሰ ከተማ ማዕከል በመሆን፤ ከ1982/83 እስከ 1993 ዓ/ም ድረስ የሰሜን ኦሞ አስተዳደር ፣ የሰሜን ኦሞ ክልልና የሰሜን ኦሞ ዞን ርዕሰ ከተማ የሆነችው አርባ ምንጭ ፣ ከ1993 እስከ 2011 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ዓመታት ደግሞ ጋሞ ጐፋ ዞን ዋና ከተማ በመሆን አገልግላለች፤  በአሁን ጊዜ ህብረ ብሄራዊ ከተማችን   "አርባ ምንጭ" የጋሞ ዞን መዲና ሆና እያገለገለችም ትገኛለች፡፡

በአሁን ወቅትም ከ2015 ዓ፤ም ጀምሮ የደቡብ ኢትዮጵያ ምክትል ርዕስ መስተዳድርና የህግ አውጭ ምክር ቤት መቀመጫ ስትሆን የክልሉ የኢኮኖሚ ክላስተር ማዕከል በመሆን እያገለገለች ትገኛለች፡፡

ተቋማትና መዝናኛ ማዕከላት:-

የአርባምንጭ ከተማ በተፈጥሮ መስህብ የተንበሸበሸች በመሆኑዋ በርካታ ተሪስቶች ወደ ከተማዋ የሚመጡ ሲሆን ባለፉት አመታት ብቻ በሚሊዬን የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና እንግዶችን ተቀብላ ደረጃቸውን በጠበቁ ማራኪ በሆኑ ሆቴሎች፣ ሪዞርቶች፣ ሎጆች ፤መኝታ ቤቶች አስተናግዳ ሸኝታለች። አሁንም የአገር ውስጥም ሆነ የውጪ ቱሪስቶችን እና እንግዶችን ከቀድሞው በተሻለ ጥራትና መስተንግዶ በመቀበል ላይ ትገኛለች።

መሠረተ ልማቶች :-

በርካታ መሠረተ ልማቶች ያሉባት ከተማ ስትሆን የአለም አቀፍ አየር ማረፍያ ፣ ከስምንት በላይ የሚሆኑ ደረጃቸዉን የጠበቁ አስፓልት መንገዶች ፣ በርካታ የዉስጥ ለዉስጥ ኮብል ንጣፍ መንገዶች ፣ መሸጋገሪያ ድልድዮች ፣ ከስድስት በላይ የሚሆኑ አደባባዮች ፣ የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊ ቴክኒክና ሳታላይት ዩኒቨርሲቲ ጨምሮ በርካታ ኮሌጆች ፣ ከ35 ሺ በላይ ተማሪዎችን የሚያስተናግደው አንጋፋው የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፣  የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል፣ ግዙፉ ሪፌራል ሆሲፒታል ፣ የጤና ጣቢያዎች ፣ የአርባ ምንጭ ከተማ ዉሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ፣ የአርባምንጭ ከተማ ቴሌ ኮሚዩኒኬሽን የአርባምንጭ ከተማ መብራት ሀይል ድርጅትን ጨምሮ በርካታ መሠረተ ልማቶች ይገኛሉ፡፡

የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች:-

ግንባታቸው ተጠናቀው አገልግሎት ከጀመረው ጋሞ አዳሪ  2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የአንጋፋው አርባ ምንጭ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃና መሠናዶ ትምህርት ቤት G+3  ህንፃ በተጨማሪ ከሰሞኑ የሚመረቁት  አዲስ ግዙፉ ልዩ የዶክተር አመኑ መታሰቢያ ሆስፒታል፣  የጋሞ አደባባይ፣ የአረንጓዴ ልማት ስራዎችና ሌሎች በርካታ መሠረተ ልማቶች ሲሆን ከ200 ሚሊዬን ብር በላይ ወጪ የአርባምንጭ ውሀና ፍሳሽ ድርጅት ሁለገብ ህንፃ፤ ለተለያዩ የቢሮ አገልግሎት  የሚውሉ የከተማ አስተዳደሩ ፣ የማዘጋጃ ቤት ከዳስተር ህንፃ በሚጠናቀቁበት ወቅት ለሕዝብ ተደራሸ አገልግሎት የሚሠጡና የከተማዋን እድገት የሚያፋጥኑ ናቸው።

ከተማዋ በ2015 ዓ.ም የአስር ዓመት መዋቅራዊ ፕላን ሰፊ የሕዝብ ትስስርን፣ ዘመናዊ የከተማ አኗኗር፣ የአረንጓዴ ልማት ሽፋን የሚረጋገጥበትና ሰፊ የኢንቨስትመንትና የልማት አማራጮችን ባካተተ መልኩ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ የገባች  ተመራጭ ከተማ ነች።

የሰላም ሰገነትና የአቃፊ ባህል ማዕከል:-

አርባ ምንጭ፤ በአቃፊና አስታራቂ በሆነው የጋሞ ህዝብ የተከበበች ከተማ በመሆኗ በሀገሪቱ የተፈጠረውን ለውጥ ተከትሎ በመጣው ያለመረጋጋት በአንዳንድ አካባቢዎች ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሣዊ ኪሳራ በገጠመበት ወቅት በከተማዋም ሊፈጠር የታሰበ ንብረት የማውደምና የጥፋት ድርጊት የጋሞ አባቶች ዓለምን ባስደመመ እንዲሁም ድንቅና ምሣሌ በሚሆን ሁኔታ እርጥብ ሣር ብቻ በመያዝ ስሜታዊነትን፤ቁጣንና ጥፋትን በማብረድ በታላቅ የታሪክ ማህደር ተመዝግበዋል

የአርባ ምንጭ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሚዩኒኬሽን

ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]