መርጡለ ማርያም በምስራቅ ጎጃም፣ ሞጣ አውራጃ ውስጥ የሚገኝ ጥንታዊ ቤ/ክርስቲያን ሲሆን በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ከተሰራው አክሱም ጺዮን ቀጥሎ የተሰራ ሁለተኛው ቤ/ክርስቲያን ነው።
የሃድያዋ ንግስት እሌኒ ግብጻውያንን በማስመጣት በ1510 የጥንቱ ቤ/ክርስቲያን በግምብ ተሰርቶ እንዲሻሻል አደረገች ። [1] ነገር ግን በ1529-30፣ አጠቃላይ ቤ/ክርስቲያኑ በግራኝ አህመድ እንዲፈርስ ተደረገ። በ1540ወቹ ውስጥ በአጼ ገላውዲወስ አነሳሽነት ቤ/ክርስቲያኑ እንደገና ታነጸ። ነገር ግን በ1560 ወቹ መልሶ በተንቀሳቃሽ የኦሮሞ ቡድኖች ጉዳት ደረሠበት። ለግማሽ ምዕት አመት እንደፈረሰ ቆይቶ በአጼ ሱሰኒዮስ ዘመን ጀስዩቱ ብሩኖ ብሩኒ ንግስት እሌኒ ባሰራቸው ቤ/ክርስቲያን ፍርስራሽ ድንጋይ በመጠቀመም እንደገና ቤ/ክርስቲያኗን እንዳነጸ ጻህፍት ይዘግባሉ [2]
- ንግስት እሌኒ በመርጡለ ማሪያም እንደተቀበረች ይነገራል።
- በ1604 ሱሰኒዮስ በመርጡለ ማርያም የዙፋን አክሊል እንደደፋ በታሪክ ተመዝግቧል።
መርጡለ ማርያም
በራፍ- መርጡለ ማርያም
መርጡለ ማርያም
መስኮት- መርጡለ ማርያም
መርጡለ ማርያም
- ↑ Guida, consoziazione turisticta Italiano, Milano, 1938, p398
- ↑ Cheesman, "lake Tana and the Blue Nile" p269