በሌ

ከውክፔዲያ
በሌ
Bale Ambbaa
ከተማ
አገር  ኢትዮጵያ
ክልል ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል
ዞን ወላይታ
ወረዳ ኪንዶ ኮይሻ
ከፍታ 1,500 ሜ.
በሌ is located in ኢትዮጵያ
{{{alt}}}
በሌ
የበሌ ፡ አቀማመጥ ፡ በኢትዮጵያ ፡ ውስጥ

6°55′ ሰሜን ኬክሮስ እና 37°31′ ምሥራቅ ኬንትሮስ


በሌደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልልወላይታ ዞን የሚገኝ ከተማ ነው። ከተማውም በወላይታ ዞን የኪንዶ ኮይሻ ወረዳ የአስተዳደር ዋና ከተማ ሆኖ ያገለግላል። በሌ ከአዲስ አበባ ወደ ደቡብ በአዲስ ቡታጅራ-ሶዶ መንገድ ስከሄድ እስከ 400 ኪሎ ሜትር ርቀት ይደርሳል። ከወላይታ ዞን ዋና ከተማ ከሶዶ በ38 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። ከተማው በአማካይ ከባህር ጠለል በላይ 1500 ሜትር ከፍታ አላው። በሌ በካርታ ስታይ በ6°55'05" ሰሜን እና በ37°31'55" ምስራቅ መካከል ይገኛል።

የህዝብ ቁጥር[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

በሌ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ውስጥ ሕዝብ ተጠጋግተው ከሚኖርባቸው ቦታዎች አንዱ ነው። እ.ኤ.አ. በ 2020 የህዝብ ብዛት ትንበያ በማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ በተካሄደው የከተማው አጠቃላይ የህዝብ ብዛት 16,926 ይይዛል። ከኢነዚህም ወንዶች 8,217 ሲሆኑ ሴቶች ደግሞ 8,709 ይቆጥራሉ።[1]

ምንጮች[ለማስተካከል | ኮድ አርም]

  1. ^ "የበሌ ከተማ የህዝብ ብዛት". Archived from the original on 2022-07-07. በ2022-02-04 የተወሰደ.