ከ«አማራ (ክልል)» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

ከውክፔዲያ
Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 62፦ መስመር፡ 62፦
[[ru:Амхара (регион)]]
[[ru:Амхара (регион)]]
[[sh:Regija Amhara]]
[[sh:Regija Amhara]]
[[sr:Регион Амхара]]
[[sr:Амхара (регион)]]
[[sv:Amhara (region)]]
[[sv:Amhara (region)]]
[[tr:Amhara Bölgesi]]
[[tr:Amhara Bölgesi]]

እትም በ01:45, 27 ፌብሩዌሪ 2013

አማራ ክልል

አማራ (ክልል 3) ከዘጠኙ የኢትዮጵያ ክልሎች አንዱ ነው። ዋና ከተማ ባሕር-ዳር ነው። የአማራ ብሔራዊ ክልል ጅኦግራፊያዊ አቀማመጥ በ8° 45 እስከ 13° 45 ሰሜን የኬንትሮስ እና በ35° 46 እስከ 40° 25 ምስራቅ የኬንትሮስ መስመር ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በምስራቅ የአፋርና የኦሮሚያ ክልሎች፣ በምዕራብ ሱዳን እና ቤንሻንጉል-ጉምዝ ክልል፣ በሰሜን የትግራይ ክልልና በደቡብ የኦሮሚያ ክልል ያዋስኑታል፡፡ የቆዳ ስፋቱ ፻፶፯ሺ፸፮ ካሬ ሜትር ሲሆን ከአገሪቱ አሥራ አምስት በመቶ ድርሻ ይይዛል፡፡የየክልሉ ሕዝብ ብዛት ደግሞ በ፳፻፪ ዓ/ም ፲፰ ሚሊዮን ፻፺፪ ሺ ፯መቶ ፺፭ እንደነበር የተገመተ ሲሆን ከአገሪቱ ጠቅላላ ሕዝብ ሩብ እጅ አካባቢ ድርሻ ይይዛል፡፡

ክልሉ በ፲ ዞኖችና በ፻፷፮ የገጠርና የከተማ ወረዳ አስተዳደሮች የተከፋፈለ ሲሆን ከዚህ ውስጥ ፴፰ የሚሆኑት የከተማ አስተዳደሮች ናቸው፡፡የአማራ፣የአገው፣የኦሮሞና የሌሎች ብሔረሰቦች በጋራ የሚኖሩበት ክልል ነው፡፡ በዚሁ ክልል ውስጥ ሰሜን ሸዋ አንዱ የአማራ ክልል እና ባለታሪክ ክልል ሲሆን የአጼ ሚኒሊክ የትውልድ ሀገር ከደብረብርሃን 5 ኪሎሜትር ርቀት አንጎለላ አካባቢ ሲሆን ይህ ክልል በጀግንነት የሚታወቅ ቦታ ነው። ከእነሱም ውስጥ ተጉለትቡልጋምንጃርጅሩመሬ/መርሀቤቴ/ ፣ መንዝይፋትአንኮበር ፣እና ሌሎችም አሉ። ይሄ ዞን ጀግንነት ብቻ ሳይሆን ደግነትና እንግዳ ተቀባይ ፣ አክባሪ ፣ ሀይማኖተኛ ፣ፈሪሀ እግዚአብሔር ያለው ፣ አትንኩኝ ባይ ፣ ጀግና ሕዝብ ነው። ይህ ክልል 98.5 በመቶ አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ነው ። ነገር ግን ጥንቱ የ ቤተ አምሐራ ምድር መነሻ የአሁኑን ወሎ አጠቃሎ የያዘ ሲሆን በውስጡም ጥንታዊውን አምሐራ ሳይንት፣ ደብረሲና፣ ተንታ፣ወግዲ፣ከለላ፣ለጋንቦ፣ኩታበር፣አምባሰል፣ሮሃ(ላሊበላ)፣ደላንታ እና ዳውንት፣ግዳን...ወዘተ ያጠቃልላል።

ሌላው ያአማራ ክልል ዞን ሰሜን ጎንደር ነው። ዞኑ ከ20 በላይ ወረዳዎች ሲኖሩት ብዙ ታሪካዊ ቦታዎች ይገኛሉ። ከነዚህም መካከል የፋሲል ግንብየሱሰንዮስ በተ መንግስትየዞዝ አምባ ውቅር ፍልፍል ገዳም፣ ዋሻ ፣ የጎርጎራ ወደብየወርቃምባ ውቅር ፍልፍል በተ ጊዎርጊስ ገዳም... የራስ ዳሸን ተራራ ወዘተ. ናቸዉ።

ምዕ/ጎጃም ዞንም በዚሁ ክልል ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በውስጡ ቡሬ ወምበርማ ወረዳ፡ ሰከላ፡ ይልማና ደንሳ፡ ደምበጫዳሞት ወረዳዎችን ይገኙበታል። ቡሬ ወረዳ የንግድ ማኣከል ስትሆን ወለጋን (ነቀምትን)፡ አዲስ አበባን አና ባህር ዳርን ታገናኛለች። በወረዳዋ ዉስጥ ሁሉም አዝዕርቶች የሚመረቱ ቢሆንም በዋናነት በርበሬጤፍበቆሎ፡ በብዛት ይመረታሉ። ቡሬ ወረዳ አንድ ግብርና ማሰልጠኛ፡ አንድ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፡ 1 ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ፡ 1 ፕሪፓራቶሪ አና 3 አንደኛና መለስተኛ ት/ቤቶች ይገኙባታል። የማዕድን ዉሃ ፋብሪካና ሌሎች የግብርና ማቀነባበሪያዎችም ይገኛሉ። ለግብርና ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነ የአየር ንብረትና መሬት ያላት ወረዳ ስትሆን ባለሃብቶች በዚህ አካባቢ ቢሰማሩ ዕራሳቸዉን ጠቅመቅው ህብረተሰቡን መጥቀም ይችላሉ።

የተፈጥሮ ሀብት

በክልሉ አልፎ አልፎ ከሚታዩ የመንግሥትና የማኅበራት ደኖች፣ በደሴቶች፣በአብያተ ክርስቲያናት፣ በወንዞች ዳርቻና ሰው ሊደርስባቸው በማይችሉ ገደላማና ተራራማ ስፍራዎች ከሚገኙ ጥቂት ደኖች በስተቀር ሊጠቀስ የሚችል ከፍተኛ የደን ሀብት ጋር በቅርብ የተያያዘ ነው። በዚህ ረገድ በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ የሚገኙ እንደ ቀይ ቀበሮዋልያጭላዳ ዝንጀሮ እንዲሁም በምዕራባዊው የክልሉ አካባቢ ዝሆን አንበሳነብርሰጐንና የተለያዩ አዕዋፋት በስተቀር ከፍተኛ የዱር እንስሳት ክምችት ካለመኖሩም በላይ በተለያዩ አካባቢዎች ባሉ ጥቂት የደን ቅሪቶችና ዋሻዎች የነበሩት አነስተኛ ቁጥር ያላቸው አራዊቶችም ለዘመናት በደረሰው የደን መጨፍጨፍና መራቆት ምክንያት ከክልሉ ወደ ሌላ አካባቢ እንደተሰደዱ ይታወቃል፡፡

የክልሉን የማዕድን ሀብት አስመልክቶ በሚገባ የተጠናከረ ጥናት ባይኖርም ከክልሉ ስነ-ምድራዊ ሁኔታዎችና ከተካሄዱ አንዳንድ ጠቋሚ ጥናቶች መረዳት እንደሚቻለው በክልሉ ውስጥ የተለያዩ ማዕድናት እንደአሉ ይገመታል። በዚህም መሠረት በሰሜን ሸዋ የኦፓል ማዕድን፣ በሰሜን ጐንደር፣ በጭልጋና በደቡብ ወሎአምባሰል ወረዳ የድንጋይ ከሰል ክምችት እንዳሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከዚህም በተጨማሪ ለግንባታ ሥራ የሚውል በቂ የድንጋይ፣ የኖራ ድንጋይ፣የሸክላ አፈር፣ ጅኘሲየም፣ የጌጣጌጥ ማዕድናት እንዲሁም በዓባይ ሸለቆ የዕብነ በረድ ሐብቶች እንዳሉ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ይሁን እንጅ በውል የሚታወቀው ሐብትም ቢሆን በበቂ ሁኔታ አልለማም።

የውሐ ሀብት

ክልሉ የትልልቅ ወንዞች ባለቤት ሲሆን በአጠቃላይ በሦስት ዋና ዋና ተፋሰሶች ተከፋፍሎ ሊታይ የሚችል ነው። እነርሱም የዓባይ፣ የተከዜ እና የአዋሽ ተፋሰስ ናቸው። ወደነዚህ ተፋሰሶች የሚገቡና ዓመቱን በሙሉ የማይደርቁ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ትልልቅ ወንዞች ያሉ ሲሆን በክልሉ በጥቅም ላይ ያልዋለ ሰፊ የውሐ ሀብት መኖሩን ያመለክታሉ። ከነዚህ በተጨማሪ እንደ ጣናና አርዲቦ የመሳሰሉ ሐይቆችም በክልሉ ውስጥ ይገኛሉ። በአጠቃላይ በክልሉ ውስጥ ባሉ ትልልቅ ወንዞችና መጋቢ ወንዞች የመስኖ ልማት ለማካሄድ የሚያስችል ከፍተኛ የውሐ ሐብት ክምችት እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ይሁን እንጅ እስከ አሁን ጥቅም ላይ የዋለው በጣም አነስተኛ ነው።

ምጣኔ ሀብት

በአመዛኙ አብዛኛው የክልሉ ምጣኔ ሀብት በግብርና እና ከብት እርባታ ላይ የተመሠረተ ነው። በአጠቃላይ ክልሉ ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ ቁጥር፣ ለእርሻና ለእንስሳት እርባታ ተስማሚ የሆነ መሬት፣ የአየር ንብረት እና የውሐ ሀብቶች ያሉት በመሆኑ በተለይም የሰብል እና የእንስሳት ሀብት ልማት ለማካሄድ የማይናቅ አቅም አለው። በዝናብም ሆነ የመስኖ እርሻ ልማት በማስፋፋት በክልሉ በገበያ የሚውሉ የተለያዩ የአገዳ፣ የጥራጥሬ፣ የቅባት፣የአትክልትና ፍራፍሬ ሰብሎችን ማምረት ይቻላል። ጤፍ፣ ገብስ፣በቆሎ፣ ማሽላ፣ዳጉሣ፣ ስንዴ፣አተር፣ ባቄላ፣ ሽምብራ፣ ጓያ፣ምስር፣ሰሊጥ፣ ጥጥ፣ ተልባ፣ ወዘተ የመሳሰሉት በክልሉ ውስጥ ከሚመረቱ ሰብሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ ናቸው። በእንስሳት ሀብት ረገድም በወተት ምርታማነታቸው የታወቁ የፎገራ ዝርያዎችና በፀጉር ምርት የታወቁት የመንዝ በግ ዝርያዎች በክልሉ ይገኛሉ።

የጎብኚዎች መስሕብ

በቱሪዝም የሥራ መስክ ሊበለጽጉ ፣በሰፊው አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ እና በዓለም የቅርስ መዝገብ የሰፈሩት የጐንደር ቤተ መንስግት ህንፃዎች፣ የላሊበላ አብያተ ክርስቲያናት፣ የሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ እንዲሁም ልዩ ልዩ የቱሪዝም መስሕቦች አሉት፣ ይሁን እንጅ ክልሉ ሰፊ የሆነ የቱሪዝም እምቅ ሀብት ያለው ቢሆንም በሚፈለገው መጠን በጥቅም ላይ ውሏል ማለት አያስደፍርም። በዚህ ረገድ፤አካባቢዉ የብዙ ታሪካዊ ገዳማትና የታሪካዊ ቅርሶችም ባለሀብት ነው። ለምሳሌ ከሚጠቀሱት መኃል ፦ አደል ሚካኤል፡ ይስር ፏፏቴ፡ ባንጃ ተራራው ወዘተ...

ዋቢ ምንጭ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ድረ-ገጽ፤ "የክልሉ አጠቃላይ ገጽታ" (accessed 21 Dec 2012) http://www.amharainfo.gov.et/index.html/index.php?option=com_content&view=article&id=61%3A2011-02-10-05-51-55&catid=7%3Aoverview-of-the-region&Itemid=29&lang=en


ኢትዮጵያ

ታሪካዊ ቦታዎች - አክሱም | ላሊበላ | ጎንደር | ነጋሽ | ሐረር | ደብረ-ዳሞ | አዲስ አበባ
አስተዳደራዊ ክልሎች - ትግራይ | አፋር | አማራ | ኦሮሚያ | ሶማሌ | ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል | ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች | ጋምቤላ | ሐረሪ | አዲስ አበባ | ድሬዳዋ
ቋንቋዎች - አማርኛ | ግዕዝ | ኦሮምኛ | ትግርኛ | ጉራጊኛ | ሶማሊኛ | አፋርኛ | ሲዳምኛ | ሃዲያኛ | ከምባትኛ | ወላይትኛ | ጋሞኛ | ከፋኛ | ሃመርኛ | ስልጢኛ | ሀደሪኛ
መልክዓ-ምድር - አባይ | አዋሽ | ራስ-ዳሽን | ሶፍ-ዑመር | ጣና | ደንከል | ላንጋኖ | አቢያታ | ሻላ
ከተሞች - የኢትዮጵያ ከተሞች